ልጥፎች

ከዲሴምበር 4, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ

81 ንፁህ አማራወች በጅምላ ከእስር ቤት ተረሸኑ። የኦሮምያ ልዩ ኃይል በኦነግ የጫካ ክንፍ ጥምር ጆኖሳይድ ተፈፀመ።

81 ንፁህ አማራወች በጅምላ ከእስር ቤት ተረሸኑ። የኦሮምያ ልዩ ኃይል በኦነግ የጫካ ክንፍ ጥምር ጆኖሳይድ ተፈፀመ።   "ተረኝነት" እያለ የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ አዝሎ በመተርጎም አቅምን ሲቀብር የኖረው ፖለቲከኛ ተንታኝ፤ ጋዜጠኛ ዘጋቢ አሁን ያስረዳኛል። ዕጣ ነፍሴን አራት ዓመት ሙሉ አሁን ያለው የገዳ ሥርዓት ነው። የገዳ ወረራ፤ የገዳ መስፋፋት፤ ዬገዳ አስምሌሽን፤ ዬገዳ ዲስክርምኔሽን ነው። ከችግሩ ጭብጥ ካልተነሳን መፍትሄው ይርቃል።    "ተረኝነት" የሚለው እጭ ላይ ያለ ፖለቲካ አዛይ እና ትጥቅ አስፈቺ ነው ስል ሰሚ አላገኜሁም ነበር። እኔከዚህም አልፌ የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ ሴሪሞኒያዊ መፍነሽነሹን ትቶ የእስራኤሎችን፤ የስፔኖችን መንገድ ይከተል በማለት በትጋት ሠርቻለሁኝ። ለዚህ ነው ዛሬ ትግሉን እንመራለን ያሉት አንጨባርቀው፤ አንጨባርቀው መራራ ስንብት ሲፈፅሙ በተደሞ፤ በጥሞና በዝምታ እዬተከታተልኩ የምገኜው። ይህ ቀረ እምለው አንዳችም ጉዳይ የለም። የትግል አቅጣጫውን ፍንትው አድርጌ ፅፌ፤ አስገንዝቤያለሁኝ። ፀፀት የለብኝም። ተረኝነትን አጉልተው የሚያስጮሁት በግርዶሽ የሥርዓቱ ዋቢወች ናቸው። ይህን ዘመኑ ይገልጠዋል። እንደምን የትግሉን አቅጣጫ እያወኩ ሲያተራምሱት እንደባጁ።   • https://sergute.blogspot.com/2022/05/blog-post_21.html ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም። - ዲሴምበር 16, 2019 • ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም። ከዚያ የከበደ መከራ ላይ ናቸው አላዛሯ ኢትዮጵያም ሆነ እማማ አፍሪካም። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱) ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Se