ልጥፎች

ከጃንዩወሪ 5, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

!ዳግማዊ አባ ኮስትር አቶ ንጉሡ ጥላሁን የማን ናቸው?

ምስል
!ዳግማዊ አባ ኮስትር አቶ ንጉሡ ጥላሁን   የማን ናቸው? ! „አንተ በህይወት ሳለህ አእምሮህም  ሳለች ግብርህን አትለወጥ።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴ ቁጥር ፳፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 05.01.2019  Sergute©Selassie ፍቅር በፍቅር! ·        ከእመ ዝምታ ከእናቱ ሲዊዝ ዋው ሻሾ ፍጥነቱን ጨምሯል ዛሬ የታደለ ቀን ነው። ሻሾን እወደዋለሁኝ እንደ አድዮ ነው የማዬው። በቃ በዚህ ከቀጠል ነገ ነጭ ስጋጃ ለሰንበት ሙሽራ አንጥፎ ይጠብቃል ማለት ነው። ግን ውዶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ ወይ? ·        ወግ ቢጤ …. ሰሞኑን አንድንድ ዜናዎች ከዚህም ከዚያም ሲወርቡ ደፍሬ መጻፍ አልቻልኩም። የጠራ መረጃ በግራ በቀኝ ማግኘት ስለነበረብኝ። አቶ ንጉሡ ጥላሁን የጠ/ሚኒስተር ጽ/ቤት የፕሬስ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው እርግጥ መሆኑን ዛሬ የበለጠ አረጋግጫለሁኝ። ስለሆነም በዚህ ዙሪያ የምለው ይኖረኛል። ·        አቶ ንጉሡ ጥላሁን የማን ናቸው? ለመሆኑ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የኢትዮጵያ? - የአማራ? - የጉራጌ? - የኦሮሞ? - የዜግነት? - የዞግነት? ከቶ - የማን ናቸው። እንደ ሥርጉ ሥላሴ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የራሳቸው  ብቻ ናቸው። እድግመዋለሁኝ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የራሳቸው ብቻ ናቸው። ለሁሉም መስመር ደግሞ ሊንክ አገናኝ ድልድይ ናቸው። ለውጩም ለአገር ውስጡም። ዘለግ አድርገን ስንሄድበትም ከዚህም ያለፈ ይሆናል። ወደ ሌላ ዓለም ይዶለናል። ለጊዜው በቁጠባ ይያዝ ...  እንዲህ ዓይነት ሰብዕና በጥንቃቄ መያዝ ይኖርበታል።  ለሁሉም መስመር ሊንክነታቸው አሉታዊ ከሆነ አደጋው ሰፊ ነው። አዎንታዊ ከሆነ ግን ትርፍን መቸርፈስ ነው እስኪበቃ። ስለምን ልባም የሆነ አቅ

ሳተናው ወጣት አቶ ምግባሩ ከበደ ሳንጠግባቸው የት ገቡ?

ምስል
ሳተናው ወጣት   አቶ ምግባሩ ከበደ ሳንጠግባቸው የት ገቡ? „ለሞት እስከ ደርስ ድረስ ሁልገዜ መከራ ተቀብያለሁ  እና ስለዚህ ነገር እግዚአብሔር ከመከራ ያድነኛል“ መጽሐፈ ሲራክ ፴፩ ምዕራፍ ፲፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ  Sergute©Selassie 05.01.2019  ከእመ ዝምታ ሲዊዝ ·        ጠብታ። ዛሬ ክረምቱ ከገባ ለመጀመሪያ ጊዜ አያ ሻሾ መጣሁ ብሎ ብንብን እያለ ነው። ትናንት ሃይለኛ ብርድ ነበር። ከሃይለኛ ብርድ ቀጥሎ አያው ሻሾ እንደሚከተል ልብ ልክ ቢሆንም ከመኝታዬ ስነሳ ሙሉ ለሙሉ አያዋ ሻሾ ከነመጎናጸፊያው ስጋጃውን ዘርግቶ ኑልኝ ይላል ብዬ ነበር። አሁን ግን በስሱ ይዞታል።  ሌላው የሲዊዝሻ መለያ አያ ሻሾ ሲኖርም ልክ እንደ አውድ ዓመቱ የእማ ዝምታ ነገር ጸጥ ረጭ ነው። እና ሥርጉትሻ ወደ ባዕቷ ገባ ብላ ታጣጥመዋለች። ግርግር የሌለበት፤ ህውከት የሌለበት፤ ኳኳቴ የሌለበት ረጋ ያለ ዓለም ይናፍቃል አይደል? እኔ ለዚህኛው ዓለም የተፈጠርኩ ነኝ። ረጭ ላላው ...  እንደዛ …  ስለሆነም ዛሬም ምንም እንኳን ዕለተ ቅዳሜ ቢሆንም ጸጥታ አንጻራዊ ይኖራል አይዋ ሻሾ ሳይደክም ወይንም ሳይሰለች ገፋ አድርጎ ከሄደበት ነገ ዳግሚያ ባይናከተን ሆኖ እርፍ እንደሚል ነው። እንጠባበቃለን … ·        የስጋት እንቁላል። የብአዴን የስሜን አሜሪካ ጉዞ ብዙም ስላልተመቸኝ ጥፌ ነበር። ምክንያቱም እኔ ፈሪ ስለሆንኩኝ። ያልኩትም አልቀረም እነሱ ስሜን አሜሪካ እያሉ ነው በቅማንት ጉዳይ ያደቡ ሃይሎች ስንጥቅ ፈጥረው ጥፋት ያስከተሉት።  በብአዴን በኩል የአማራር አካሉ ክፍተትም እንዲሁ ሌላው ስጋቴ ነበር። በስጋቴ ልክ ምን ያህሉ እንደታዬ አላውቅም። እኔ ግን ሳዬው የአማራ የብዙሃን መገ