ፍቅርን መቀበልም ማብቀለም ፈተና ነው።
ፍቅርን መቀበልም ማብቀለም ፈተና ነው። ከሥርጉተ ሥላሴ 16.06.2018 ከመነኩሴዋ ሲውዝዬ ነፍሴ። „ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሄርን እጠራለሁ፤ ከጠላቶቼም እድናለሁኝ።“ (መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ምዕራፍ ፳፪ ቁጥር ፬) · መክፈቻ ። እንዴት ናችሁ የኔወቹ የልቦቹ አባ እና እማ እነ ቅንዬ ? ዛሬ ቀኑ ፈታ ብሏል። ፏ ብላlች ልዕልተይ። አሁን አንድ ጹሑፍ ከብራና ሳተናው አነበብኩኝ። ከማከብራቸው ጸሐፊ አቶ ስዩም ተሾመ ነው። ወቅታዊ ነው ብዬም አላምንም። ጭብጡ ለአብይ መንፈስም ተቀራራቢ አይደለም ብዬ አምናለሁኝ። ተቀራራቢ ያልሆኑ መንፈሶች ሃሳብን ከመክፈል ውጪ ለምናስበው ተስፋ ጠቃሚ አይደለም። ክብሩነታቸው በማህበረ ደራጎን ታፍነው ባሉበት በዚህ ወቅት የሚያጽናና እና የሚያበረታታ፤ ሃሳብን የሚደግፍ እንጂ እንዲህ ያሉ መንፈሶች እንብዛም ለተሰፋ አይረዱም። ስለዚህም ሚዛኑን ማስጠበቅ ታሪካዊ ድርሻዬ ስለሆነ የግድ መጻፍ ነበረብኝ። ተጥፏልም። አሁን እንደ አዬሁት ወደ 362 ሰው ሸር አድርጎታል። ያው ብሶትን ማባበል የተለመደ ስለሆነ። በስተጀርባ በስተፊት ጠቀሜታ እና ጉዳቱ ለማን እና ለምን የሚለውን ብዙም አናስብበትም። የራሳችን አቅም በተሰበረ ቁጥር የትውልድ ብክነት ቀጣይነት አይታዬነም። የእኛ ፖለቲካ ልግመኛም መሆኑ ብቻ ሳይሆን የሚያሳዝነው ከግል ምኞት ጋርም የተጠባቀ መሆኑ ነው። · መነሻ። „ለሀገር ሰላም፣ ለሕዝብ ደህንነት