ልጥፎች

ከጁን 13, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

እቴ ሆይ!

ምስል
        እቴ ሆይ!            ከሥርጉተ ሥላሴ  14.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።)                              „ሕዝቤ ሆይ ና ወደ ቤትህ ግባ።“                        (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፭ ቁጥር ፳) እቴ ሆይ! ሙሽሪት እሸት አማራችቱ      እቴ ሆይ! ቅዲስቲት ፍቅር ናፋቂቱ       እቴ ሆይ! ህብሪቱ የዕምነት እልፍኝቱ                   እቴ ሆይ! ፍቅርተ የማተብ ርቱ                     እቴ ሆይ! ቀዳሚት የመሆን ሊቂቱ                           እቴ ሆይ! ቅኒቱ የዘመን ፍቱኒቱ                          እቴ ሆይ! መቻል ነሽ የሥርዬት እትብቱ።                                 እቴ ሆይ! ድሪዬ ነፍቆት አራሽቱ                              እቴ ሆይ! መዲና ህቭር ፈታይቱ                       እቴ ሆይ! ምግባሯ ድምቀት አዳይቱ                        እቴ ሆይ! ሁሉዬ ትዝታ አብሪቱ            እቴ ሆይ! ግሎባል ሥልጡን እሜቴይቱ             እቴ ሆይ! ማንጠግቦሽ ትዝታን ሳይቱ   እቴ ሆይ! ምንገዶሽ ሥልጡን ዘማናይቱ!   ሥጦታ ለውቢት ለአዲስ አባባ ይሁንለኝ።  የኔዎቹ ኑሩልኝ። መሸቢያ ጊዜ።

የሐሴት ፋናዬ።

ምስል
   የሐሴት ፋናዬ።             ከሥርጉተ ሥላሴ 13.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)               „በዚያ ቀን እንዲህ ይሆናል ታላቅ መለከት ይነፋል።“                     (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፯ቁጥር ፲፫) ኑሪልኝ እናቴ የተስፋ መንበሬ ኑሪልኝ እማማ የነፍስ ዝማሬዬ፤ ኑሪልኝ ልዕልቴ የፍቅር ዝናዬ ኑሪልኝ ልዕልቴ ማዕረግ ሽልማቴ ኑሪልኝ ንግሥቴ የመኖር አድባሬ፤ ኑሪልኝ መሆኔ የሰው ሰውነቴ ኑሪልኝ ዕንቁዬ ሚስጢር ገበታዬ ኑሪልኝ ክብረቴ ፍቅር መስታውቴ ኑሪልኝ ኢትዮጵያ የሐሤት ፋናዬ! የኔዎቹ መሸቢያ ጊዜ። ኑሩልኝ።

ትውውቅ ተልግመኛው ፖለቲካ።

ምስል
       ልግመኛው ፖለቲካ።                                        ከሥርጉተ ሥላሴ 13.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)           „አቤቱ አንተ አምላኬ ነህ፤ ድንቅን ነገር የዱሮ ምክርን በታማኝነትና በእውነት አድርገሃልና ከፍ ከፍ አደርግህ አለሁ።                             ሥምህንም አመሰግንህ አለሁ።“ (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፭ ከቁጥር ፩ እስከ ፪) ልግመኛው ፖለቲካ ርህርህና፣ አርቆ ማሰብ አልፈጠረለትም። አልሰራለትም።  የኢትዮጵያው ፖለቲካ መልኩ ልግመኛ፤ ቁመናው ልግመኛ፤ አቋሙ ልግመኛ፤ መንፈሱ ልግመኛ፤ ውስጡ ልግመኛ፤ ቅርጹ ልግመኛ፤ ፎርሙ ልግመኛ። አንጀቱ ልግመኛ። ልቡ ልግመኛ። ኩላሊቱ ልግመኛ። ህሊናው ልግመኛ። ፊንጢጣው ልግመኛ። ጉበቱ ልግመኛ። ፊኛው ልግመኛ። ህሊናው ልግመኛ። ጭንቅላቱ ልግመኛ። አንደበቱ ልግመኛ። ልሳኑ ልግመኛ። ዓይኑ ልግመኛ። ጆሮው ልግመኛ። እጆቹ ልግመኞች፤ እግሮቹ ልግመኞች። ክናዱ ልግመኛ። ኳቴው ልግመኛ። እርምጃው ልግመኛ። ዕይታው ልግመኛ።  ተስፋው ልግመኛ። ምኞቱ ልግመኛ ግን ባለትልቅ ራዕይ ራዬኛ ። ይቻላል በልግም ተባዝቶ በልግም ውጤት ቀመር። ይሆናል በልግመት ተቦክቶ በልግመት ተጋግሮ ማባያውም በልግመት ተቁላልቶ በልግመት ፌርሜሎ ተጥዶ ትልቁን ራዕይን ያሳካል ሲባል በምንም ተባዝቶ ሟርተነን አውግቶ ከምሾ ተጋብቶ፤ ደመርን ቀጥሮ፤ ሳቅነን ፈርቶ፤ ፈገግታን አጣውሮ ደስታን አጨልሞ ተስፋን አስጨንቆ ጭንቅትን ደግሶ ተስፋ ቆራጭነትን ዲል አድርጎ ድሮ፤ አያሆንምን ኩሎ፤ አያቻልምን ግጥግጥ ጠርቶ አይነን በርግጫ ቅልቅል ነፍሱን አጥፍቶ „ትልቋ ኢትዮጵያን“ ያልማል። ቧልተኛ በሉት ልግመኛውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፈሊጥ። ልግመኛው ፖለ

"ሙያ በልብ"

ምስል
     „ሙያ በልብ“                                     ከሥርጉተ ሥላሴ 13.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።)          „እውቀትን ለማን ያሰተምረዋል? ወይስ ወሬ ማስተዋልን ለማን ይሰጣል? ወተትን ለተወ ወይስ ጡትን ለጣሉ ነውን?               ትእዛዝ በትእዛዝ፣ ትእዛዝ በትእዛዝ፣ ሥርዓት በሥርዓት፣ ሥርዓት በሥርዓት ጥቂት በዚህ ጥቂት በዚያ ነው።              በባዕድ አፍ በልዩም ልሳን ለዚህ ህዝብ ይናገራል፣ እርሱም ፣--- እረፍት ይህቺ ናት የደከመውን አሳርፉ ይህችም                                        ማረፊያ ናት አላቸው፤ እነርሱም ግን መስማትን እንቢ አሉ።“                                            (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፰ ቁጥር ፱ እሰከ ቁጥር ፲፪) እኔ እንደሚገባኝ እና እንደምረዳው ከሆነ ከእንግዲህ አማራ ከዬትኛውም የፖለቲካ ድርጅት፤ ከዬትኛውም የፖለቲካ ሊሂቅ፤ ከዬትኛውም ጋዜጠኛ፤ ከዬትኛውም አክቲቢስት፤ ከዬትኛውም ዘመን አመጣሽ የፖለቲካ ተንታኝ ጋር እስጣ ገባ የሚያስፈልገው አይመስለኝም። እርግጥ ነው በዚህ በአዲሱ የአብን መንፈስ የማይመቹትን እዬፈለፈሉ ጥንካሬን ለማትጋት ለማውጫነት ያለፉትን አምክንዮች በማንሳት ከውድቀት እንዲድን መታታር ግን የተገባ ይሆናል። የእኔም ጹሁፍ ዓላማ ይሄው ነው።  አዲሱ አብንም ከልብ ሆኖ ሊያዳምጠን ይገባል። ገና ከመፈጠሩ እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ተራራ ያሰኜኛል ካለ እራሱን አንድ አድርጎ ለመምራት ደግሞ ከተሳነው ጣፊያ ልመና መሄድ ራሱን ያሳጠዋል፤ የዛሬ ድምቀት ነገን ያከስማል። ስለምን? በፈለገ ቅብ ድርጅት ከእንግዲህ የጎንደር መሬት እንዲታረሥ አንሻም። ጎን