ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 15, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የሰማይ እና የምድር ንጉሥ እዬሱስ ክርስቶስ "#ክንፍ" አለውን? የወሮ ዝናሽ ታያቸው ውኃ ያልነካው ፈጣጣ ፈንጣጣም አስተምህሮ ሃግ ሊባል ይገባል።

ምስል
  የሰማይ እና የምድር ንጉሥ እዬሱስ ክርስቶስ " #ክንፍ " አለውን? የወሮ ዝናሽ ታያቸው ውኃ ያልነካው ፈጣጣ ፈንጣጣም አስተምህሮ ሃግ ሊባል ይገባል። ስለ ቃሉ ንሰኃ እገባበታለሁ አይደለም ብራና ዘርግቶ ሥንኝ ጽፎ በአደባባይ ለመዘመር ቀርቶ? #ለሚመለከተው ሁሉ። "አቤቱ ከድፍረት ኃጢያት ባርያህን ጠብቀኝ።   ወደ እግዚአብሄር አምላክ ለሚቀርብ ምስጋና እንዲህ በድፍረት እና በማናአለብኝነት ተንጠራርቶ ጥሰት ውስጥ መዘፈቅ የጤና አይመስለኝም። ለነገሩ የ፬ኪሎው ቤተ መንግሥት ሽብር፤ ጭንቅ ውስጥ እንደባጀ ያመሳጥራል። ሌላላው የሰማይ እና የምድርን ፈጣሪ አማኑኤል ለእነሱ ዬግፍ ሥልጣን ብቻ ምርቃት እንዳደረገም ያሳጣል። ሥንኞቹ የባለቤታቸው የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አይደሉም። ዘዬው፤ ዘኃ ግራው የሳቸው የቀዳማዊዋ እመቤት ወሮ ዝናሽ ታያቸው ይመስላል። ምቱም በዚህው ዙሪያ ነው። ጭንቀት፤ መራድ፤ ሽብር እና ራድ ቤተመንግሥቱን መናጡን ያመሳጥራል። ለምን ፈታ ደይሊ እንደዘለለው ሥንኙን አላውቅም። የአነበበውም አሟልቶ አይደለም። አንዷ ፊደል ስትጠብቅ፤ ስትላላ ብዙ እጅግ ብዙ ጉዳዮችን ታመሳጥራለች። አማርኛ ቋንቋ ቅኔም ነው የምለውም ለዚህ ነው። ዘማሪ ዝናሽ ታያቸው አዲስ የዶግማ ፍልሰት መጥረቢያ ይዘው ከች ብለዋል። ጭብጡ እግዚአብሄር ክንፍ አለው ከሚለው አፈንጋጭ ዕምነት እና ዕሳቤ ይመነጫል። እዬገረመኝ ያለው ጉድ የኢትዮጵያ አንስት አማንያን በሃይማኖት ዙሪያ ያላቸው አሁናዊ ድፍረት ነው። ሎቱ ስብኃት። አበስኩ ገበርኩኝ። አሁን በዘመናችን ወደ አራት ተጠግተዋል። በአዲስ ፍልስፍና ፍልሰት ላይ ያሉት ማለቴ ነው። አባቶቻችንም ሃግ አይሉም። እሱ ብቻ ሳይሆን አንጡራ ጥሪታቸው ለሌላ ሃይማኖት ተቋም መጠሪያ ሲሆንም አንተ ታውቃለህ ብለው ዝም ሆኋ

ግን ዶር ዳንኤል በቀለ በህይወት አሉን? እስከመቼ ድረስ ይህን ኢ- ሰባዕዊ፦ ኢ- ተፈጥሯዊ ዬአረመኔ ሥርዓት አገልጋይ ሆነው ይቀጥላሉ? መቼ ነው የኃላፊነት መለቀቂያ የሚያስገቡት???? በጉጉት እጠብቃለሁ። ንስኃም፤ ፀፀትም።

ምስል
ግን ዶር ዳንኤል በቀለ በህይወት አሉን? እስከመቼ ድረስ ይህን ኢ- ሰባዕዊ፦ ኢ- ተፈጥሯዊ ዬአረመኔ ሥርዓት አገልጋይ ሆነው ይቀጥላሉ? መቼ ነው የኃላፊነት መለቀቂያ የሚያስገቡት???? በጉጉት እጠብቃለሁ። ንስኃም፤ ፀፀትም። ስክነት ስንቃችሁ የሆነው የቤታችን ቤተኞችእባካችሁ ሼር አድርጉልኝ። አመሰግናለሁ። "አቤቱ የመዳህኒቴ አምላክ በቀን እና በሌሊትበፊትህ ጮኽሁ፤ ፀሎቴ ወደ ቤትህ ትግባ፥ ጆሮህን ወደ ጩኽቴ አዘንብል፤ ነፍሴ መከራን ጠግባለች እና፥ ህይወቴም ወደ ሲኦል ቀርባለች እና፥ ወደ ጉድጓድ ከሚወርዱ ጋር ተቆጠርሁ፤ ረዳት እንደ ሌለው ሰው ሆንሁ።" (መዝሙረ ዳዊት ፹፯ ከቁ ፩- ፬)     ለማከብረወት ለዶር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ የሰባዕዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር። አዲስ አበባ።   እኔ በምን ሁኔታ ላይ እንደምገኝ ድንግል ብቻ ታውቃለች። መከራን ገድሞ ማስተናገድ የፈተናወች ሁሉ ቁንጮ ነውና። የሆነ ሆኖ ዶር ዳንኤል በቀለ የዘመን መለወጫን በምን ሁኔት አከበሩ? ቀለል ያለች ጓዘ ቀላል ጥያቄ ናት። በዘመኔ ትዝ ሳይሉኝ ሁሉም አውደዓመቶች አልፈዋል። የዘንድሮው መርግ ነበር። ዕንባማ ተራራ። እኔ አገሬን ከለቀቅኩ በቤተ - እግዚአብሄር ዓውደ ምህረት ላይ ከሚከበሩት በስተቀር አክብሬው እማውቀው ዓውደ ዓመት የለም። ያም ሆኖ ግን ቀኑም፤ ሌቱም፤ ሰከንዱም፤ ደቂቃትም መርግ ሆኖ ያለፈው የዘንድሮው ነው። መሸከም - አልቻልኩም። ማስታገስ - አልቻልኩም። ማስተባበልም አልቻልኩም። ማሰብም - ማስታወስም አልፈለግሁም ነበር ግን እንዴት ይቻል???? የአብይዝም የመቃብር ስፍራው፤ የአሳቻው የአብይዝም ሙሉ ካቢኔያችሁ ደግሞ ድልቂያ ላይ ነበር። ማህበረዕብን። ማህከነ። ተሳህለነ። እግዚኦ!! #የሆነ ሆኖ! ዶር ዳንኤል በቀለ ሆይ! ነፍሰወት - አለችን? ትር