ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 8, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያን #መዳፈር አይገባም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን #ማጣጣል እና #መናቅ፤ ባለፈም #መታገልም አይገባም።

ምስል
  ኢትዮጵያን #መዳፈር አይገባም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን #ማጣጣል እና #መናቅ ፤ ባለፈም #መታገልም አይገባም።   "አቤቱ ንጹህ ልብፍጠርልኝ።" አሜን።     ጤና ይስጥልኝ እንዴት አደራችሁ ቤተ - ሥርጉትሻ ቅኖቼ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ከዩንቨርስ ጋር ያላት የዕውቀት ደረጃ #የሰመረ ነው። ሳይንስ በደረሰበት ዘመን አይደለም ሳይንቲስቷ ኢትዮጵያ ሳይንቲስት የሆነችው። ፈላስፊት ኢትዮጵያ ፈላስፋ የሆነችው ሳይንስ የዕውቀት ዘርፍ ሆኖ ግሎባሉ ዓለም በተቀበለበት ዘመንም አይደለም። ዩንቨርሷ ኢትዮጵያ ዩንቨርስን የቀመረችበን መክሊቷ የምዕት ነው። ኢትዮጵያ ጀማሪ አስትሮኖመር አይደለችም። #የፊደል ገበታ እንጂ። የእሷነት ሚስጢሯ ማህለቅ ደግሞ #ግዕዝ ቋንቋ ነው። ግዕዝ ቋንቋ ብቸኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅብዓዋ ነው። የተሰጠችው ከእዮር ነው።   ኢትዮጵያ ዊዝደሟ ከምድር እስከ እዮር የዘለቀ መሆኑ እኛ በደረስንበት ዘመን እንሆ #ገሃድ እየወጣ ነው። ከስድስት ዓመት በፊት ብላቴናዋ ዶር ሮዳስ ጽፈው፤ ተንብየው፤ ተፈላስፈውበት የነበረው የፋክት እንክብል እንሆ ዕውን ሆነ። ሊቅነት በታምራት፤ ዕውነት በትንግርት ኢትዮጵያ #ልኳን ስታገኝ እንዲህ ነው።    ሊቀ - ሊቃውንቱ ዶር ሮዳስ ከእግዚአብሄር በታች እራሳቸውን ይጠብቁ ዘንድ በትህትና ላሳስባቸው እወዳለሁኝ። ጥንቃቄ ያተርፋል እንጂ አያከስርም። ሚስጢር እንዳይፈስ በአጓጉል ሁኔታ ጥንቃቄ አጀንዳወት ቢሆን ምኞቴ ነው።   ዓለማችንን በዩንቨርስ ዕውቀት የሚተረጉሙ ኢትዮጵያ ከተፈጠረች በኋላስንት ሺህ ዘመናት በኋላ የተቋቋሙት የአስትሮኖመር የምርምር ተቋማት እንኳን የኢትዮጵያን የህሊና የሥልጣኔ ደረጃ ሊመክት ወይንም ሊለካካ ...

የአጤ አባይ #ዳግም ልደት እና የኢትዮጵያ #የፖለቲካ እስረኞች።

  የአጤ አባይ #ዳግም ልደት እና የኢትዮጵያ #የፖለቲካ እስረኞች።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   እኔ በኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ በኢትዮጵያ ቴሌኮም፤ በኢትዮጵያ ሠራዊት፤ በኢትዮጵያ አባይ ግድብ ኢትዮጵያን በጥልቀት በሚወክሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ተቋማትን በሚመለከት የየዘመኑን ገዢወች በምሞግትበት ሁነት ፈጽሞ አላያቸውም። እራሳቸው ትውልድ ስለሆኑ። በጣም እጅግ #ቁጥብ ነኝ። በሙግት ፈጽሞ አልነካካቸውም። ይልቁንም ዝምታየን በማስተዋል እመግባቸዋለሁኝ። #እስቲ ዛሬ ………    #አያድርግብኝ እንጂ እኔ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ብሆን ኖሮ፥ ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞችን ይዤ የአባይ ግድብን ዳግም #ልደትን እንዲዩ አደርግ ነበር። ይህ አዲስ ክስተት ለሌላ ንጹህ ግሎባል ፖለቲካ ሁነት ጋር ልዩ ቀረቤታ ሊኖረው ስለሚችል፤ አዲስ ጎዳና ይጠርግ ነበር። የዓለምም አዲስ #አጀንዳ ይሆን ነበር። ለግሎባሉ የሰብዓዊ መብት አስጠባቂ ተቋማትም ፈር ቀዳጅ የፊደል ገበታ በሆነ ነበር። የኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኞች የመናገር፤ የመፃፍ፤ የማሰብ፤ የመራመር፤ ሃሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ መብታቸው ላይ የኢትዮጵያ ህገ - መንግሥት ፈቅድነውም አልፈቀድነውም፤ በሚፈቅደው ድንጋጌ ልክ ሊሆን ይገባል። የሚዲያ ሠራተኞች፤ ጸሐፊወች ሞጋቾችን እና የኢትዮጵያ መንግሥትን የሚያገናኘው ድልድይ የኢትዮጵያ ህገ - መንግሥት ርካብ ብቻ ነው።   የሆነ ሆኖ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ በድንገቴ ተውኔት የተዋጣላቸው ናቸው እና የፖለቲካ እስረኞችን ከአጤ አባይ ከሆደ ሰፊው፤ ከታጋሹ ጋር ፊት ለፊት ካአገናኙ በኋላ፤ ከእንግዲህ የፈለጋችሁ አብረን እንመለስ፤ የፈለጋችሁ ከዛሬ ጀምሮ መንግሥታችን ከቤተሰቦቻችሁ ጋር ትቀላቀሉ ዘን...

ፍቅር እና አስተዳደጓ። "ሰፊነት" በትክክል ይገልፃታል።

ምስል
  ፍቅር እና አስተዳደጓ። "ሰፊነት" በትክክል ይገልፃታል።   "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄርም፤ አካሄዱን ያቃናለታል።"  (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱)         ምዕራፍ ፲፮።   ዕለቱን ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ተያያዥ ሃሳቦችን አነሳለሁኝ። የወጀቡ ማየል ጎንደር የቆረጠ ውሳኔ ከወሰነች መልካም ስለማይሆን። ጎንደርን ነጥሎ መጓዝ ለአማራዊ ፖለቲካም አይበጅም። ለኢትዮጵያዊነትም ጠቃሚ አይደለም። የጎንደር ጽኑ መንፈስ ተገሎ የትም አይደረሰም። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሊቃናት ውስጥ በአብዛኞቹ ጎንደርየ ስሩዝ እንደሆነች አውቃለሁኝ። ምንም አትፈይድም ከሆነ ነገርየው አይጠቅምም። አቅም መሰብሰብ እንጂ መበተን #ብልህነት ስላልሆነ።    ይህን እምናገረው ስለ ጎንደሪና ምክንያት እየተፈለገ መጨፍጨፋ ሊያባራ አልቻለምና። በቅንነት መተቸት ቢገባም፤ በበቀል ተነሳስቶ መምተር ግን የተገባ አይደለም። ለኢትዮጵያ ሆነ ለአማራ ጎንደሮች አስፈላጊ ቅመሞች ነን። ጉዞው ጣዕም እንዲኖረው ከታጨ እኛን አግልሎ ከሆነ??? #ጠብቁት ።   #መነሻ ።   የአርቲስት ወ/ሮ ፍቅር አዲስ ነቃ ጥበብ ወላጅ እናቷ የለስላሳው ማሩ ቀመስ ደንቢያ ተወላጅ እንደሆኑ በልጅነት እሰማ ነበር። በአካል አላውቃቸውም። ሁለተኛዋ ለጋስ እና ደግ እናቷን ነው እኔ እማውቀው። ወላጅ አባቷ አባ ነቃጥበብ ግን #የቤተክርስትያን ዕውቀትም ያላቸው፤ ጭምት ሰው ነበሩ። በሙሉ ይሁን በከፊል በእኛ ዘመን ትርጉም ሰጪ ስላልነበረ "ከየት መጣ" የሚለው ነጣይ ቋንቋ ጠንቅቄ መናገር ባልችልም አባ ነቃጥበብ ጎጃሜ እንደሆኑ እስማ ነበር። ይህም ከቤተክርስትያን ጸጋቸው ጋር በተያያዘ ነበር አማዳምጠው።    የጎን...