ልጥፎች

ከኦክቶበር 2, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የሃይማኖት ተቋማት የህዝብ ሰቆቃ አጀንዳቸው አይደለም።

ምስል
ሃይማኖት ምንድን ነው? „ልጄ የበደልከው በደል የሳትከው ነገር አንዳለ እወቅ  ከዚህ በኋዋላ ዳግመኛ አትበድል ስለ ቀደመው ሃጢያትህ ንስሓ ገብተህ ተቀመጥ።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፳፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ© ሥላሴ 02.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። እኔ ውዶቼ ስለ ሃይማኖት ፍልስፍና ልናገር አይደለም። ይህ ጸጋ የአቨው የሃይማኖት ሊቃውንት መክሊት ነው። ሃይማኖት ማለት ምንድን ነው ብዬ የምጠይቀው ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሃይማኖት ተቋማት ከንፈር ከመምጠጥ በስተቀር በዚህ የመከራ ቀን ከህዝብ ጎን ሊቆሙ አለመቻላቸው ሃይማኖት አለ ኢትዮጵያ ውስጥ ለማለት ከበደኝ። የእውነት ከበደኝ ሃይማኖት አለኝ ለማለትም። የእውነት ይጭነቃል። ጂጂጋ ላይ ያን ያህል ሐዋርያት ሲታረዱ፤ አድባራት ሲነዱ፤ ምዕማናን ያን ያህል መከራን ሲቀበሉ አንድም ልዑክ  ከቅዱስ ሲኖዶስ ተልኮ ሄዶ ቦታውን እስከ አሁን ድረስ አላዬም። ለመሆኑ ፕትርክና ምንድን ነው? ምዕመናን እቦታው ድረስ ሄዶ ካላጽናን? ዓምት ሙሉ መፈናቀል?  ዓመት ሙሉ በሰው ሰራሽ ችግር እንዲህ ፍዳ መክፈል። ተቆጭ የለ። መካሪ የለ። የሚገስጽ የለ። ግርጫማ ጸጉር ያለው የለ። የሚፈራ የለ። በሃይማኖታዊ ተቋማት ለተጎዱት አንዳችም ነገር አልተደረገም። ማውገዙን እማ እኛ ድሆችም እናወግዘው የለ። በቃ ሚዲያ ላይ ወጥቶ መናገር የሃይማኖት አባትነት ያሰጣልን? ሃይማኖት ለዚህ መከራ ቅርብ ካልሆነ ማን ሊሆን ነው? በዬቦታው ለቅሶ ነው። በዬቦታው ዋይታ ነው። የመንግሥት መሪዎችን አይገስፁ የሚቆጣቸው የለ፤ የሃይማኖት አባቶች ቸልተኞች እና ግድየለሾች። ለነገሩ የራሰቸው ገማና ከሆነስ? ሌላው ቀርቶ ቡራዩ ላይ እስከ 15 ሺህ ተፈናቀለ የተ

የፈረደባት "ኢ" ትደፈር ይሆን?

ምስል
ቀን የሚሰጥ ብልህነት። „የእግዚአብሄር ቃል ወደ ኤርምያስ እንዲህ ሲል መጣ እንሆ፣--- የሥጋ ለባሽ ሁሉ አምላክ እግዚአብሄር ነኝ፤ በውን እኔን የሚያቅተኝ ነገር አለን?“ ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፴፪ ቁጥር ፳፯ እስከ ፳፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 02.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። አንቺ ሆይ! ያልፍልሽ ይሆን? ዛሬን አዴፓ እንዴት እንደሚውል አላውቅም። ቀድም ብዬ እንደ ገለጽኩት የአቶ ደመቀ መኮነን ጉዳይ ጫና እንደ ነበረበት ገልጫለሁኝ። እለቃለሁ ያሉበት ምክንያት እስከ ጉባኤ ድርስ ይፈለጉ ስለነበር፤ አሁን አገልግሎትህን ጨርሰሃል ዓይነት ነው። ነገር ግን የአማራ ጉባኤ ከምለው የኢትዮጵውያን ጉባኤ አልፈቀደም እናም እንዲቀጥሉ ተውሰኗል። ቀን የሚሰጥ ብልህነት እንዲህ ይገለጻል። ሌላው የክልሉ ጉባኤዎች በፕሮግራሙ ላይ መወያዬት ነበረባቸው ያም አልተፈቀደም። ዝግጅት በቂ ጊዜ ስለሚጠይቅ ይላል የአቶ ምግባሩ ከበደ ቃለ ምልልስ፤ ዓመቱን ሙሉ የማንን ጎፈሬ ያበጥሩ ነበር? ስላልተፈቀደ ቢሉ አይሻልምን? የአማራን መንፈስ ማን ሲፈልጋቸው ነው ቀድሞ ነገር? ዓርማ እኮ ከ ዓለማ እና ከግብ ነው የሚመነጨው። ዓላማ እና ግቡን ደግሞ የኦዴፓ አዲሱ ፍልሰፍና ነገሮናል።  የሆነ ሆኖ ልብ ያለው ብልህነት በዬትኛው ማህበረሰብ መንፈስ ፕሮግራሙ እንደሚዘጋጅ ፈቃጅ ያስፈለግው ስለነበር ነው።  በዛ ፕሮግራም ውስጥ አማራ ጉባኤ ላይ የተፈራ ጉዳይ ስለነበረ ነው። በማዕከላዊ ደረጃ ግን ረቂቅ ተዘጋጅቷል። ዕውነቱ ይህ ነው። ስለዚህ የኢህአዴግ ጉባኤ አዲሱን የማሻሻያ ረቂቅ ፕሮግራም ተቀብሎ ያጸድቀዋል - ነገ። የሚፈራው አንድ የወያኔ ሃርነት ትግራይ መንፈስ ብቻ ነው። አረግበዋል ተብሎ የተሰበው መንፈስ ደግሞ አሁን ታዳሚ ነው እኩል።