ልጥፎች

ከኦክቶበር 12, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አህዱ ራዲዮ እና ዕድምታው በጥቂቱ።

ምስል
አህዱ አሰገዱ። „ተግሳጹን ተቀበሉ ጌታ እንዳይቆጣ፤ እናንተም በመንገድ እንዳትጠፉ ቁጣው ፈጥና ትነዳለችና። መዝሙር ፪ ምዕራፍ ፲፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                                               የላቀው ሊሂቅ! ·       ግ ራሞተ ሰሞናቱ።፡ አህዱ በሚባል ራዲዮ አቶ ሌንጮ ለታ እና አቶ በቀለ ገርባ ቃለ ምልልስ አድርገዋል። ትንሽ በትንሹ እንዬው እስቲ ብዬ አስባለሁኝ። በውይይቱ የተሻለ የመልስ መስጠት ጥበብ በአቶ ሌንጮ ለታ አይቻለሁኝ ስልታዊ እና ግልጻዊ ለመሆን ጥረዋል። የአቶ በቀለ ገርባ ደግሞ ወደ መንፈስ ለመቀረብ ማዶኛ ሆኗል - ለእኔ። ያልመድኩት ነገር የሳቸው ጉዳይ ነው። ጊዜ ያስፈልገኛል።  አድማጮች ሲጠይቁ ነበር። ጠያቂዎች እና አስተያዬት ሰጪዎች አቶ ሌንጮ ለታን ከፍ አድርገው „ክቡር“ እያሉ ማቅረባቸው አቶ በቀለ ገርባን አልተመቻቸውም የመረጋጋት ሁኔታ አላዬሁባቸውም። እኔ ሁለመናን ነው የምከተታለው።  ይህን ሳይ ሚሊዮኖች የሰገዱለት  የአብይ ለማ ፍቅረ አክብሮት እንዴት እንዳስተናገዱት ወፌን ጠይቅኳት። ይገባል አይደል። በሁለቱ ሊሂቃንም ብዙ ሰው ነው የሚጸፈው አክብሮ። ወዶ ናፍቆ አልቆ እና .... እናማ አቶ ሌንጮ ለታን አምስገነው አድማጮች ሲናገሩ ፊድባኩን ለኩት፤  ይህን ወስጠቱን ቪዲዮውን እያዬ መገመት ነው። https://www.youtube.com/watch?v=ifs2-94ibME አቶ በቀለ ገርባ አቶ ሌንጮ ለታ በአሐዱ ሬዲዮ bekele gerba lencho leta interview on ahadu radio አቶ በቀለ ገርባ ባላፈውም ጊዜ ሥሜ በክፉ ተነሳ፤ እን እከሌ አሳንሰው አዩኝ  ብለው እ

የህሊና ሪህ

ምስል
የህሊና ሪህ። „እኔ ግን ንጉሤን ሾምሁ በተቀደሰው ተራራዬ በጽዮን ላይ።“ መዝሙር ፪ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። መነሻ። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/91906 « እኔን እጎዳለሁ ብለህ መሃል ሰፋሪውን አድማ አስተማርክ » | አቻምየለህ ታምሩ ነገረን ነገር ሲያመጣው .. . እኔ አማራ የሆንኩት አቶ አቻምየለህ ታምሩ በቪዥን ኢትዮጵያ ጉባኤ ላይ ተጋብዞ ጊዜ ፈጀህ ተብሎ ሁለት ደቂቃ ሲለምን እና ሌሎች ደግሞ የተሰጣቸውን ዕውቅና አክብሮት ሳይ ነበር በዛች ቅጽበት አማራነቴ ውስጤን ያሟሸው። ጥቃት አልወድም!  እና ሁልጊዜ ሥሙን ሳይ የአቻምን የእኔ አማራነት የመሆን ፈቀድ ከሱ ነፍስ ጋር የተያዘዘ ስለመሆኑ አዘክረዋለሁኝ። የአማራነቴ ሥጦታ የመጣው ከአቻም መገለል ጋር በፅኑ የተያየዘ ነው። ከእንግዲህ ወደኋላ እንደ አልመለስ አድርጎ ደግሞ ቅኑ የጎጃም ህዝብ በደሙ አትሞበታል። የጎጃምን የመሆን ልቅና ያዬሁበት ዘመን በዚህ የአማራ የህልውና የማንነት ተጋድሎ አብዮት ዘመን ነው።  የጎጃም ህዝብ የቅኔ ጉባኤ አቅም እና ቃልኪዳን አማራነቴን የበለጠ አድምቆልኛል።   እሰቃለሁኝ እኔ እዚህ በአማራ ጉዳይ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት በአማራ ክልል ብቻ አማራነትህን ጣል ቲያትር ሲተውን። እሚሆን አይደለም። በልዩ ሁኔታ አማራኔቴ ልክ እንደ ፆታዬ ክብሬ ሆኗል። የአብይ ሌጋሲ ይልቅ ባይደክም ደስ ይለኛል። ሥርጉተ ሥላሴ እኮ ሞገደኛ ናት። የእሷን ልብ፤ የሷን ፍቅር፤ የእሷን ታማኝነት ለማግኘት ብዙ መድከም ያስፈልጋል። እኔ ስላልኩት ሳይሆን ከልጅነት እስከ እውቀት የሚያውቁኝ ሰዎች ያውቁኛል። አብሬያቸው የሠራሁት እንደ ዕድል