#ውስጥነት።
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
የሰውነት መለኬያ የውስጥነት #ንጽህና ይመስለኛል። ይመስለኛል እኔ አዘወትራለሁኝ።
የሰውነት መለኬያ የውስጥነት #ንጽህና ይመስለኛል። ይመስለኛል እኔ አዘወትራለሁኝ።
ምክንያቴ #ጥናታዊ ተግባር ስላልከወንኩበት ነው።
ወደ ቀደመው ስመለስ ለመኖር፤ መኖርን ለማስቀጠል ውስጥን በተፈጠረው ልክ #በንጽህናው ማስቀጠል ነው።
ንጽህና ደግሞ ከራስ እንጂ #ከደጅ አይጀምርም።
እያንዳንዳችን የቅድሚያ ተግባራችን ሊሆን የሚገባው በብዙ ድሪቶ የታጀለውን የውስጥ ቆሻሻ ለማጽዳት #መቁረጥ፤ #መወሰን፤ ውሳኔውን ደቂቃ ሳያጠፋ ወደ ድርጊት ማሸጋገር ይገባል።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን። ኑሩልኝ። አሜን።
ሥርጉትሻ 2025/08/26
#አጤ ዘመን እና #አጤ ሂደት እንደምን ባጃችሁ?
"አቤቱ ንጡህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
አጤ ዘመን ወይንስ አጤ ሂደት ማን ይሆን #ቀዳሚው? ማን ይሆንስ? #መሪው? እኛስ በአጤ ዘመን እና በአጤ ሂደት ተፈጥሯዊ ክንውን #ሾለክን ወይንስ ልካችን በሚፈቅደው ልክ አብረን #ተጓዝን? ፈተናው ይኽው ነው።
"አቤቱ ንጡህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
አጤ ዘመን ወይንስ አጤ ሂደት ማን ይሆን #ቀዳሚው? ማን ይሆንስ? #መሪው? እኛስ በአጤ ዘመን እና በአጤ ሂደት ተፈጥሯዊ ክንውን #ሾለክን ወይንስ ልካችን በሚፈቅደው ልክ አብረን #ተጓዝን? ፈተናው ይኽው ነው።
ሌላውን
#መተቸት #ቁልቁለት ነው። ኧረ ከቁልቁለትም የተሻለ ሞዞቦልድ አልጋ ነው። እኛን ሌላው ሲተቸን ደግሞ #ዳጥ እና #ምጥ ነው። ለምን? ሰውነት ግድፈትም ጸጋው ነው ብየ እኔ በግሌ እቀበለዋለሁኝ።
#መተቸት #ቁልቁለት ነው። ኧረ ከቁልቁለትም የተሻለ ሞዞቦልድ አልጋ ነው። እኛን ሌላው ሲተቸን ደግሞ #ዳጥ እና #ምጥ ነው። ለምን? ሰውነት ግድፈትም ጸጋው ነው ብየ እኔ በግሌ እቀበለዋለሁኝ።
መግደፍ እንዳሻህ ብለን ባንወስንለት
እንኳን ሊሆን የሚችል፤ የሚጠበቅ መሆኑን ልንቀበለው ይገባል ባይ ነኝ - እኔው ሥርጉትሻ። እኛ #ሰወች ነን። ልንሳሳት መቻላችን የተፈጥሯችን ልጥፍ ወይንም ደባል ሳይሆን #ውህድ ነው።
እንደ ፕላዝማ ማለት ነው።
ግን በተመሳሳይ ግድፈት በመመላለስ መዳከር ለእኔ #መታመም ነው።
ይህን ነው ወደን እና ፈቅደን ማረም ያለብን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉትሻ 2025/08/26
ይህ በፈጣሪያችን፤ በአላሃችን እጅ ያለ የቃሉ የትርጉም ዕለታዊ ክንውን ነው።
ዕውነት ይሸምግለው።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉትሻ 2025/08/26

#ሽሽት ለምን?
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
የሚከፋው፤ የከፋውም ከተፈጥሮ፤ ከሰዋዊነት #ሽሽት ነው።
ለምን? በልኩ፤ ስለልኩ፤ ለልኩ መሆን ስለሚሳነን?
#መሳን በእጅ በሌለ ነገር ቢሆን - በሆነ፤ ግን ነገር ግን እኛ በምንችለው ነገር ለምን በራስ ተፈጥሯዊ #አቅም ላይ #ሽሽትን እንፈቅዳለን? ሰው ሆኖ ስለ ሰው ልጅ #ደህንነት በቅንነት ማሰብ፤ ማሰላሰል እንዴት ያቅታል?
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉትሻ 2025/08/26
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ