ልጥፎች

ከጁላይ 11, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የሰውን ልጅ መኖር በግፍ መቀማት #ስርቆት አይደለምን?

ምስል

#ማን ተጫወተው? ለእንግሊዞች ለዋንጫ ውድድር እግዚአብሄር ነው የፈፀመላቸው ማለት ይቻላል።

  #ማን ተጫወተው? ለእንግሊዞች ለዋንጫ ውድድር እግዚአብሄር ነው የፈፀመላቸው ማለት ይቻላል።   #ማን ተጫወተው? ለእንግሊዞች ለዋንጫ ውድድር እግዚአብሄር ነው የፈፀመላቸው ማለት ይቻላል። ያን አሰልቺ ላንግባይሊክ፤ እጅግም አድካሚ ለተጫዋች ብቻ ሳይሆን ለተመልካች የአጨዋወት ዘይቤያቸውን ይዘው በፔናሊቲ ሎተሪ ዛሬም ሆላንድን ሁለት ለአንድ ረተው ለዋንጫ ተፋላሚ ሆነዋል። ግርም ነው ያለኝ። በግል ያላቸውን ብቃት ሳያቀናጁ ለዋንጫ መብቃት የእግዚአብሄር ሥራ ነው ማለት እችላለሁኝ። በግል በጣም ቀልጣፋ ኮከቦች እንዳሏቸው አስተውያለሁ።    ዛሬን በጎል እልልታ አህዱ ያሉት መጀመሪያ ለግብ የበቁት ሆላንዶች ነበሩ። እንደ ጀርመኑ Das Erst ትንታኔ ሆላንዶች ለዚህ ዕድል ለመብቃት 20 ዓመት ጠብቀዋል ብሎ ነበር። ዛሬ በመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እንግሊዞች ተስለው ነበር የቀረቡት። ባይቀጥሉበትም። አቻ ያበቃቻቸውን ግብ ያስቆጠሩት በለመዱት ፔናሊቲያዊ ዕድል ቀንቷቸው ነው።ከእረፍት መልስ ሁለተኛውን ግብ አክለው እንሆ ሆላንድን ረተው ለዋንጫ ደረሱ። ይገርማል።    ትናንት ብቃታቸው በግል እና በቡድን በቋሚነት እያሳዩ የመጡት ስፔኖች በመደበኛ የጨዋታ ጊዜ ፈረንሳይን ሁለት ለአንድ በሆነ ጎል ብቻ ሳይሆን በጨዋታ ብልጫ በአቅም፦ ብቃት ፈረንሳይን ሸኝተው እነሱ ለዋንጫ አልፈዋል። #ይገባቸዋልም ። ዬፈረንሳይ ቡድን ካታር ላይ ለዓለም ዋንጫ ያበቃው ያ ታይቶ የማይጠገብ ቅልጥፍናው እና አርቱ ብቃቱ ሸሽቶት ከዚህ ግባ የሚባል ጨዋታዊ ትዕይንት ሳያሳይ ነው ከዚህ የደረሰው።   #ኦስትርያ ፤ #እምዬ ሲዊዝ፤ #ቱርኪ ፤ የክርስቲያ ሮናልዶ እና የፔፔ ፖርቹጋል፦ እንዲሁም ቀደም ብሎም #ኮራ ተሰናብተው #የእንግሊዝ እና #የፈረንሳይ ቡድን እዚህ መድረሳቸው ለኳስ ብቃት