ልጥፎች

ከዲሴምበር 4, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ባለቤት አልባወቹ የአብነት የቆሎ ተማሪወች ሰቆቃ። ይድረስ ለዶር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ የሰባዕዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር፦

ምስል
ባለቤት አልባወቹ የአብነት የቆሎ ተማሪወች ሰቆቃ። ይድረስ ለዶር ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ የሰባዕዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር፦ አዲስ አበባ። "ጎለመስኩ አረጀሁም፤ ፃድቅ ሲጣል፦ ዘሩም እህል ሲለምን አላዬሁም።" (መዝሙረ ዳዊት ም ፴፮ ቁ ፳፭)     ዶር ዳንኤል ሆይ! በቅድሚያ እንደምን ሰነበቱ? ዛሬ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት የሊቀ ሊቃውንት መፍለቂያ የሆነው ዬዬኔታ ቤት ሰፊ ሰቆቃ እዬደረሰበት ነው። ብዙ የቆሎ ተማሪወች ህይወታቸውን አጥተው ሰማዕትነትን መቀበላቸውን በተለያዬ ጊዜ ይደመጣል። በሌላ በኩል የቆሎ ተማሪወች በእስር እንግልት ላይ መሆናቸውንም ባለፈው ሳምንት በላስታ ላሊበላ ቅርስ ችግር ላይ ከተወያዬው ጉባኤ ተገንዝቤያለሁኝ። 1) የታሰሩ የቆሎ ተማሪወች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈቱ ዘንድ እንዲረዱን እሻለሁኝ። በእንተ ሥመ ለማርያም ብለው ለምነው፤ ከውሻ ጋር ተጋፍተው፤ እራፊ ጨርቅ ሌት እና ቀን ተላብሰው ቀለም ሊማሩ የሄዱ ንፁኃን እንደምን በእስር ይንገላታሉ? ይህን ጉዳይ ድርጅተወት በይፋ ዕውቅና ቢሰጠው እና ክትትል ያደርግበት ዘንድ በትህትና አሳስባለሁኝ። 2) በድሮን የሚከወነው ጥቃት በአብያተ ቤተክርስትያን፤በገዳማት፤ ሰብሰብ ብለው በሚገኙ ንፁኃን ላይ ስለመሆኑም አዳምጣለሁኝ። እንደምን አንድ ምራኝ ብሎ የተመረጠ መንግሥት በህዝቡ ላይ ይህን መሰል አረመኔያዊ ተግባር ይፈጽማል??? መቼ ነውስ የሚቆመው? ለዓለም ሰላም ወዳድ ኃያላን አገሮች እና ስለ ሰው የሚገዳቸው ሉላዊ ተቋማትም በሚገባቸው ቋንቋ ጉዳዩን ማሳወቅ የሚገባ ይመስለኛል። ሰው እኮ ዳንቴል አይደለም። 3) የላሊበላ አብያተ ትውፊቶች፤ እና በሌሎችም ያሉ አብያተ ቤተ ክርስትያናት እንደ ትውልድ እንክብካቤ ሊደረግላቸው ሲገባ የጥቃቱ ሰለባ፤ ዒላማም ሆነዋል። ለምን?

ቤተ - የዕብደት አለሎ!

ምስል
  ቤተ - የዕብደት አለሎ! ቤተ - የበቀል ካስማ። ቤተ - የፍርሰት ናዳ! ቤተ የኢትዮጵያ ቅብረት - የሞት ድንኳንኛ። ቤተ - የሴ ራ የሬሳ ግብረ ኃይል። የኢትዮጵያኒዝም ነቀዝ አድናቂነት¡¿¿¿ ቤተ _ የጥላቻ ካንፓኒ ሎቢስት¡¡¡ "ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።" ማህበረ ግብረ ሰይጣን ዝክረኞች ይህ ሁሉ የአማራ ደም፤ ጉስቁልና፦ የህልውና አሳር ለእናንተ ፌስትባል ነው። "የቡርቃ ዝምታ" የዲያቢሎስ ቅኝት አድናቂነት ዲዲቲነት የትውልድ ካንሰር ነው። ለዚህም ነው እኔ አማራ ከማን ጋር ለእርቅ ይደራደር የምለው። ፋክቱም ሎጅኩም አያስኬድም። ከጭንቅላት ውስጥ የተገነባው የጥላቻ ሃውልት መፍረስ ነው እርቀ ሰላም፤ ፍትህ ሊያመጣ የሚችለው። ሰይጣን በቅድስት አገር ኢትዮጵያ መዘከር የሰማይም የምድርም ወንጀል ነው። የስንት ሊቀ ሊቃውንት አገር ኢትዮጵያ? የስንት ዓራት ዓይናማ ፀሐፍት አገር ፈላስፊት ኢትዮጵያ? ኢትዮጵያን ለመሰነጣጠቅ የፋንታዚ ፖሊሲ ነዳፊ አውጪን የመቃብር ሥፍራን መዘከር ማለት እኔ ፀረ ኢትዮጵውያዊነትም ነው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 2/11/2023

የዕውቀት ባለፀጎች ኢንፍሌንሽን ኢትዮጵያን እንዳይገጥማት እሰጋለሁኝ።

ምስል
  የዕውቀት ባለፀጎች ኢንፍሌንሽን ኢትዮጵያን እንዳይገጥማት እሰጋለሁኝ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።" አገር የሰፈር የእድር ማህበር አይደለም። የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ደጋፊያን እዬጠቀሟቸው አይደለም። ምንም አይነት የእርምት ዕይታ እንዳይኖር ጠቃሚ ሃሳቦችን በደቦ እያስበረገጉ ነው። ይህ ደግሞ ቁልቁለት ዳጥ እና ምጥ ያዋልዳል። ለትውልድ፤ ለአገር የሚጠቅመው በሁሉም የሙያ መስክ ያሉ ኤክስፐርቶት የሚሰጡት ሙያዊ ክሪቲክ ሊደመጥ ይገባል። በሌላ በኩል መከራውን የተሸከመው ህዝብ አጋጣሚ ሲያገኝ የሚያሰማው ብሶት ፖሊሲ ቀራጭ ሊሆን ሲገባ አደና እና እስር፤ ግለት እና ማሳዳደድ የውድቀት ዋዜማወች ናቸው። እረኛ ምን አለ ታላቅ የዊዝደም ፈር ቀዳጅ ነው። በሌላ በኩል በተለያዬ ሙያ ፕሮፌሽናል የሆኑ ኢትዮጵውያን ወጀብ ፈርተው አንገታቸውን ደፍተው መጠበቅ እናት አገርን መካድ ይመስለኛል። ይህም ብቻ አይደለም የሙያ ሊቀ ሊቃውን ከሙያዊ፤ ከዕውቀታዊ ማዕቀፋቸው ወጥተው ፕሮፖጋንዳውን ከተቀላቀሉም ሰፊ የሆነ የአዋቂወች በረከተ ፀጋ ኢንፍሌንሽን ኢትዮጵያ ሊገጥማት ይችላል። የኢትዮጵያ የስድስት ዓመቱ ችግር የተጋገር ችግር ነው። ስለሆነም ያልሰከኑ ቦጅቧጃ ፍላጎቶች ትውልድንም አገርንም ማዳን አይቻልም። በሌላ በኩል የአገር እና የትውልድ ክብር እና ልዕልናም ከግለሰቦች ሙገሳ፤ ውደሳ ዝቅ ካለ ይህም የሚያስፈራ አደጋ ይመስለኛል። ውዶቼ እንደምን እዬሆናችሁልኝ ይሆን? ቸር ሁኑልኝ። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 4/12/2023 ፈላስፊት ኢትዮጵያ ይቅናሽ። አሜን። Sergute Selassie   · Shared with Public