ልጥፎች

ከዲሴምበር 28, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያዊነት ምንጩና አገነባቡ ከሃሳብ በላይ ነው።

ምስል
ጥፈተኛው ማን ነው? „ከቀና ህግ ወጥተን ሳትን“ መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                                                               መንፈስ! እንዴት ናችሁ የኔዎቹ? ደህና ናችሁ ወይ ? በዛ ሰሞን በአንድ የግል ቪዲዮ እስራኤል አገር አባቶች መደብደባቸውን አዳመጥን አዬንም፤ አሁን ደግሞ ኢትዮጵያ ሻሸመኔ ተመሳሳይ ነገር መፈጸሙን አዬን። የቆዬ ስለመሆኑ አይደለም ጉዳዩ። ጉዟችን ወደዬት ነው? ቀደም ባሉ ጊዜያት ላይ በመ ዶሻ ተቀጥቅጠው ያለፉ ወገኖች አሉን፤ ተገድሎ ተዘቅዝቆ የተሰቀለ ወገንም አለን። መፈናቀሉ፤ መደፈሩ፤ መተዛዘን መመ ከኑም አለ። አጀንዳችንም አይደለም ከሚዲያ ማሟቂያ ባለፈ፤ ሰከን ያለ ተግባር የቸርነት አንበሉ ዮሴፍ ገብሬ ከፈጸመው ውጭ። ያለፈውን ዓመት ትንሳኤን አብሮ ነው ያሳለፈው። ·        ው ጊ ያ ? ይህ የመንፈስ የነፍስ ውጊያ መንስኤው ምንድን ነው? ምን ተማርንበት? ምን አቀድንበት? ምን አጨንበት? ምን አሰብንበት? ምን አስተረቀንበት፤ ምንስ ል ንታረ ቅ አሰብንበት ይህ ነው የዛሬ ጉዳዬ። ·        ምን አሰብ ንበት ስለ ውድቀታችን። ወድቀ ና ል። ወድቀናል ሁላ ች ንም። ስለምን? ትውልዳዊ ድርሻችን ለመወጣት አቅም ስሌለን - የመንፈስ ብርታት መቀኗችን ፈሰስ ስለሚል። በ2008 እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር የጸጋዬ ድህረ ገጽን ስጀምር ዋናው ሞቶዬ „ትውልዳዊ ድርሻችን በህብረት እና በ አንድ ነት እንወጣ“ ይል ነበር። ሁለተኛው አጋዥ ሞቶዬ እንደ ቅመም „እልፍ ነን እና እልፍነ ታችን እልፍ እንድርገው“ ይል ነበር።  ለዚህም ለመጀመሪያ