ልጥፎች

ከፌብሩወሪ 2, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ህግ በራስ ላይ እንዲህ ተፈጻሚ ሲሆን ተስፋ ማደሪያ ይኖረዋል።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ህግ በራስ ላይ እንዲህ  ተፈጻሚ ሲሆን ተስፋ ማደሪያ ይኖራዋል። „ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፳፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02.02.2019 ከእመ ዝምታ ከሲዊዝሻ።                                             „ለተባረከች አገር የተባረከ ትውልድ“    ·        መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=yIzEROYdwoE #EBC   ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የጉዲፈቻ ልጃቸውን ህጋዊ አደረጉ፡፡ „ለተባረከች አገር የተባረከ ትውልድ“ ዓላማው አድርጎ የተነሳው እሸቱ መንፈስ እንሆ እንደ ማንኛውም ዜጋ በፍርድ ቤት ተገኝተው ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው እና ጠ/ሚር አብይ አህመድ ከ5 ወራት በፊት በጉድፊቻ የተረከቡትን ልጃቸውን በህጋዊ ውሳኔ መቀበላቸው ኢቢሲ ዘግቧል።  ህግን እንዲህ በሁሉ ዘንድ እኩል ተፈጻሚ ሲሆኑበት ተስፋ ማደሪያ ይኖረዋል። ተስፋም መብቀያ ይኖረዋል። ተስፋም ጥግ ይኖረዋል። ተስፋም ትውልድ ይሆናል። የትውልድ የመንፈስ ብክነትም በዚህ መልክ መልክ ቅጥ ለማስያዝ ተግባሩ ትራስ ይሆነዋል። ትውልድም ከሚሰማው ይልቅ የሚያየውን ስለሚያምነው በሚያምነው ልክ ትውልዳዊ ድርሻውን ለማሳከት ወይንም ለመወጣት ቁርጠኛ ይሆናል። ይህ ከህግ አንጻር ብቻ ሳይሆን ከሰባዕዊነት አንጻርም በመንፈስ አትራፊ መንገድ ነው። ከሰባዕዊነት አንጻር ብቻ ሳይሆን ከእኛዊነት አንጻርም ተቋማዊነቱ ዝልቅ ነው። ችግርን የእኔ ማለት። አይዟችሁ የማለት። አለንላችሁ የማለ

ሁሉም ነገር ያስፈልጋል ሁሉም ነገር ጠቃሚ ነው ከሁሉ ግን የሉዑላዊነት ከብርን ማስጠበቅ የበለጠ ነው።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ጠ ጣ ር ። „ ኖን። መንገዳችን እንመርምር እና እንፈትን። ወደ እግዚአብሔርም እንመለስ።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ፫ ቁጥር ፵ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  01.02.2019 ከእመ ዝምታ ኪሲዊዝሻ። ·        ጠብታ። ውዶቼ እንዴት ናችሁ። ዛሬ ቪንቲ ከፋፍቷታል። እንዲህ ከፍቷት እኔ ደግሞ ጫና ብጨምርባት ሆድ ይብሳታል ብዬላችሁ መውጣቱንም ተውኩት እንጂ ዛሬ የዓመቱ ቅዳሜ ብዙ ነገር ታልሞለት ነበር። የውርጩ ገጹ ጭጎጎት አስመስሎ ይታመሳል።  ጠብታውም መጣሁ ሄድኩ እያለ እሱን እራሱን በተፈጥሮው ውስጥ ሆኖ ይነሳስተዋል። ፊታውራሪ ጉምም አይቅርብኝ ብሎ አብሬ ልታደም ብሎ ዕለቱን የሙጥኝ ብሏል። ሻሾ ግን ብቅ አላለም ትናንት መክሰስ ዛሬ ቁርስ አልሰጡትም መሰል። እና ሥርጉቱሻ በሶስት በአራት ለመሰለቅ ስለምን ትታደም እትዬ ዛሬን? ካሊሟን ደራርባ ጉብ ብላ እስቲ ብራና ሆይ! ይትናንቱን ልቀጥልህ ብላ ኮቢ ፍለጋ ስትማስን ሳይጠሩሽ አቤት በራሷ ጊዜ ከች። ·         መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=miHgNJKM4mY Ethiopia : [ አዋረዳት ] ጠ / ሚ አብይ ይህቺን ሃገር እንደ አዜብ መስፍን የበዘበዘ እና የሰረቀ ሰው የለም የቀለጠች ሌባ ናት ·        የፍሬ ነገር የሆድ ዕቃ። „በመጀመሪያ የተከበረው ምክር ቤት እንዲገነዘበው የምፈልገው ኢትዮጵየ ውስጥ ወንጀል ሰርቶ ወንጀል በመሠራቱ በመንግሥት ዲክለር ተደርጎ ያልታሰረ ሰው የለም። ልዩነቱ መንግሥት ባዘጋጀው እስር ቤት ውስጥ መንግሥት እዬጠበቀው፤ መንግስት እዬቀለበው መታሰር እና እራሱን ማሰር ካልሆነ በስተቀር አልታሰ