ልጥፎች

ከፌብሩወሪ 1, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

"ሉዕላዊ አገር እንጂ ሉዕላዊ ክልል የለም።" ጠ/ሚር አብይ አህመድ ከተናገሩት ...

ምስል
   እንኳን ደህና መጡልኝ።  „ሉዕላዊ አገር እንጂ ሉዕላዊ  ክልል የለም። እንደ አፈዎ  ያድርግልን ይሁንልን እስኪ …   „ ጋሜል። አንዳልወጣ በዙሪያ ቅጥር ሠራብኝ። ሰንሰለቴንም አከበደ።“ ሰቆቃው ኤርመያስ ፫ ቁጥር ፯ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  01.02.2019 ከእመ ዝምታ ኪሲዊዝሻ።   „ሉዕላዊ አገር እንጂ ሉዑላዊ ክልል የለም“ ይህ ከዛሬው ከጠ/ሚር አብይ አህመድ መልስ የተወሰደ ነው።   ·        እንደ እኔ ዕይታ እና ተደሞ ልሄድበት ወደድኩኝ። እንዲህ …   ይህ የሆነበት መሰረታዊ ጉዳይ አለ። ይህ መሰረታዊ ጉዳይ ትግራይ እንደ ሉዑላዊት አገርነት ነው 27 ዓመት የቆዬችው። ቀደም ባለው ጊዜ እኔ ስጽፍ ተጋድሎው ኢትዮጵያዊነት እና ትግራዊነት ነው እል ነበር።   በጣም ለረጅም ጊዜ ስጽፍ ተጋድሎውን ስምለከተው የነበረው ትግራዊነት ኢትዮጵያዊነት ተክቶ ለመውጣት ስለመሆኑ ነበር የሚረዳኝ። ነውም ። ሂደቱም ሁኔታው የነበረው ኢትዮጵያ ትታይ የነበረው እንደጠላት አገር ነው ። ቅኝ እንደተገዛች አገር።   የህወሃት ማንፌስቶ ጸረ ኢትዮጵያ ነው ልክ እንደ ኦነጉ። ኦነግ ሥልጣኑን ቢያገኝም ከቻለ በዚህ መልክ ህወሃት 27 ዓመት በነበረበት ልክ ካልቻለ ደግሞ የራሱን አገር መፍጠር ነው። ህልሙም ዕውነቱም ይኸው ነው። መንትዮሹ መንገዳቸው ይኸው ነው።   ባዶ ቤት አግኝተው ጊዜያዊ ጋብቻ የፈጸሙትም በዛ መልክ ነበር። አጅሬው ወያኔ ለቀን ያደረሰውን ሻብያንም፤ ሽፋን ሰጪውንም ኦነግንም በጊዜ ሸኝቶ በለሱን በበለስ አጣፍጦ ተኮፈሰበት እንጂ።     ወደ ቀደመው ምልሰት ሳደርግ ይህን ያክል ጊዜ ቀርቶ ህወሃት ከዚህ ደረጃ እደርሳለሁ

"ከችግር ማትረፍ" ከልቤ የገባ አገላለጽ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  „ከችግር ማትረፍ“ „ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሳ ነው፤ ርህራኄው አያልቅምና።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ፫ ቁጥር ፳፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  01.02.2019 ከእመ ዝምታ ኪሲዊዝሻ።   ቅኖቹ አዱኛዎቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ ወይ? ዛሬ የኢትዮጵያ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠ/ሚር አብይ አህመድ ላቀረቡት ጥያቄ መልስ ሲሰጥ አዳመጥኩኝ። በዚህ ዙሪያ በቻልኩት መጠን ነጠል አድርጌ የማያቸው ቁም ነገሮች ይኖሩኛል። እርዕሱን ሐረግ አጥቼለት የነበረው ያስቸገረኝ አመክንዮ ስለነበር በዚህ አጋጣሚ ስላገኘሁ ደስ እያለኝ መንበሩ ላይ ጉብ አድርጌዋለሁኝ። አገላለጹ ዩሳቸው ነው። ውስጤን ስላገኙልኝም አመሰግናቸዋለሁኝ። „ከችግር ማትረፍ“ ወርቅ አገላለጽ ነው። በዚህ ጫናው ባዬለበት ሁሉም መዋቅራዊ ጠገግ ሳይንድ፤ የነበረው መዋቀር ባለመፈረሱ የሚመጣውን ቀውስ ለመሸከም በወሰነ አቅም፤  ሳቦታጅ እና የሴራው መረብ እንዳለ ግን በስልት እና በጥበብ አዲስ ሥርዓት ለማዋለድ በሚካሄደው ግብግብ ውስጥ ጫና ሊፈጥሩ ይችላሉ የሚባሉ ችግሮችን በመጎርጎር በግነትም ይሁን ነገሮችን በማጣደፍ የሚታዩ የትርምስ ዓውዶችን በመፍጠር እረገድ ያለውን ማነኮር የገለጹበት መንገድ እኔ ወድጀዋለሁኝ።  „ከችግር ማትረፍ“ በምልሰት የ50 ዓመት የኢትዮጵያ የፖለተካ ጉዞ ስንገመግመው ችግር አምራች፤ ትውልድ አባካኝ፤ መዋዕለ መንፈስ አባካኝ ነበር። በቅሎ ተሳክቶ ጸድቆ አቅም ማዬት ሃራም ነበር።  ይህም ብቻ አይደለም የሂደቱ ተዋናይ ካፒቴኑ ራሱ ሁለንትናዊ አቅሙም ድርጁ አልነበረም። ዘመን የሚሰጠውም የሚነሳውም ነገር እንደ ተጠበቀ ሆኖ። ዛሬ ዲጂታል ዓለም ላይ ነው ያለነው