ልጥፎች

ከጁላይ 3, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የመንግሥት ኃይሎች በአማራ ክልል የጤና ተቋማት እና ባለሙያዎች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል፡ሂዩማን ራይትስ ዋች

ምስል
  "የመንግሥት ኃይሎች በአማራ ክልል የጤና ተቋማት እና ባለሙያዎች ላይ ጥቃት ፈጽመ ዋል፡ሂዩማን ራይትስ ዋች" የፎቶው ባለመብት, Amhara Health Bureau ከ 8 ሰአት በፊት የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሎች በአማራ ክልል ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ መጠነ ሰፊ ጥቃቶችን በጤና ባለሙያዎች፣ በህሙማን እና በጤና ተቋማት ላይ ፈጽመዋል ሲል የመብት ተሟጋቹ ሂማን ራይትስ ዋች ከሰሰ።   https://www.bbc.com/amharic/articles/c97832pz01mo "የመንግሥት ኃይሎች በአማራ ክልል የጤና ተቋማት እና ባለሙያዎች ላይ ጥቃት ፈጽመዋል፡ሂዩማን ራይትስ ዋች ታማሚ እና አስታማሚ"   የፎቶው ባለመብት, Amhara Health Bureau ከ 8 ሰአት በፊት   "የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይሎች በአማራ ክልል ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ መጠነ ሰፊ ጥቃቶችን በጤና ባለሙያዎች፣ በህሙማን እና በጤና ተቋማት ላይ ፈጽመዋል ሲል የመብት ተሟጋቹ ሂማን ራይትስ ዋች ከሰሰ።   አንድ ዓመት ሊሞላው በተቃረበው በአማራ ክልል በፌደራሉ መንግሥት ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል እየተካሄደ ባለው ግጭት፣ የመንግሥቱ ኃይሎች እና ተባባሪ ሚሊሻዎች በክልሉ የጤና ተቋማት ላይ ፈጽመዋቸዋል ያላቸውን ጥቃቶች በተመለከተ ሂዩማን ራይትስ ዋች ዝርዝር ሪፖርት አውጥቷል።   ሪፖርቱ በክልሉ ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ካለፈው ዓመት ማብቂያ አንስቶ የመንግሥት ኃይሎች ቢያንስ 13 በሚደርሱ ከተሞች በጤና ተቋማት እና በሠራተኞች እንዲሁም በትራንስፖርት አገልግሎቶች ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን የሚያመለክቱ መረጃዎችን ማሰባሰቡን አመልክቷል።   የሂማን ራይትስ ዋች የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ላቲሺያ ባድር “የኢትዮጵያ ፌደራል ኃይሎች ለሰላማዊ ሰዎች ሕይወት

የሰባዕዊነት #ሐዋርያዊት ቅድስት አገር #ሲዊዘርላንድ።

ምስል
  የሰባዕዊነት #ሐዋርያዊት ቅድስት አገር #ሲዊዘርላንድ ።   "አድርገኽልኛል እና አመሰግንኃለሁ። "       እንደ አገር አስተዋይ አገር ብርክታዊቷ ሲዊዘርላንድ። እንደ ሕዝብም አስተዋይ ህዝብ ሲዊዛውያን። በብዙ አጋጣሚወች ብዙ ሲዊዛውያንን አግኝቻለሁ፤ የማድመጥ አቅማቸው፤ ልታይ ልታይ አለማለታቸው፤ ለሰው ልጅ ያላቸው ጥልቅ ፍቅር እና አክብሮት፤ ለመርዳት ያላቸው ፍጥነት፤ ለውሳኔ ቁጥብነታቸው ይገርማል። ይደንቃል። ያስተምራል።    አንዱ ወይንም አንዷ ሲዊዛዊት በራሳቸው የትምህርት ተቋማት ናቸው። እንደ እኔ ሲዊዞች በተፈጥሯቸው ፖዘቲብ ቲንከር ናቸው። ካቀረቡ ከውስጣቸው፤ ሲለዩም በነበረው የፍቅር ደረጃን ሳያጓድሉ፤ ሳያስተጓጉሉ ነው። ሁልጊዜ በሚገጥሙኝ ዕድሎች ሁሉ ተምሬባቸዋለሁ። ልዩ ናቸው እና።    መፃህፍት ሦስቱን በአንድ ላይ አሳተምኩኝ። ቤቴ አራተኛ ፎቅ ላይ ነው። መፃህፍቶችን በእሷ መኪና ጭነን አምጥተን ተሸክመን አመላልሰን ቤት አስገባነው። ጓደኛዬ ሲዊዛዊ የህክምና ዶር ናት። ይህ ትህትና፤ ይህ ታዛዥነት ለአንዲት ስደተኛ #ማንም ፤ #ምንም ለሌላት ባተሌ። ከጨረስን በኋላ ምን ነክቶን ነው ግን አጋዥ ሰው እኮ መቅጠር እንችል ነበር አለች እና ጅልነታችን ያስቃል አለች። ሌላ ጊዜ ደግሞ የገዛሁት እና የመጣልኝ ዕቃ ትክክል አልሆን አለ። ክርክሩ በሙያ እንዲታገዝ አማካሪዬ ከቦታው ድረስ አብረውኝ ሄደው ከእኔ ጋር ሞገቱል። ሌላም ሌላም ነገር ማንሳት እችላለሁ። የትም ሄጄ #ተከፍቼ እምመጣበት ሁኔታ የለም።    ጭምት - ቅን፤ ሰባዕዊ - ተፈጥሯዊ፤ አጽናኝ - ደግ፤ ሥልጡን - ሩህሩህ፤ ትጉህ - ታጋሽ፤ ድንቅ - ውብ፤ ፈርኃ እግዚአብሄር የሰከነባት፤ ዲሞክራሲ በሚዳሰስ በሚጨበጥ መልኩ #ዕውን የሆነባት ልዩ፤ ፍፁም ልዩ አገር ሲ

እንኳን ደስ አለሽ ቅድስቴ ሲዊዚሻ።

ምስል
  እንኳን ደስ አለሽ ቅድስቴ ሲዊዚሻ። የሲዊዝ ድንቆች በውብ ትዕይንት በበርሊን ስታዲዮ #ኢጣሊያንን 2 - ለ0 በሆነ ውጤት ለቀጣይ ዙር ጨዋታ የመጀመሪያው ቲም ሆነዋል። ጨዋታቸው እጅግ ውብ፤ የተረጋጋ፤ ሥርዓት የነበረው ነበር። የሲዊዝ ቲም በአጨራረስ ላይ በነበረ ግድፈትብዙ #የግብ ዕድል አምልጧቸው ነው እንጂ ቢያንስ 4ቷን የማምጣት ዕድል ነበራቸው። ዛሬ ሲዊዞች ምንም ዓይነት ቢጫም፤ ማስጠንቀቂያም አልገጠማቸውም። በፍፁም የተረጋጋ መንፈስ ነበር የተጫወቱት። ጣሊያኖች #በሦስት ቢጫ #ዜሯቸውን ይዘው ይጓዛሉ። የጣሊያን ቡድን እጅግ ጠንካራ የነበረ ሲሆን ጉልበታቸው አሁንም አለ። ቢሆንም ግን ጉልበታቸው ለቀጣይ ጨዋታ አላሳለፋቸውም። እስከ 25 ደቂቃ ድረስ እንደ ኤክስፐርቶች አገላለጽ 65/% በሲዊዝ ቲም ቁጥጥር ሥር ነበረች እሜቴ ድንቡልቡል። ከረፍት በፊት የሲዊዘርላንድ ቲም በአንድ ግብ ለእረፍት ሲወጣ፤ ከረፍት መልስ በሰከንዶች ልዩነት ሁለተኛዋን ደገሙ እና የጣሊያን ቡድን ተስፋ ደመና አለበሱት። የዕለቱ ዳኛ ፍፁም የተረጋጉ ስለነበረ ለዲስፕሊን ጨዋታ ምቹ ነበሩ። ከእረፍት መልስ እሜቴ ድንቡልቡል 65% በሲዊዝ ቲም ሥር ነበረች። ዕውነት ለመናገር ጎል ጠባቂ ሶመር ብዙም ሥራ አልነበረበትም ማለት ይቻላል። የጣሊያን ቲም አመዛኙ ጊዜው በመከላከል፤ የሲዊዝ ቲም በማጥቃት እና በመከላከል ጥምር ቅልጥፍና ድፍረትም ታክሎበት በጥሩ ጨዋታ ለውጤት በቅቷል። የሲዊዝ የዕለቱ አሰላለፍ 3.4.3 ነበር ከጀርመን ጋር በነበረው ግጥሚያ አሰላለፋ የተለዬ ነበረ። ጀርመንን ሙሉ 90 ደቂቃ አንድ ለምንም የመራው የሲዊዝ ቲም በተጨማሪ ጊዜ ነበር ጀርመን አንድ ግብ በማስቆጠር ከምድቡ የመሪነቱን ቦታ ሳያስነካ ያጠናቀቀው። በዛ ጨዋታም የቅድስት አገር ሲዊዝ ቲም የጨዋታ ብልጫ ነበረ

ኧረ።

  ኧረ። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" እንዴት ሰነበታችሁ? እባካችሁ ለፖለቲካ መሪወች፤ ለተፅዕኖ ፈጣሪወች፦ ብላችሁ ማህበራዊ ኑሯችሁን አታውኩ። የውስጥ ሰላማችሁንም አትቀናቀኑ። # አናውቃቸውም።  መደገፍ መብት ነው፤ መሞገትም። ግን እነሱን አምናችሁ እና ተማምናችሁ ከጽኑ ወዳጃችሁ ጋር አትለያዩ። ትናንት ከብክበን መስክረንም ሌት ተቀን ተግተን መንበር ላይ ያወጣናቸው ዛሬ ኢትዮጵያን እስከመቀናቀን ደርሰዋል።  ማህፀንን እንደ ዱባ የሚቀረድድ መራር ሸክም። የሞግትናቸውንም // ከደገፍናቸው ጋር ስናነፃጽረው ግብረ መልሱ ከራሳችን ውጪ በፍፁም ልባችን ማንንም ማመን ምን ያህል ውስጥን እንደሚያቆስል እያዬሁ ነው።  ኧረ! ለሁላችን አምላካችን // አላሃችን ልብ ይስጠን። አሜን። ውዶቻችንም በማያዘልቅ አመክንዮ ብለን አንጣ። በተለይ የውስጥ ሰላማችን ለሌላ ሰብዕ ብለን አንጣ። #አንተዋወቅም ። እኛ ላዩን እነሱ ውስጡ ለውስጥ ሲጓጓዙ ነው የኖሩት።  ሥርጉትሻ024/07/02

ትዝብት።

  ትዝብት ።  "የቤትህ ቅናት በላኝ ።" አንድ ግንኙነት ዲስፒሊን ሊኖረው ይገባል። አንድ ተቋምም ዲስፕሊን ሊኖረው ይገባል። እንኳንስ የፖለቲካ ድርጅት። እኔ ዛሬ ጓዶቼን ባገኝ፤ ለዓይነ ሥጋ ቢያበቃኝ እንደምን ሐሤት ባገኜሁ። ቃል ኪዳኑ ሰው ሠራሽ አይደለም እና። በወል፤ በጋራ የተከወኑ ተግባራት ለጎርፍ ሲሸለሙ ስመለከት ገረመኝ። ታማኝነት፤ ኪዳን፤ ውል፤ ቃል በኢትዮጵያ የፖለቲካ፤ የማህበራዊ ኑሮ መና ወና ሆኑ።  በዚህ ውስጥ መሪነትን እሰቡት። ልሙጥ አልሆነባችሁም። የሚቀር ነገር የለም። የተዋጠ ቅቤ አይቀርም። ከምንጊዜም በላይ ክውን ብዬ በራሴ ራዕይ እና ግብ መትጋቴ የእኔ ሳይሆን የላይኛው እርዳታ መሆኑን ተገነዘብኩኝ። ተከርክሞ ክውን ብሎ ገድሞ መኖር በቢሊዮን ዶላር የማይገኝ ሥጦታ ሆኖ አገኜሁት።  ሰው ከሰው ጋር ሲኖር፤ ሲሰራ፤ ሲወዳጅ እኮ ብዙ በጣም ብዙ ነገር ሊታወቅ ይችላል። ያን ጊዜ ጠብቆ የጥቃት ሚሳኤል ማድረግ ነውር ነው። #መጠበቅ //መጠበቅ እንደምን ያቅት። "አቤቱ ለአንደቤቴ ጠባቂ አዘጋጅ።" አሁን ሚዲያ ላይ የሚገኝ ህዝብ እኮ ገብያ ማለት ነው። ይፈታል። እና የተቋምን ቃልኪዳን ማፍሰስ? ሥርጉ2024/07/02

ደራሲ ባለቅኔና ዲፕሎማቱ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ

ምስል
  ደራሲ ባለቅኔና ዲፕሎማቱ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ     በኢትዮጵያ ሥነ ጽሑፍ ታሪክ ታላቅና ግዙፍ አስተዋጽኦ ያላቸው ደራሲ፤ታሪክ አዋቂ፤የታወቁ ዲፕሎማት፤በቤተ ክህነት ትምህርትና በቋንቋ የተካኑ፤ ባለቅኔ፤ገጣሚ፤የዘመናቸውን ዕውቀት የቀሰሙ ምሁር፤ በአኗኗራቸው በምሳሌነት የሚታዩና ሠርተው የማይደክሙ ኢትዮጵያዊ ናቸው ፡፡እኒህ ሊቅ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ ይባላሉ፡፡ ከአባታቸው ከአቶ ወልደ ሥላሴና ከእናታቸው ወይዘሮ ወለተ ማርያም ዜና የተወለዱት ግንቦት 1 ቀን 1871 ዓ ም በቀድሞ አጠራሩ በመርሐ ቤቴ አውራጃ በታች ቤት ወረዳ ረመሸት ቀበሌ ደን አቦ ገዳም በተባለ ሥፍራ ሲሆን ያረፉት ደግሞ መስከረም 9 ቀን 1931 ዓ ም እንግሊዝ አገር ባዝ በተባለው ቦታ በስደት ላይ እያሉ ነው:: ብላቴን ጌታ ኅሩይ ለቤተ ሰቦቻቸው የመጀመሪያ ልጅ ሲሆኑ አባትና እናታቸው ከእርሳቸው ቀጥሎ በተከታታይ ሁለት ሴት ልጆችን ወልደዋል። እንጦጦ ራጉኤል ደብር መጥተው የመጻሕፍትን ትርጓሜ በዘመኑ ከነበሩት የደብሩ ሊቃውንት ዘንድ ተምረዋል። ብላቴን ጌታ ኅሩይ በትዳር ሕይወታቸውም መልካም አርዓያ ስለነበሩ ከባለቤታቸው ወይዘሮ ሐመረ እሸቴ ስድስት ልጆን ወልደዋል፡፡በርካታ የልጅ ልጆችንም አፍርተዋል፡፡ቤተሰባቸውንም በእግዚአብሔር ሕግ መሠረት በፍቅር ይመሩና ያስተዳድሩ ነበር፡፡በድርሰት ረገድ ከ21 በላይ የተደነቁ መጻሕፍትን ደርሰዋል፡፡ሥራዎቻቸው ሁሉ ትሕትናን፤ትክክለኛነትን፤ምግባረ ሠናይነትንና ሞራልን ከፍ አድርገው የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ከጻፉዋቸው መጻሕፍት ውስጥ ኢትዮጵያና መተማ የዓፄ ዮሐንስ ታሪክ ባጭሩ፤ ወዳጄ ልቤ ፤ ዳግማዊ ቴዎድሮስ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ፤ የልዕልት ወይዘሮ መነን መንገድ በኢሩሳሌምና በምስር፤ መጽሐፈ ቅኔ፤ ዋዜማ፤ በኢትዮጵ