ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 12, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ደጉ አቶ ዮሴፍ ገብሬ፤ ተባረክ!

ምስል
የማስተዋል አንበል። „ደግ ሰው ግን ለሞመት በደረስ ጊዜ በ ዕረፍት ይኖራል።“ መጽሐፈ ጥብብ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፯ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·          መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=9ndpRVHlBG8 „Jossy In Z House የአዲስ አመት ዘመድ ጥየቃ ከኢንጅነር ስመኘው ቤት“ ደግነት ለራስ ቢሆንም ትውልድን በማነጽ እረገድ ተቋም ነው። የደግነት ተፈጥሮ ሰላምን ይሰጣል። መጀመሪያ ሰላም የሚሰጠው ለራስ ነው። ሲቀጥል ለቤተሰብ ነው። ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ለአላዛሯ ኢትዮጵያ ነው። ኢትዮጵያ በመንፈስ ታለቅሳለች - ሲከፋት። በመንፈስ ታናባለች - ሲጨልምባት። በመንፈስ ትሰጋላች - አዬሩ ሲታወክ። በመንፈስ ሰላሟ ይታወካል ልጆቿ - ሲበተኑባት። ኢትዮጵያ ልጆቿ ሲጠነክሩ እሷም - ትጠነክራላች። ልጆቿ ሲዝሉ እሷም - ትዝላለች። ልጆቿ ተስፋ ሲኖራቸው እሷም - ተስፋ ይኖራታል። ልጆቿ ተስፋቸው ሲደርቅም እሷም - ክው ትላለች። ልጆቿ ቅስማቸው ሲሰበርም እሷም - እንኩት ትላለች። እናት እኮ ናት - አገር። አንጀት ናት የትወልድ ባዕት። ህሊና ናት የነፍስ ባድማ። ልክ እንደ ሰው ነው ጠረኗ። እንዲህ ደግሞ በክፉ ቀን፤ ሰው በጠፋ ቀን፤ ቀን ፊቱን ባዞረ ዕለት፤ አዬሩ በከፈው ማዕለት፤ ተስፋው በራቀ ዕለት፤ ስጋቱ አገር ምድሩን በረቂቅ ባከለለው ሰዓት አንድ እንደ ወልዴ የዛን የበርሃ ከልታማ ቤተሰብ ሄዶ መጠዬቅ ምን ይባል? አለሁላችሁ፤ አይዟችሁ ከአዘቦቱ ቀን ይልቅ ይህ ቀን ወሳኝ ነው። በምን መስፈርት ይህ ደግነት ይተርጎም? በምን ሜትር ይህ ቸርነት ይለካ? በምን ደረጃ ይህ ማስተዋል ይመዘን? ይገርማል እጅግም ይደንቃል። ይህ ቅን ወ

በባዕላት ከብር ለሚገባው ክብር መስጠት ዕንቋችን።

ምስል
ማለፊያ! „አድርገህልኛል እና ለዘላላም አመሰግንሃለሁ።“ መዝሙር ምዕራፍ ፶፩ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 12.09.2018 ከጭምረቷ ሲዊዘርላንድ። በሰመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ አሜን! ኑሩልን! ·        መነ ሻዬ። https://www.youtube.com/watch?v=CLDYosWqMXQ „ሁለቱ ሲኖዶሶች አንድ በመሆን በአንድት የአዲስ አመት በዓል ሲያሳልፉ የሚያሳይ ልዩ የበዓል ዝግጅት“ ከእንግዲህ „ሁለቱ ሲኖዶስ“ የሚለው ቃል ራሱ መታረም ያለበት ይመስለኛል። በቅደስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብጽዑን አባቶች ባዕለ ቅዱስ ዮሖንስን ሲያከበሩ ሊባል ይገባል። ቀድሞውንም ዶግማው አንድ ነው የነበረው።  ቅድስት ቤተክርስትያነችነን ጊዜ ፈተነ፤ ዲያቢሎስ ሲረታ ደግሞ አህቲ ቤቴክርስቲያን እንደ ተፈጥሯዋ ሆነች።  የሆነ ሆኖ እጅግ የሚመስጥ የበዓል ጠረን በቅደስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብፁዕን መኖሪያ ቤትም መከወኑ ዘገባው ያመልከታል። ለእኔ በቅድስት ፓትርያርክያት ደረጃ እንዲህ ባህላዊ ትውፊት ሳይጓደልበት ሲከበር የመጀመሪያዬ ነው። እንዲህ ሲከበር አይቼ አላውቅም። ቡናው እየተቆላ እንደ አባት አዳሩ መሰናዶው ተሟልቶ፤ ቤት ያፈራው እንደዛ ኑብኝ ኑብኝ አያለ፤ መዘምራን እዬወረቡ ቅኔው እዬተዘረፈ እፁብ ድንቅ ነው። ይህ ትውፊታችን፤ ትሩፋታችን ያከበረ አያያዝ የዛሬ 10 ዓመት ብዬ ሳስብ ዘመኑም፤ ታሪክም፤ ትውፊትም፤ ትውልድም፤ አገርም የሚካስበት አዲስ ስዕል ዲዛይን ሸልሞኛል። በሌላ በኩል ድርጊቱ  የአብይ ሌጋሲ ታሪክንም እዬጻፈልን ነው። ታሪኩ ደግሞ የ አላዛሯ ኢትዮጵያ አንጡራ ሃብቷም ነው። የነገ ደግሞ ትውፊቷ። ውርስ ቅብብል እንዲህ እያለ ከትወልድ ወደ ትውልድ

የቤቴ ውሽክታ ...

ምስል
 ድገሙኝ ሰለሱኝ ይል ነበር … „የእግዚአብሄር ቸርነት ምድርን ሞላች።“ መዝሙር ምዕራፍ ፴፪ ቁጥር ፭ ከሥርጉተ© ሥላሴ 12.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ·        ዓ ውደ ዓመት እና የቤቴ ውሽክታ …. አቤት ሃሞጭ የመሰለው ጥርስ እንዴት ያምራል? አቤት ዓይን እንዴት ይስባል፤ አቤት ተረከዝ እንዴት ከሩቅ ይጣራል፤ አቤት ሽንጥ እና ዳሌ እንዴት ያስንቃል  የእኔ እንዳይመስላችሁ ውዶቼ የቤቴ ነው … ትናንት ለመጀመሪያ ጊዜ ኮንፒተር ሳይከፈት ተዋለ ታደረ። ለመጀመሪያ ጊዜም በዘመነ ስደት ቅዱስ ዮሖንስ ዲል ተብሎ በሙሉ መሰናዶ ተከበረ። አይደለም ሥርጉትሻ ቤቴም ሳቀ በሳቅ፤ ሰናይ በሳናይ፤ ፈገግታ በፈገግታ። ተመስገን! ነፃነት ለካንስ እንዲህ የሳቅ ንጉሥ ነው። ነፃነት ለካንስ እንዲህ ሁለመናን ያፍለቀልቃል። ነፃነት ለካንስ የአቅም መሃንዲስ ነው። ነፃነት ለካንስ ሃይል ነው። ነፃነት ለካንስ እንዲህ ናፍቆትን ይክሳል። አገር ቤት እያለን ታናሽ እህቴ ጳጉሜን ቤቱን ዝርክርክ ታደርገው ነበር። ቅዱስ ዮሖንስ እንዲደምቅ የምትለው ብሂል ነበራት። አሁን እኔም ከሰሞናቱ እንደዛ ገጥሞኝ ነበር። ሥራ ብዝት ብሎብኝ ሰነበተ። ግዢውም እንዲሁ። እኔ ለአውድዓመት እንብዛም ነበርኩኝ አገር ቤት። ያው ሥራ ይበዛብኝ ስለነበር። ቤተሰቦቼ ደግሞ ቀን ቆጣሪዎች ናቸው። ይወዳሉ። እንዲያውም ቅዱስ ዮሖንስ እና ፋሲካ አንድ ሳምንት ቢከበር ባዮችም ናቸው። የሆነ ሆኖ ከአገር ስወጣ ብዙም አልከበደኝም። ነገር ግን ዘንድሮ የተሰማኝ ስሜት የተለዬ ነበር። ደግሞም የዘንድሮው ባዕል መከበር ሲያንሰው ነው። የውስጤ ሊባል የሚገባው ነው። አዬሩ ራሱ እንዴት ደስ ይል ነበር። የኢትዮ ኤርትራ ዋንጫችን በበለስ ነበ

ነገረ ጋዜጠኛ መሳይ ...

ምስል
በመሆን ውስጥ ብዙ ፈተና አለ። „መተለላፉ የቀረችለት፤ ኃጢያቱም  የተከደነችለት ምስጉን ነው።“ መዝሙር ምዕራፍ ፴፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  12.09.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ·        መነሻ „የከንቲባው ነገር – መሳይ መኮነን“ ·        ወግ ቢጤ … መርጋዊ ፈተና ያለው በመሆን ውስጥ ነው። በመሆን ውስጥ ያለው ፈተና ደግሞ መጀመሪያ የሚያጠቃው የራስን ሰብዕና እና ሞራላዊ አቅም ነው። በራስ ሰብዕና ውስጥ መሆን እንዲገኝ ከተፈለገ ዕውነትን መድፈር ይጠይቃል። ዕውነት ተፈጥሮ አለው። ዕውነት የኖረው ሆነ ወደፊትም የሚኖረው በተፈጥሮው ውስጥ ነው። ዕውነት አምላኪነቱ ለተፈጠረበት ዕውነት ብቻ ነው። ዕውነት ዳኛ የሚሆነው በተፈጥሮ ውስጥ ለመኖር ለፈቀዱት ብቻ ነው። አሁን እኔ በጸሐፍት ውስጥ የማዬው ዕውነት እንደ ፍልጎታችን፤ እንደ ዝንባሌያችን፤ እንደ ስሜታችን ሆኖ ነው በአብዛኛው ጊዜ። ከዚህ የወጡ ጸሐፍት ደግሞ አሉ ለምሳሌ የኢኮኖሚ ሊቀ ሊቃውነቱ እና ጸሐፊ ዶር ፈቃዱ በቀለ። እሳቸው ጹሁፋቸውን ሲያዋቅሩት መሰረታቸው፤ መደወሪያቸው፤ ባላ እና ወጋግራው ሆነ ሰቁ ሁሉመናው የሚዋቀረው በፋክት ላይ ነው። ስለሆነም ሁኔታዎች እውሃ ቅዳ አውሃ መልስ ቢል፤ ወጀብ ቢናጥ፤ አውሎ ቢጋልብ፤ ማዕበል ቢጎርፍ ንቅንቅ አይልም የጹሁፋቸው መንፈስ።  መቼም አንድ እና አንድ ሲደመር ሦስት ሆኖ አያውቅም ወይንም ራሱን መልሶ አንድ ሆኖ አያውቅም። ያው ሁለት በቋሚነት ነው የሚሆነው። ቁጥሮቹ በተለያዬ ቀለማት፤ በተለያዬ ዲዛይን፤ በተለያዬ ስፋትና እርዝመት ይጻፉ አንድ እና አንድ ሲደመሩ ሁለት ብቻ ነው የሚሆኑት። ድምሩ ቋሚ ነው። የዶር ፈቃዱ በቀለም የጹሁፍ መንፈስ እንዲህ ነው። ፋክቱ