ከቶ የአላዛሯ ኢትዮጵያ ባለቤቷ ማን ነበር?
ከቶ የአላዛሯ ኢትዮጵያ ባለቤቷ ማን ነበር 27 ዓመት ሙሉ? „እግዚአብሄርም ቃየልን ወንድምህ አቤል ወዴት ነው አለው፤ ቃዬልም እኔ የወንድሜ የ አቤል ጠባቂ እኔ ነኝን አለ።“ መጽሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ፳፰ ቁጥር ፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ 13.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። · መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=crQyRhfQXY4 ሰሞኑን በሕግ ቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን በተመለከተ የጠቅላይ አቃቤ ሕግ መግለጫ፣የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንን በተመለከተ የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ · መቅደመ ብልሃት። እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ዶር . አብይ አህመድን እንዴት ትተረጉሜያቸዋለሽ ብባል ብሄራዊ ቀናችን ናቸው ብዬ ነው። ኪንግ ማርቲን ሉተር አሜሪካን የማዳን የመሪነት ብቃታቸው ዛሬ ነው ይበልጥ የታዬ የተገለጠው - በወጉ። አሜሪካ ለራሷ ተርፋ የብዙዎች ተስፋ መሆን መቻሏ የትናንት የኪንግ ማርቲን ሉተር የተጋድሎ ውጤት ነው ። ተስፋ ባጣንበት፤ ጥልፍልፉ ችግራችን መፍትሄ አልቦሽ ሆኖ ከጭቃ ወደ ጭቃ በዙር አዳክሮ በደቆስን ሰዓት፤ ጨንቆን ጥግ አልቦሽ በሆንበት ወቅት ብቅ ያለ የመሪነት ልዩ ድንቅ ክህሎት ነው የ ዶር . አብይ አህመድ መንገድ ። እርግጥ ዛሬ ፍሬውን ልናይ አንችል ይሆናል፤ ብንከተለው ግን ብሄራዊ ቀን የሚያስወስን ቁም ነገር በዚህ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ህሊና ውስጥ አለ። በተቃርኖ ያልሰመጠ፤ በአድሎ ያልበከተ፤ በግለት ያልጨቀዬ፤ በበደል ያልከተመ በንዑድ መንፈስ ንጥረ ነገር