ልጥፎች

ከማርች 4, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አስደማሚ ታሪክ /ከጸሐፊ መስፍን ማሞ/

ምስል
አስደማሚ ታሪክ “እግዚአብሔርን፤ --- አንተ ጌታዬ ነህ አልሁ።  መዝሙር” ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፪ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! ኢትዮጵያ የአውሮፓን አይሁዶች ከሂትለር እልቂት ታድጋለች! (ትርጉም) የኢየሩሳሌም ፖስት (The Jerusalem Post) በ27/1/19 ባስነበበው ዕትሙ ይዞት የወጣው ታሪክ ‘ርዕስ’ ነው - ከላይ የቀረበው። ይዘቱ እንዲህ ይከተላል።  በአውሮፓ በናዚዎች የሚካሄደው ዕልቂት ጡዘት ላይ በደረሰበት ኦገስት 1943 (እኣአ) ኢትዮጵያውያን አይሁዶች (ፈላሻዎች) በመሪዎቻቸው አማካይነት ንጉሠ ነገሥት ሃይለ ሥላሴን በመቅረብ አስደማሚ የሆነ ጉዳይ አቀረቡላቸው። የአውሮፓ አይሁዳውያንን ኢትዮጵያ በስደተኝነት እንድትቀበልና እነሱም በፈላሻዎች መኖሪያ መጠለያ እንዲያገኙ ንጉሡ እንዲረዱ የሚል ነበር ጥያቄያቸው። በዋርሶ (Warsow) የጌቶ (Ghetto) አመፅ ከተካሄደ ሶስት ወር በሁዋላና የናዚዎች ማሰቃያዎች አራቱ የኦሽዊትዝ ማቃጠያዎች (Auschwitz crematoria) በሥራ ላይ ከዋሉ ሁለት ወር በሁዋላ የዛሬው ጄሩሳሌም ፖስት በቀድሞው መጠሪያው ፓልስታይን ፖስት (Palestine Post) ኢትዮጵያ አይሁዳውያን ስደተኞችን መቀበሏን የሚያትት ዘገባ ይዞ ወጣ። ኦገስት 8/1943 የታተመው ይህ ጋዜጣ ሲያብራራ “የአይሁዳውያንን ወደ ኢትዮጵያ የመሰደድ (Jewish Immigration to Abyssinia) አማራጭ በሎንዶን የሚገኙት የኢትዮጵያ ሚኒስትር ከአቶ ሃሪ ጉድማን (Harry Goodman) እና ከእስራኤል የአጉዳቱ ዶ/ር ስፕሪንገር (Dr. Springer of Agudath) ጋር ተወያይተዋል” ብሏል።  “የአውሮፓ አይሁዳውያንን በፈላሻዎች መንደር እንዲጠለሉ ለማድረግ የፈላሻ መ

እነ አያልቅበት ብአዴኖች ደግሞ ምን እያሉን ነው?

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  እነ አያልቅበት ? „የሞት ጣር ያዘኝ“ መዝሙር ምዕራፍ ፲፯ ቁጥር ፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  04.03.2019  ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ።                                                 አሁን ደግሞ ከመጋቢት 24. ቀን 2010 ጀምሮ                                                   በኦህዴድ ሎሌነት አዲስ መጸሐፍ ይጻፍለታል ።                                                         ሰኔል ላይ ለሽ ብሎ ለተኛው ብአዴን። መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=LSgTOyi8uCk&t=3s " ለአማራ ሕዝብ ባሪያ እንሆናለን። " አዴፓ ·        ተ ናግሮ አናጋሪ ነው ብአዴን … ድንቄም! ብለናል ብአዴን ለአማራ ህዝብ ባሪያ እሆናለሁ የሚለውን ተረት ተረት። ለኦነጋውያን ባሪያ እንሆናለን ቢባባል ያምራል። ኦዴፓ // ኦህዴድ ለውጥ ከታባለበት ቀን ጀምሮ የኦሮሞ ሙሁራንን፤ የኦሮሞ ጸሐፍትን፤ የኦሮሞ ፖለቲከኞችን፤ የኦሮሞ ብለጎሮችን፤ የኦሮሞ የሲቢክስ ድርጅቶችን፤ የኦሮሞ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችን፤ የኦሮሞን አክቲቢስቶችን አቅም ያላቸውንም የሌላቸውንም፤ በአገር ውስጥ እና በውጪ በትጋት፤ ባልተቋረጠ ትትርና በዶር ለማ መገርሳ የቅድሚያ ቅድሚያ ተስጥቶት ሲሳረበት ባጅቷል። ብአዴን ደግሞ የፌድራል መንግሥቱን ጫና ተሸክሞ ግርባነቱን ሲከውን ከራርሟል። ይህም ብቻ አይደለም የኦሮሞ አክቲቢስቶች፤ የኦሮሞ ጸሐፍት፤ የኦሮሞ ደም ያላቸው ሁሉ በተገኘው የሃላፊነት ቦታ ሁሉ በክብር በልዕልና ቦታ ሲሰጣቸው አያሆይ ብአዴ

የአባ ገዳ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ሚዲያ AMMA „ፊንፊኔ“ ማለትን አህዱ አለ።

ምስል
 እንኳን   ደህና   መጡልኝ።  የአባ ገዳ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ሚዲያ  AMMA „ፊንፊኔ“  ማለትን አህዱ  አለ። „አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል?  በተቀደሰው ተራራህስ ምን ይኖራል?“ መዝሙር ፲፬ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  04.03.2019  ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። ·          መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=7-czVdnfWA0 " የት እንግባ ?" ቤታቸው የፈረሰባቸው የለገጣፎ ነዋሪዎች በብአዴን በዘመነ ህወሃት እንዳሻቸው ሲወራኙበት የነበረው የሳጅን በረከት ዘመን ተጠናቆ አሁን ለባለተራው ለአባ ገዳ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ለጥ ብሎ በመስገድ ላይ ይገኛል። ጥቁሩ ዘመን በአዲስ የባርነት ጥቀርሻማ ዘመን በተሃድሶ ላይ ይገኛል። እንሆ የህወሃትን ዓርማ የህወሃትን ዓላም እና ግብ የጣለለትን እራፊ ጨርቅም መለያዬ ነው ብሎ አደግድጎ በሎሌነት ወደ ተግባር ለመቀዬር ከፍ እና ዝቅ ሲል 27 ዓመት ሙሉ የባጀው ብአዴን አሁን ደግሞ የአማራ የማንነት ተጋድሎን ድል እና ዕሴት አሳልፎ ለኦነጋውያን በማስረከብ ለአዲሱ ግርባነት ለጥ ብሎ ሰግዶ፤ አደግደግዶ በበታችነት ይማስናል። አዲሱ የኦዴፓ ካድሬ ጉዳይ አስፈጻሚ እና የኦነግ አንባሳደር አቤቶ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ሆነው ተገኝተዋል። አጤው በዛ ሰሞን በተርሚናል ምረቃት ላይ ከቤታቸው ተነስተው እስከ አዬር መንገዱ የባዕል ቦታ ድረስ እንደ ታቦት ታጅበው በቴሌቪዥን በተደገፈ ቅንብር ነበር ጉዟቸውን ታደሙ የተባልነው።  ሁለተኛው ይሁኑ አጥቢያው ይሁኑ ሳልሳዊ ይሁን የሳቸው ደረጃ ባይታወቅም።  በዚህ የሰላይነት ተግባራቸውም አንቱ ሆነው ቁንጮው የጠ/ሚር ሆ

እግዚኦ!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ስለምን ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ይሳደዳሉ? „በክፉዎች ምክር ያልሄደ፤ በሃጢያተኞች ምክር ያልቆመ፤  በዋዘኞች ወንበር አልተቀመጠ፤ እሱ የተመሰገነ ነው።“ መዝሙር ፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  04.03.2019  ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ አሜን። ·        መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=niRWapzk9rg Ethiopia: ጥብቅ መረጃ - የአቡነ ማቲያስና የዶ / ር አብይ አህመድ ምስጢራዊ ስብሰባ | "" አዲስ አበባን ለቅቄ እሄዳለሁ " አቡነ ማቲያስ ·        መግቢያ። ውዶቼ እንዴት ሰነበታችሁ። በቅድሚያ እንኳን ለጥቁሮች የድል ቀንዲል ለሆነው ለ123 የዓድዋ ድል በሰላም አደረሰን። ኦነግ ደግሞ ሚኒሶታ ላይ በዚኽው ቀን በታቀደ ሁኔታ ፍላጎቱን አስፈጽሟል።  በሌላ በኩል በባዕት ያሉት ደግሞ የኦነግ አክሮባቲስቶች ነገሩ ሁሉ ግልብጥብጥ አድርገው እነ አደናግሬ አዲስ ጎፈር ለብሰው ብቅ ብለዋል። እነሱንም እንኳን ለዚህ ቀን አበቃቸው። ሥማችን እንደ ንቀይር ተደረግን ከማለት ጀምሮ በበታችነት ለዘማናት ሲማስኑ ከባጁበት አረንቋ ወጥተው በቅጽበት ደግሞ የአድዋ ድል ታዳሚነታቸው ታይቷል። ከምን እንደተፈጠሩ ራሱ እስኪገርመን ድረስ። በሌላ በኩል ዛሬ አብይ ፆም ለቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማንያን ገብቷል። ፆም የፈተና ወቅት ነው። ፈተና በራሱ ጊዜ ሲመጣ መልካም ነው እና ብፁዕ ወቅዱስ ሊቀ - ሊቃውንት አባቶቻችን የቀደመውን ጽናታቸውን አስቀጥለው ቅድስት ቤተ ክርስትያናችን ልዕልና ያስከብሩ ዘንድ ልዑ