ልጥፎች

ከጁን 16, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ፍቅርን መቀበልም ማብቀለም ፈተና ነው።

ምስል
                            ፍቅርን መቀበልም ማብቀለም ፈተና ነው።                                       ከሥርጉተ ሥላሴ 16.06.2018 ከመነኩሴዋ ሲውዝዬ ነፍሴ።                                „ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሄርን እጠራለሁ፤ ከጠላቶቼም እድናለሁኝ።“                                               (መጽሐፈ ሳሙኤል ካልዕ ምዕራፍ ፳፪ ቁጥር ፬) ·          መክፈቻ ። እንዴት ናችሁ የኔወቹ የልቦቹ አባ እና እማ እነ ቅንዬ ? ዛሬ ቀኑ ፈታ ብሏል። ፏ ብላlች ልዕልተይ። አሁን  አንድ ጹሑፍ ከብራና ሳተናው አነበብኩኝ። ከማከብራቸው ጸሐፊ አቶ ስዩም ተሾመ ነው። ወቅታዊ ነው ብዬም አላምንም። ጭብጡ ለአብይ መንፈስም ተቀራራቢ አይደለም ብዬ አምናለሁኝ። ተቀራራቢ ያልሆኑ መንፈሶች ሃሳብን ከመክፈል ውጪ ለምናስበው ተስፋ ጠቃሚ አይደለም። ክብሩነታቸው በማህበረ ደራጎን ታፍነው ባሉበት በዚህ ወቅት የሚያጽናና እና የሚያበረታታ፤ ሃሳብን የሚደግፍ እንጂ እንዲህ ያሉ መንፈሶች እንብዛም ለተሰፋ አይረዱም። ስለዚህም ሚዛኑን ማስጠበቅ ታሪካዊ ድርሻዬ ስለሆነ የግድ መጻፍ ነበረብኝ። ተጥፏልም።   አሁን እንደ አዬሁት ወደ 362 ሰው ሸር አድርጎታል። ያው ብሶትን ማባበል የተለመደ ስለሆነ። በስተጀርባ በስተፊት ጠቀሜታ እና ጉዳቱ ለማን እና ለምን የሚለውን ብዙም አናስብበትም። የራሳችን አቅም በተሰበረ ቁጥር የትውልድ ብክነት ቀጣይነት አይታዬነም። የእኛ ፖለቲካ ልግመኛም መሆኑ ብቻ ሳይሆን የሚያሳዝነው ከግል ምኞት ጋርም የተጠባቀ መሆኑ ነው። ·         መነሻ። „ለሀገር ሰላም፣ ለሕዝብ ደህንነት

ክፉዎች የተፈጠሩበትን ነው የሚሠሩት- እኛሥ ሥማችን ማን ይባል?

ምስል
                    ክፉዎች የተፈጠሩበትን ነው የሚሠሩት።                              አሳዛኙ ነገር እኛ ማዳበሪያ መሆነችን ነው።                                  ሥንሠራው የባጀነው ይሄንኑ ነው።                                                ከሥርጉተ ሥላሴ 16.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ)                               „መዳህኒቴ ሆይ ከግፍ ሥራ ታድነኛለህ።" (መጽሐፈ ሳሙኤል ምዕራፍ ፳፪ ቁጥር ፫) ያለን ወገን ኑሮው ይህን ይመስላል። አብይ የተረከበው ። ክፉዎች ክፉ ናቸው። የተፈጠሩበትን ነው የሚሠሩት። አሳዛኙ ነገር ለመልካም ነገር እንተጋለን የሚሉት የነፃነት ታጋዮች ይህን መሰል የመከራ ዜና የሚናፍቃቸው መሆኑን ነው። ለዚህ BBN ለናሙና መውሰድ ይቻላል። ይህ ሚዲያ ከጅምሩ ኦቦ ለማ መግርሳን ኮንኖ የተነሳ መሆኑ የታወቀ ነው። ከዚያ ቀጥሎ በዶር አብይ ዙሪያ እጅግም ከሰው በወረደ ሁኔታ ደፍሮ የተወያዬ ሚዲያ ነው። https://www.youtube.com/watch?v=FqzoTUA4V8E News Analysis: Hidden Truth About Lemma Megersa https://www.youtube.com/watch?v=tSKRWiXexSU BBN Presents Jawar Mohammed | Lemma Megersa | Oromo | Amhara | EPRDF አንድ ሰው ጊዜውንም ፍቅሩንም ውስጡንም የሰጠው ሚዲያ እንዲህ ሲሆን እጅግ ያሳዝናል። ሌሎቹ እንደ ኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን ያሉት የፖለቲካ ተፎካካሪዎች ስለሆኑ የተሻለ አቅም በመጣ ቁጥር ዳጥ እና ምጥ ስለሚይዛቸው ምኞታቸው ተንጠልጥሎ አዬር ላይ ስለቀረ