ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 1, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ናፍቆትን መገደብ ለነፍስ ራህብተኞች ሃጢያት ነው ...

ምስል
ሳቅን፤ ናፍቆትን ለመገደብ የታደመው ዕሳቤ ወቅታዊነት ይጎድለዋል። „ማንም ራሱን አያታልል፤ ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበበኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ይሁን።“ ወደ ቆረንቶስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 01.09.2018 ከጭምቷ ሰዊዘርላንድ። ·         የጭብጥ መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=en5MiO0Tq1w #EBC   አድማ የመቱ የሲቪል አቪየሽን ሰራተኞችን በመተካት ለሰሩ ሰራተኞች እውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው፤   ·        መቅድመ ነገር። የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ትናንትም ዛሬም ደምኗል። ትናንትም ዛሬም ልዕልተይ የለችም። ትናንትም ዛሬም ብትጠራ ዓይኔን ግንባር ያድርገው ብላ፤ ጠላታችሁ እልም ይበል እልም ብላለች። ትውር አላችም። እናም እኛ ምናችን ሞኝ ነው ደረትረት ብለን ጉብ ብለናል። ግን ያው እንደ ዳሽን ተራራ ከንፈራችን በልዕልተይ ላይ ነፋ አድርገናል።  ያካፋል፤ ያበራል፤ እንገናም ያካፋል እንደ ገናም ይባራል በቃ እንደ ወርህ ሚያዚያ ቅጥ አንባሩ ጥፍት ያለበት ቀን ነው ዛሬ። ብቻ በዚህ ዓመት የተሻለ የበጋ ጊዜ ስለነበር እንዳሻት ሙቀቷን አክስክሳናለችና አሁን ብትመጣም ብትቀርም እንደ ፍጥርጠሯ ብለናል ስለ አውሮፓዊቷ እሜቴዋ ጠሐይ። ·        የወ ግ ገበታዬን እስቲ ዘለግ አድርጌ ላስኪደው… እንዲህ … የአብዬሽን ሰራተኞች ካለፈው ሰኞ ጀምሮ የሥራ ማቀም አድማ ለመምታት አቅደው ነበር። መቼም ዜናው ሲሰማ ጎሽ፤ ደግ አደረጉ ልላቻው እልቻልኩም። ምክንያቱም ወቅታዊነቱ የሴራ ይመስል ስለነበር። ስለምን ዓውዳመትን ታክኮ አድማን ለመከወን ታሰበ? እኔ የሠራተኛ ማህበር አደራጅ ነበርኩኝ።