ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 23, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ለሦስተኛ ጊዜ የሰማይ ምልክት።

ምስል
እዩት እስኪ ውዶቼ። „በረድኤታችን በእግዚአብሄር ደስ ይበላችሁ፤ ለያዕቆብ አምላክ እልል በሉ“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፹ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ© ሥላሴ 23.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲውዘርላንድ። በ2015 መግቢያ ወር ላይ ሰማይ ላይ ብዙ ሠረገላዎች የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ለብሰው አያለሁኝ። ለአንዲት መነኩሲት እህቴ ደውዬ ነገርኳት። ለቤተሰቦቼም ሲደውሉልኝ ውጪ አገር ለሚኖሩት እንዲሁ ነገርኳቸው።  ከዛ የካቲት 24 ቀን እዚህ ሲዊዘርላንድ የኢትዮጵያ አዬር መንገድ በጀግና ሃይለመደህን አበራ አማካኝነት ካለምንም እንከን ጄኔባ አረፈ። ያው አዬር መንገዳችን ነጹሁን ሰንደቅ ተሸላሚ ስለሆነ ከቤተሰቦቼ ጋር ይህን ነው ያሳዬሽ ተባብለን አለፍነው። ሌላ እውነት ደግሞ ልንገራችሁ። እዚህ ሲዊዘርላንድ የ193 አገሮች ገጽ በሚመለከት አንድ ጥናት ነበር። እኔ ለካስቲንግ ተጋብዤ ተሳታፊ ነበርኩኝ። ካስቲንግ ከመሄዴ በፊት ለብሼው የምሄደውን መምረጥ ፈልግኩኝ። ጉትቻው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ተገዝቷል። ልብስ ግን ከምገዛ በቤት ውስጥ ባለው ልጠቀም ብዬ የቤቱ ሁሉ ልብስ ወጣ። መዘነጥ ዋናው ሆቢዬ ነው ከምል መደበኛ ተግባሬ ነው ከልጅነት እስከ እውቀት። እርግጥ ነው ፎቶው ከአንገት በላይ ነበር - ገጽ ብቻ ነበር የሚፈለገው። ነገር ግን ከወገብ በላይ ያለው የፊትን ገጽ የማድመቅ ድርሻ የሚኖረው ልብስ አስፈልጎኝ ነበር። የቤቱ ሁሉ ልብስ ተዘርግፎ ተሞከረ፤ ሁሉም ሊያደምቀኝ አልቻለም። መጨረሻ ላይ ቲ ሸርት ነበርኝ የኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ያን አውጥቼ ስለብሰው ምኑን እነግራችሁዋለሁኝ ቦግ አደረገኝ። በቃ ደስ አለኝ። የሚገረመው ክረምት ላያ ስለነበር ስሄድ ደረብረብ ያለ የሚመጥን አለባባስ ነበረኝ። ስገባ ካስቲንግ ቲሙ ተመልክቶኛል።

ለውጥን ማስቀጠል በህግ የበላይነት እና በተጠያቂነት!

ምስል
ብልህነትን ከብልሆች ብቻ ሳይሆን ከሞኝዎችም መማር ይገባል። „ከቀረውም ብርና ወርቅ አንተ እና ወንድሞችህ ለማድረግ ደስ የሚያሰኛችሁን ነገር እንደ አምላከችሁ ፈቀድ አድርጉ።“ መጽሐፈ ዕዝራ ምዕራፍ ፯  ቁጥር ፲፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 23.90.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ የሰርክ ዕጣ ለቅሶ!ማን አብሶ? እንዴት አለችሁ አዱኛዎቼ። ደህና ናችሁ ወይ? አንድ ዜና ሰማሁኝ ዕውነት ከሆነ ወርቅ እርምጃ ነው። የጠ/ሚር አብይ አህመድ የስሜን አሜሪካ ጉዞ መሰረዝ ጉዳይ የልቤ የሚባልለት ነው።   በዚህ ስሌት የስሜን አሜሬካው የቀደመው ከሀምሌ 19 ጀምሮ የነበረው ጉዞም ተሰርዞ ቢሆን ለእኔ ምቾት የሚሰጠኝ ነበር። እኔ ተደሞዊ ነገር ነው ግጥሜ። ደመቅ ያለ ነገር አይወድልኝም። ብልጭልጩም እንዲሁ ...  ሌላው የሰኔ 16 የድጋፍ ስልፍም ወቅቱን ያልጠበቀ በፍርክርክ ትልም ዜጎቻችን ለመሰዋዕትን የቀለበ ነበር፤ ይህንንም ተቃውሜ ጽፌ ነበር። እንዲቀርም ተማጽኜ ነበር። በውስጡ ያልተደፈሩ ሽንቁር - ድፍርስ - የጎርፍ ክምሮች ነበሩቡት። ለአዲስ አባባ የበቀል ጥሪት ማከማቻም ነበር። ይሄው ድሃው ዋጋ እዬከፈለበት ነው። አስከፋዩ ደግሞ የቀናው፤ የተቃጠለው ወገን መሆኑ ነው የሚያቆስለው። ለዚህ ነው ወዮ አዲስ ስል የባጀሁት።  ሌላው ይህ አቀባባል ምንትሶ ቅብጥርሶም የሃይል አሰላለፉን መስመር ቀያሽ ስለነበር አስፈላጊ አልነበረም። ፍንትው ያለ መረጃ ይሰጥ ነበር።በዚህም ሆነ በዚያም፤ እንዲህም ሆነ እንዲያ መስዋዕት ከፋዩ ደሃው ነው። ሊሂቃኑ እማ ምን ሲነካቸው ነው። የሆነ ሆኖ ደስታን ቆጥቦ መያዝ ቀጣዩን ጉዞ የስኬት ዘውድ ይደፋለታል። ከመዋለ ንዋይ ይልቅ ደስታን በቅጡ ቆጥቡ መያዝ ከብዙ ነገር ይታደጋል ። ነፍስ ሆኖ ነፍስ ይ