ልጥፎች

ከኦክቶበር 8, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አላዛሯ ኢትዮጵያ አምላክ አላት።

ምስል
የትውልዱ ብክነትን ለማስቆም ከቶ ለማን አቤት ይባል? „አቤቱ እስከ መቼ ፈጽመህ ትረሳኛለህ?“ መዝሙር ፲፪ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 08.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                                  ከቶ የአማኑኤል አባታችን ሥጦታው እንዴት ይዞች ኋ ዋል? እኔ ፈጣሪ በቃቸሁ አለን የሚል ዕምነት ነበረኝ። ግን የሆነ አልመሰለኝም። ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል የሚስፈልገው የአዕምሮ ላውንደሪ ነው ። የ50 ዓመት የሴራ ፖለቲካ ባህል አሁንም አለ እንዳለ። ይህን እንለውጣለን ብለው የተነሱት የለውጥ ሐዋርያት ትግላቸው ከራሱ ከሊሂቃኑ ህሊና ጋርም ጭምር ነው። በምን ኦሞ አጥበው ከአዲሱ የአሰተሳሰብ መንፈስ ጋር ሊያዋድዱት እንሚቻላቸው ብርታቱን ይስጣቸው። እነኝህ የበቀልን ዓውደ ለመደምሰስ የተነሱ አዲስ ቡቃያዎች ያን  የቆዬውን የታቆረ የሴራ የሽምቅ ውጊያ አስወግደው የእነሱን ንጹህ ድንግል አሰተሳስብ እንዴት ማዋለድ እንደሚችሉ ፈተናው ውሃ ያዘለ ተራራ ሆኖ እዬታዬ ነው። ራሱ የፖለቲካ ሊሂቃኑ ለመለወጥ ያላቸው ፈቃድ ምን ያህል ይሆን? ራሳቸውን ማሸነፍ ቢችሉ አባሎቻቸውን፤ ደጋፊዎቻቸውን በዚህ አዲስ  የአስተሳብ ባህል ለመቀረጽ እንዲህ አይችግርም ነው። የዬትኛውም የፖለተካ ድርጅት ይሁን ንቅናቄ ይሁን ግንባር መጀመሪያ ከራስ የመነሳትን ተጋድሎ መጀመር ያለበት ይመሰላል። ራስን ሳይለውጡ ተከታይን ሆነ አባልን መለወጥ ፈጽሞ የሚቻል አይመስልም። ለውጡ ወረቀት ላይ አይደለም። ለውጡ ከውስጥ መሆን አለበት። አንድ ሊሂቅ የዘመተበትን ሌላኛውን ሊሂቅ ራሱ ሄዶ ይቅርታ አድርግልኝ ካላለ አሁንም ቦክሱ ቀጣይ ነው የሚሆነው። ተጎጆው ደግሞ ሰላም የመናፈቀው ህዝብ ነው። አሁንም እንደ ትናንቱ መካሰስ ስሞታ