ልጥፎች

ከጁን 28, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ከሞቀ ተንቧላይ።

ምስል
ከሞቀ ተንቧላይ። ከሥርጉተ ©ሥላሴ 28.06.2018  (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።) „አቤቱ በቁጣህ አትቅሰፈኝ በማዓትህም አትገስጸኝ።“      (መዝሙር ምዕራፍ ፮ ቊጥር ፩) መጣድ ለምድጃ መቼ አስቦት ለሰው ከሞቀው መደንከር በማለት ተውሎው። ትንት ከትናንቱ ሊሆን ተተላይ ዛሬም እንቶ ፈንቶ ምላስ ተንቧላይ። ባትሪ እያለለት ሲቸገር ስልባቦት ከንፈር ምን ሲገደው ስፖርት እያለለት። ዓይን ጆሮ ቢኖረው ምንኛ ይነደው በስንጥቅ በትርትር እፍረቱን ሲልጠው። የሙርቅርቅ ሰፌድ ተዚያ ተዚህ ማዶ የፍርክርክ ቤቱ አለሁ ባይ ተንዶ። ዝቅ ብሎ መኖር ምንኛ ይደላል እንደ ልብ ለመኖር ማተብ ያድላድላል። አያፍሬን ጥሩተኝ ትንሽም ያቅራራ የሞቀ ምጣድ ነው የዕብለት ገራራ። በምንስ ጉብታ በምንስ መቆረር ማንቆርቆሪያ ጠፍቶ ገበታ ሲደፈር። እነ የትነበሩ የዘመን አልጫ እውነት ቀኗ ጠፍቶ ስትሆን ግራጫ። ማገዶ ተማግዶ ጢስ አልባ መሆኑ ጥሩኝም መጣንም ለአውነት አይሆኑ። ሃቅ በቀኗ ቀልማ ስትጣራ ነገን መጥረቢያ ተስሎ በነበር ግናግን። ታከለነ ብለውል እና ፊታውራሪ፤ ደግሞ ሊጨመሩ ሚዛን በመጥፋቷ ከበለስ ሊዳሩ። የውልድ ቡልታ በባንድም ቢተሙ መቼስ ዕውነት አይቀር ምንስ ቢላተሙ። እስቲ ተጠዬቂ አንቺ የውነት ማህደር ጠፍፍ ያልሽ ንጡሔ የቃል ነሽ መፈጠር። ግራሞት ተስቦ፤ ክፉኙ አይሎ ማባዘት ሥራው ነው የጥጥፍሬ አለሎ። ከግራር ከወይራው ከአባሎ ሲዊሉ ብርአንባር ተሆነ ሰው ለቀማ ስሉ። ተጠፈ አሁን 29.06.2018 ·     ሥ ጦታ ቀን ለተጣፋባት ዕውነት።   የኔዎቹ እናንተን ያኑርልኝ። መ

ይድረስ ለኦቦ ለማ መግርሳ፤

ምስል
የሁለት አገር ስደተኛዋ ሴት የእኛዊነት አርበኛዋ! "ጽዮን እጇን ዘረጋች የሚያጽናናት የለም።" (ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፲፯)    ከሥርጉተ ©ሥላሴ 28.06.2018     (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።)  ይድረስ ለኦቦ ለማ መግርሳ ለኦሮምያ ክልላዊ መስተዳደር ፕሬዚዳንት አዳማ። ግን ሰሞኑን ድምጠዎት ጠፍቶኛል? በጤናወት ነው ወይ ኦቦ ለማ መግርሳ? ዛሬ መረር ያለ ነገር ገጥሞኝ ፍቹ ቢጨንቀኝ፤ መንገዱ ቢጠፋብኝ ነው ለክብርነተዎት ይህን ደብዳቤ እንድጽፍ የተገደድኩት። ይድረሰዎት አይድርሰዎት አላውቅም። ጉዳዩ ስለጠንካራዋ፤ ስለብርቱዋ፤ ተኪ ስሌለት ጸሐፊ አርቲስት አስቴር መዳኔ ነው። https://www.youtube.com/watch?v=GcBhXSaFReM Ethiopia: “ ከዶ / ር አብይ ጋር ባለኝ ወዳጅነት የተነሳ የግድያ ዛቻዎች እየደረሱኝ ነው ” ቃለ ምልልሱን እያለቀስኩ ነበር የሰማሁት እጅግ አዝኛለሁ? እንዴት ነው ኦቦ ለማ መግርሳ „ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው“ ተቀለበሰ ወይ? እኔም መንፈሴ ቢመጣ እንዲህ እንደ ውሻ ውጪ ተብዬ ልባረር ይሆን? አዝኛለሁኝ።  ሰሞኑን ጠ/ሚር አብይ አህመድ ለኪነጥበብ ሰዎች የትምህርት ዝግጅት ነበራቸው። በዚህ ስብሰባ ላይ ታሪክን የሚያጠቁር ነገር ተፈጥሯል። ሴቶች ዛሬም እናልቅስን?  ·       ው ስጤ ስለ እኛዊነት አርበኝት እንዲህ ይለኛል! መቼም ገረመኝም፣ ደነቀኝም፣ አዘንኩኘም ምን አንደምለው አለውቅም ብቻ። ኢትዮጵያ በከፋት ጊዜ፤ አላዛሯ ኢትዮጵያ ባዘነች ጊዜ፤  እምዬ ባነባች ጊዜ እኔ አለሁሽ ብላ ፊት ለፊት ራሷን የማገደች አርበኛ የጥበብ ሰው ናት የሰብዕዊ ተሟጋቿ አርቲስት አስቴር መዳኔ።

ክፍል አምስት ሰቆቃው አማራ።

የቱ ይቅደም ስለ ሶቆቃው አማራ? ክፍል አምስት።   ከሥርጉተ ©ሥላሴ  28.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) „ወደ ጉባኤህ እንዳይገቡ ያዘዝሃቸው እህዛብ           ወደ መቅደስዋ አይታለችና “  (ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ፩   ቁጥር ፲ ) ·       መነ ሻ። https://www.youtube.com/watch?v=EMCbOlzvr9A አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ስለወልቃይት እና ቅማንት ጉዳይ መልስ ሰጡ Part 2 ·       እፍታ። ዛሬ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአማራ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ውይይት አዳመጥኩት። የአማራ ቴሌቪዥን ችግሩ ቀንጨብ እያደረገ የሦስት እና የሁለት ደቂቃ ቅርጥምጣሚ መረጃዎችን ከመለጠፍ የሽወዳ ፖለቲካ  ወጥቶ ሙሉውን ለቆታል። ስለሆነም ነው ዛሬ ጥዋት ሙሉውን ለማድመጥ የፈቀድኩት። ቋረጥራጣውንማ ዞር ብዬም አይቼው አላውቅም። ·       ው ጪና ውስጥ። ከክልሉ ውጪ ስላሉት አማራዎች የፖለቲካ ተስትፎ በሚለከት እኔ እዬሳቅኩኝ ነበር የተከታተልኩት የ አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን መልስ። ቀድሞ ነገር መሬቱ ላይ አማራን አማራ ውክሎት ያውቃልን ብአዴን? ብአዴን የአማራ ነውን? አማራን አይደለም በፖለቲካ ተስትፎ በዬመንግሥት መስራያ ቤቱ ከታች እስከ ላይ ማን ነው ባለቤቱ? እኮ ማነው? እማናውቅ መሰላችሁን? ከአማራ ተጋድሎ ጋር በተያያዘ ስንት የአማራ ሊሂቅ ልጆች ሥራ ፈት ቤት ውስጥ እንደተ ቀመጡ ግን ታሰቦ ያወቃልን? አማራ መሬት ላይ አማራን አስወክሎ ማውጣት ሳይቻል በሌላው ክልል ላይ ፖለቲካ ተስፎ ማሰብ መቼም ቁርጥማት ነው ለዛውም የህሊና። መጀመሪያ ክልልህ ነው በተባለው አማራ መሬት ላይ መሪዎችን ይመርጥ። መሪዎቹን ሲመርጥ ደግሞ ቅማነትም፤ አገውንም ኢት

ክፍል አራት፤ የአማራ ሰቆቃ።

ምስል
የቱ ይቅደም ስለ ሶቆቃው አማራ? ክፍል አራት።   ከሥርጉተ ©ሥላሴ 28.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) „ህፃናቶችዋ በአስጨናቂዎች ፊት ተማርከዋል“  (ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፭ ) ·       መነ ሻ። https://www.youtube.com/watch?v=EMCbOlzvr9A አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ስለወልቃይት እና ቅማንት ጉዳይ መልስ ሰጡ Part 2 ·       እፍታ። ዛሬ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአማራ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ውይይት አዳመጥኩት። የአማራ ቴሌቪዥን ችግሩ ቀንጨብ እያደረገ የሦስት እና የሁለት ደቂቃ ቅርጥምጣሚ መረጃዎችን ከመለጠፍ የሽወዳ ፖለቲካ  ወጥቶ ሙሉውን ለቆታል። ስለሆነም ነው ዛሬ ጥዋት ሙሉውን ለማድመጥ የፈቀድኩት። ቋረጥራጣውንማ ዞር ብዬም አይቼው አላውቅም። ·       ፍንቅለት። በዚህ ገለጻ ላይ ያልተመቸኝም የተመቸኝም አገላለጽ አለ። ችግሩን ከመሠረቱ መፍታት ወሳኝ ጉዳይ ነው። ነገር ግን ችግሩን ከመሠረቱ ለመፍታት በሚወደሰው የጊዜ ቆይታ ውስጥ የአማራ ልጆች እዬተፈናቀሉ መሆኖ አጀንዳ መሆን ግድ ይላል። „እኔ እምሞት ዛሬ ማታ እህል የሚደርስ በፍልሰታ“ እንዳይሆን። ዛሬ እኮ መጠለያ ያጡ የአማራ ልጆች ስለነገ ተስፋ መንገር ዛሬን አያሳድራቸውም። ስለዴሞክራሲ ማውራትም እህል ውሃ፤ መጠለያ አይሆናቸውም። አንድ ሰኔ የነቀለውን አስር ሰኔም አይተክለውም። ለገበሬው እኮ የህይወት ወቅቱ ነው። ስለዚህ ለዛሬ የዛሬን መፍትሄ ሰጥቶ የነገውን ደግሞ በቀጠሮ ማዬት ሲገባ ለዘለቄታ መፍትሄ እዬተሰራ ነው፤ ቧልት ነው። ·       ቧ ልት። እነሱ ሜዳ ላይ ፈሰው  ክልሎች ጋር በስልክ እዬተነጋገር ነው፤ በፍጹም ሁኔታ የሚያስኬድ አ

ክፍል ሦስት ሰቆቃው አማራ።

ምስል
የቱ ይቅደም ስለ ሶቆቃው አማራ? ክፍል ሦስት።   ከሥርጉተ ©ሥላሴ 28.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) „በ አውራጃዎች መካከል ልዕልት የነበረች ተገዢ ሁናለች“  (ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፪) ·       መነ ሻ። https://www.youtube.com/watch?v=EMCbOlzvr9A አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ስለወልቃይት እና ቅማንት ጉዳይ መልስ ሰጡ Part 2 ·       እፍታ። ዛሬ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአማራ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ውይይት አዳመጥኩት። የአማራ ቴሌቪዥን ችግሩ ቀንጨብ እያደረገ የሦስት እና የሁለት ደቂቃ ቅርጥምጣሚ መረጃዎችን ከመለጠፍ የሽወዳ ፖለቲካ  ወጥቶ ሙሉውን ለቆታል። ስለሆነም ነው ዛሬ ጥዋት ሙሉውን ለማድመጥ የፈቀድኩት። ቋረጥራጣውንማ ዞር ብዬም አይቼው አላውቅም። ·       ይ ድረስህ።  ዛሬ ዛሬ የአማራ ሰቆቃ ሌለውም ማህበረሰብ ይድረስህ ተብሏል። የ66ቱ ፖለቲካ በኪሳራ ሲጠነቀቅ ኦሮሞ እና አማራ እና አዋግቶ በስውር የሥልጣን ኮረቻ ለመዝለቅ ያሰበው የወያኔ ሃርነት ማንፌሰቶ መሳፍንቶች የወለቀ ማሰሮ በመሆናቸው ምክንያት ማነው ባለሳምንት እያሉ ትግራይን ያልነካ ሰቆቃ አና ብለው ተያይዘውታል። በዬቦታው፤ በዬቀዬው ሞት ነግሶ ሶቆቃ ሲፈነጥዝ ለወያኔ ሃርነት ትግራይ የልዕልታ የሠርግ እና የመልሱ መደለቂያ የፍንድሻ ማሽሞንሞኛ የጫጉላ ጊዜው ነው። ሞት፤ መፈናቀል፤ ሃዘን ለቅሶ ዋይታ ...  ይህን አስታርቆ ለመጓዝ ደግሞ የቀደመው ክ/ሀገራዊ የወሰን ክልል ካልሆነ ሌላ ሊፈታው የሚችል ነገር የለም። ይህም ቢሆን ጥናትን፤ ጊዚን ባለሙያን፤ ቅንነትን፤ ልበ ንጽህናን ይጠይቃል። እብሶ ከሴራ እና ከበቀል የጸዳ ማንንት ይጠይቃ

ክፍል ሁለት፤ ሰቆቃው አማራ።

ምስል
የቱ ይቅደም ስለ ሶቆቃው አማራ? ክፍል ሁለት።   ከሥርጉተ ©ሥላሴ 28.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) „ወዳጆቿ ሁሉ ወነጀሏት ጠላቶችም ሆኑአት።“  (ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፪) ·       መነ ሻ። https://www.youtube.com/watch?v=EMCbOlzvr9A አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ስለወልቃይት እና ቅማንት ጉዳይ መልስ ሰጡ Part 2 ·       እፍታ። ዛሬ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከአማራ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ውይይት አዳመጥኩት። የአማራ ቴሌቪዥን ችግሩ ቀንጨብ እያደረገ የሦስት እና የሁለት ደቂቃ ቅርጥምጣሚ መረጃዎችን ከመለጠፍ የሽወዳ ፖለቲካ  ወጥቶ ሙሉውን ለቆታል። ስለሆነም ነው ዛሬ ጥዋት ሙሉውን ለማድመጥ የፈቀድኩት። ቋረጥራጣውንማ ዞር ብዬም አይቼው አላውቅም። ሰፊውን ማህበረስብም ያለው አማራ ሰፊውን አምንያን ያሉትንም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ከፖለቲካ የውሰኔ ማህደር ውስጥ አውጥቶ የኢትዮጵያን ቀጣይንት ማሰብ ከባድ ነው። 27 ዓመት የተገለለው አማራ እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት አመንያን በፖለቲካ መስክ በፍጹም ሁኔታ መገለላቸውን በዬትኛውም መስፈረት ቁልጭ ብሎ እዬታዬ ነው።  ይህን በአፍንጫ ይውጣ ሳይሆን ዬክልሉ መንግሥታዊ ሃላፊዎች ሊያሰቡበት ይገባል። እኩል አመጣጥኖ ማውጣት ካልተቻለ ህብራዊነቱም ይጉድፋል፤ ውሳጤዊ አመጽም ጠንክሮ ጫፍ መያዝ ይመጣል። ·       ቋተ ህማማት! እውነት ለመናገር ይህ የ43 ዓመት መከራ ስለሆነ አደብ የሚጠይቅ ሲሆን ተከታታይ ተግባራትን ግን በአጽህኖት ይጠይቃል። በተለይ የአማራ ሊሂቃን ቀልዱን አቁመው በፍጥነት ወደ ራሳቸው መመለስ ይኖርባቸዋል። ሊቆጫቸው፤ ሊቆረቁራቸው