ልጥፎች

ዛሬ ችሎት ከቀረቡት ተከሳሾች መካከል ሰባቱ በነጻ እንዲሠናበቱ ችሎቱ መወሰኑን

  Daniel Bekele   · በእነ ጋዜጠኛ መስከረም አበራ የክስ መዝገብ በሽብር ወንጀል የተከሰሱ 16 ተከሳሾች ክሳቸውን እንዲከላከሉ ብይን ተሠጠ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት 1ኛ ጸረ-ሽብር ወንጀል ችሎት፣ በጋዜጠኛ መስከረም አበራ፣ ገነት እስማማው፣ ጎበዜ ሲሳይ እና ዳዊት በጋሻው የክስ መዝገብ በቀረበው የአስተያየት ሰነድ ላይ "ክሱን ይከላከሉ ወይም አይከላከሉ" በሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ጥር 28 ቀጠሮ ሠጥቶ እንደነበር ይታወሳል።    ችሎቱ፣ በእነ ዶ/ር ሲሳይ አውግቸው መዝገብ ሥር የተካተቱ ተከሳሾች የዋስትና ክርክር እንዲያደርጉ ብይን በመስጠት ለሚያዚያ 23 2018 ዓ፣ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሠጥቷል።    ዛሬ ችሎት ከቀረቡት ተከሳሾች መካከል ሰባቱ በነጻ እንዲሠናበቱ ችሎቱ መወሰኑን ዋዜማ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ሠምታለች። በዛሬው ችሎት በጠቅላላው በክስ መዝገቡ ከተካተቱት 51 ተከሳሾች መካከል ችሎት የቀረቡት 23ቱ ናቸው።   ዋዜማ ራዲዮ February 5, 2026 ፎቶው የቆየ ነው።

#የጠይም #ዕንቁ የእልልታ ዜና። "ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት በተመድ መንበር ላይ ተሰይሟል"

ምስል
    #እሰይ #እልል ። እስኪ ቸር ዜና ይዛችሁ ከች በሉልን።       "አድርገህልኛል እና አመሰግንሃለሁኝ።" አንድ ቀን፣ አወን አንድ ቀን ኢትዮጵያ #ተመድን የመምራት ዕድል ይኖራታል። ከጥቁር አልማዝ ይልቅ ጠይም ዕንቁ ቢባሉ።    ከአቶ Trotsky Wendesse የተገኜ የምስራች ነው። አድካሚ ቀን ነበረኝ ዛሬ ግን ይህን መሰል ዜና ብርታትን ይቸራል። "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁኝ።"    መልካም የሥኬት የምርምር ዘመን ይሆንላቸው ዘንድ እመኛለሁኝ። ኢትዮጵያም እንኳን ደስ አላት።    ========== "ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት በተመድ መንበር ላይ ተሰይሟል ከኒውክሌር ጦር መሳሪያ በላይ ዓለምን እያስፈራት ያለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ጉዳይ፣ ዛሬ በአንድ ስመ-ጥር ኢትዮጵያዊ ሳይንቲስት እጅ ላይ ወድቋል። ይህ ወጣት አዕምሮ፣ ከሀርቫርድ እስከ ኦክስፎርድ፣ ከማይክሮሶፍት እስከ IBM የጥበብ ማማዎች ላይ ተራምዶ፣ ዛሬ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) መንበር ላይ ተሰይሟል! የሳይንሱ ኮከብ ጉዞ • የማይክሮሶፍት ኩራት፦ በ "AI for Good" ላቦራቶሪ ውስጥ ዓለምን የሚለውጡ ምርምሮችን ሲመራ ቆይቷል። • የኦክስፎርድና ሀርቫርድ አሻራ፦ ማሽኖች ለሰው ልጅ ጤና እንዴት እንደሚሠሩ በሚያስደምም ጥልቀት የመረመረ ባለሙያ። • የዕውቀት ጎተራ፦ ከ27 በላይ ዓለም አቀፍ የሳይንስ ምርምሮችን ለዓለም ያበረከተ የዘመኑ ጥቁር አልማዝ። የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ በአውሮፓውያኑ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ባስተላለፉት ታሪካዊ ውሳኔ፣ ዶ/ር ግርማው ከዓለም ዙሪያ የተውጣጡ 40 ታዋቂ ምሁራንን እንዲመራና እንዲያስተባብር በይፋ ሾመውታል። "ኢትዮጵያ በዲጂታ...

#ጉግት ለጦርነት ጠቃሚ አይደለም። ሞት #ጎትትም ነው። ቂምና #በቀል የሚያዘምርም ነው።

  #ጉግት ለጦርነት ጠቃሚ አይደለም። ሞት #ጎትትም ነው። ቂምና #በቀል የሚያዘምርም ነው።    "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   ጤናይስጥልኝ አዱኛወቼ የብዕሬ እና የንጹህ መንፈሴ ፈቃደኛ አድማጮቼ እንዴት አላችሁልኝ?   ጦርነት #ብራቮ ጎሽ የምትሉት ሰው ሰራሽ አውዳሚ ክስተት ሊሆን የሚችል አይደለም። ጦርነት ተገደውም ይሁን ፈቅደው ይጀምሩት ለድል የሚያበቃ፤ ለትውልድ #ቅርስ ውርስ የሚሆን ጉዳይ አይደለም። የአለማችን ፖለቲከኞች ጦርነትን #በሁለት ይከፍሉታል። #ህጋዊ (አመክኖያዊ ወይንም ምክንያታዊ) እና #ህገወጥ (አልቦሽ ምክንያታዊነት) ብለው። ህጋዊም ይሁን ህገወጥ ማገዶው የሰው ልጅ ነው። እንጨት እንጂ የሰው ልጅ የተፈጠረው ለማገዶ አይደለም።   ፈጣሪ የረዳው #እንጨት ለታቦትም ይሆንና አክብሮተ ነገሩ ሰማያዊ ይሆናል። የሆነ ሆን ጦርነት እቅዱ ምንድን ነው ከተባለ #የእናቶችን #መሃጸን #ለቄራነት ማሰናዳት ነው። በዚህ በያዝነው ወር የዘለንስኪዝም ዕቅድ በወር 50ሺህ የራሺያ እናቶችን ማህጸን ወደ " #ሊኳንዳ " ቤት መውሰድ ነው። ለቃሉ ይቅርታ እጠይቃለሁኝ።    ይህን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ ዓለማችን አላሰናዳችም። እጅግ ያሳዝናል። ጦርነቱ እንደተጀመረ ዘለንስኪዝም እስከ 10 ዓመታት የመዋጋት አቅም አለን ብለው ነበር። ይህም የዩክሬንን እናቶች ማህጸን በታቀደ #ቄራነት ያሰላ ነበር። ይህን ጨካኝ እይታ ዓለማችን ከማውገዝ ተቆጥባ #እንክህ እንክህ ስትል ስመለከት ማህጸኔ እንደ ዱባ ይቀረደዳል።   የእስከዛሬው አልበቃ ብሎ የኤርትራ መንግሥት እና የኢትዮጵያ መንግሥት በባህር በር የይገባኛል ምክንያት ጉጉሡ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ተካሯልም። #አይጠቅምም ። በፍጹም አይ...

#መፍቻ ።

ምስል
  #መፍቻ ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“   #ምዕራፍ ፲፰።       #ጠብታ ።   ዛሬን ለእኔ ሰጠሁት። ሚሞሪን እያሞቀ ከሚገኘው ለህትም ከበቃው ሦስተኛው የዓዋቂወች የግጥም መድበሌ ላይ የተወሰደ ነበረ። በደራሽ ጉዳዮች፤ በሰብአዊነት ጉዳዮች፤ በኢትዮጵያ ዕናቶች አመክንዮ ጉዳዮች ላይ አበክሬ ስለምሰራ እኔን ስቶር ውስጥ ወይንም ሚሞሪው ውስጥ አስቀምጬ በፌስቡክ ለ፮ ዓመታት፤ በሚዲያ ከ፳ ዓመታት በላይ፤ በፖለቲካ ከጋሜዬ ጀምሮ ተኖረበት። ለእኔ ቀን ሰጥቼው አላውቅም። ይህ ሚዲያ የእኔን እኔም ላስተዋውቀው ፈለግሁኝ። ስለሆነም ዛሬን አጠገብኩት። ጹሁፎቹም ሆኑ ግጥሞቹ ከ፲፭ ዓመታት በላይ የቆዩ ናቸው። ሳድስ ላይ ስለምገድፍ እሱን እና አንዳንድ ጉዳዮችን ለማጠናከር ሞክሬያለሁኝ። እርዕሶች ጭብጡ አልተቀየረም። ማስተካከያው ፩% እንኳን አይሆንም።   መክሊት መጸሐፌ ለውዷ እናቴ፤ ለበሞቴ ልዕልቴ፤ ለእሽታ ንግሥቴ ለእብዬ ሆዴ የተሰጠ ነው። ስለሆነም በባህል፤ በትውልድ፤ በትውፊት በማህበራዊ ኑሮ፤ በዕውነት ላይ ያተኮረ ነው። ፖለቲካ የለበትም።   #መፍቻ የመክሊት መጸሐፌ ማሳረጊያ ነው። ዛሬ ስክሪብቱ ላይ ሳነበው ገረመኝ። ከፊደል እርማት በስተቀር ቅንጣት አልተጨመረበትም። እንሆ መፍቻን ………   ግን የእኔ የቅንነት ውቦች ብሩሆቼም እንዴት አላችሁልኝ። ሁልጊዜም፤ ምንጊዜም ቅንነታችሁ #ቁሞ ያስተምረኛል። ዘለግ ስላለው ትዕግስታችሁ በትሁት አክብሮት አመሰግናችኋለሁኝ።    1) የነገ የፍላጎታችን #መፍቻ ምንድ ነው? 2) ወይንስ #ማን ነው? 3) ነገን ስናስብ ዛሬ ለነገ ምን እንዲያቆዬው? --- ምን #እንዲያሰናዳለት አዘጋጅተነዋል? 3) ነገ ለራሱ ብቻ...

ሾላ።

ምስል
  ሾላ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • እዚህ ሲዊዝ ሾላ አንድ የፍሬ ዐይነት ነው። እንደ እኛ የጫጫ አይደለም። የደላው ነው። ርጥቡም ደረቁም ይሸጣል። ጣፍጭነቱ ከሥኩር በላይ ነው። ብዙ የጤና ጥቅም እንዳለውም ይነገርለታል።   አዬ! ሾላ በላ ተበላ! ወፍን አታብላ ከእኔ ጋር ዋላ! በላ ተበላ ፍቅርዬ - ሾላ ፍሬህን ሳትሳሳ አብላ~~ ፍቅሬም ልክ የለው በጣም ከነፍሬህ ስገምጥህ ልዩ ጣም። ሾላ ተራ በርሬ አንተንም አባርሬ ስመለስ ከደብሬ ሞላ ጎተራዬ ኮረጆዬ። አንትን አግኝቼ ምንስ ሆኜ … እንደምታጠግበኝ ተማምኜ … ሾላ ፍሬ የትዝታ ልዩ ቀለበት ፍቅር አመጣ የልጅነት ---- የዛች ልዕልት እመቤት --- የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ህይወት --- የክብርት መሰረት --- ናፍቆቱ አለው ምህረት --- የነፍስ ድህነት።   ሾላም ...   ሜዳ በቀል ሲሆን የገጠሩም ሆነ የከተማው ነዋሪ የሚያውቀው በልጅነት ወቅት እየተለቀመ የሚበላ ፍሬ ነው።    ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/06/2026   ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም።

አባ ወኔ ባንባ …

ምስል
  ባንባ …   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • ባልዘገይ ኑሮ ለጥር ጎንደር የሄዱ ቅን ወገኖቼ ሊዩት ይችሉ ነበር። ፋሲደስ ጥምቀተባህሩ ግቢ ይገኛል። የጎንደር ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት እንደ ቅርስ እና ውርስ አይቶ ጥንቃቄ ያደርግለት ዘንድ በጥትና አሳስባለሁኝ።    አሁን አሁን ሳስበው የዓጤወቹ ቤተኛ እንደነበር አስባለሁ። በንፋስ ጊዜ ዳንሱን ፯ኛ ርግብ በር መጸሐፌ ላይ ርዕስ ሰጥቼ ከድምጽ መግራት ጋር ቀልል ባለ ግራፊክ ለማስረዳት ሞክሬያለሁኝ። ጠረኑ ፍጹም ልዩ ነው። ከፍሬው በተጨማሪ የጎንደር ዩንበርስቲወች ምርምር ቢያደርጉበት ምርጫየ ነው።   • የባንባ ፍሬ ቅጠሉ ሰፋፊ ነው። ቀጥታ ብርቱካንማ አይደለም ተቀራራቢ ነው። አመቱን ሙሉ አረንጓዴ ነው። ሲበስል ሙክክ ያለ ነው። በራሱ ጊዜ መሬት ላይ ይወድቃል። ገብያ ላይ አይቼው አላውቅም።    የስሜን እና በጌምድርን አብዛኞን የገበሬ መንደሮችን ቆላ፣ ደጋ ወይና ደጋውን በአካል አውቃቸዋለሁኝ። ባንባን ግን አይቼ አላውቅም፤ ወይራ ፤ ሾላ ፤ አጋም ቀጋ፤ ሎሚ፤ በርቶ ሎሚ፤ ኮክ በጫካው ሁሉ በነፃ ይገኛል።   • አባ ወኔ ባንባ …    ጥላ ከለላ የአንባ ከእርጋ ጋር የተግባባ ደፋር ነው የማይባባ ስኩን የማያባባም ደጀን ብርቱካናማ ዳማ - ባንባ የዓጤው የትውፊት ዘገባ ና! እንወያይ እንግባባ። ፈልጌህ ነበር ላወርድህ --- ግን አልደረስኩብህም … ግን ለምን ላይላዩን አሰኜህ? እንደ ልቤ እንዳልሆንልህ … ስለምን ይሆን መራቕህ`? በል ተሎ ውረድ ጉድ ሳይወርድ። ተሎ! - ድረስ እንድትጎርስ። ባንባ ኮረጆዬን በል ሙላ! ተስፋዬ እንዲፈካ የዓጤው የትውፊት ዘገባ ማንነቴ እንዲጎላ አጃዬ ቲፍ ብ...

እንኮይ።

ምስል
  እንኮይ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • እንኮይም ለጤና ጠቃሚ ይመስለኛል። ቅጠሉም ሻይ ቅጠል ይሆናል ብየ ነው እማስበው። እንኮይም ለጤና ጠቃሚ ይመስለኛል። ቅጠሉም ሻይ ቅጠል ይሆናል ብየ ነው እማስበው። ጣፋጭነቱ የማንጎን ያህል አይደለም። ጠረኑ የሙሽራ ዓይነት ነው።   • ጣፋጭነቱ የማንጎን ያህል አይደለም። ጠረኑ የሙሽራ ዓይነት ነው። ራህብ ያስታግሳል፥ የቸኮሌት ያህል አቅም እንዳለው አስባለሁኝ።   • እንኮይ …   አንተ ለስላሴ ሉል እንኮይ የእመየ መሳይ … የውስጥነት - አወያይ። እንክብል ጠረንህ - ያምሮት የሲሳይ የሁነት ለዛ - የሰናይ ፍሬህ ያማረ ምርጥ - ዘር ጹዑመ ጤና - `ያገር የባላገሩ - ርስተ - መንበር። ጣፈጭ - ዘለላ የእኔ - ወለላ። አልጠግብህም ሁሌም የለህም - ልግም። እንኮይ ገር - ገራገር ልዩ የልጅነት የፍቅር - ክር ትዝታ - የምታከብር ህብረ - ዘር። የአድዮ - ቤተኛ የሰንደቃችን - ማህለኛ የእኛ - ሁነኛ።   • እንኮይም …   ዱር በቀል፡ ብሩህ ቢጫማ ቀለም ያለው፡ መጠኑ እንደ ኮሽም ወይንም እንደ ትንሽዬ ቲማቲም ሲሆን እንደ ኮሽም አይሆመጥጥም። ጣፋጭ ነው። በሌላ በኩል የኮሽም ሽፋኑ ትንሽ ኮስኮስ ይላል። የእንካይ ግን በጣም ለስላሳ ነው።    ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/02-06/2026   ጊዜ...

ኮሽም።

ምስል
  ኮሽም።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • ሎሚ ከዚህ ቅዱስ መዳህኒት ይባላል። ኮሽምም ሎሚ ያለው አቅም ይኖረዋል ብየ አስባለሁኝ። ቅጠሉም እንደ ወይራ ቅጠል ለጤና ይጠቅማል ብየ አስባሁኝ። ኮሽምም ከእናት ዓለም ጎንደር የሚበቅል ፍራፍሬ ነው።   ኮሽም ... ኩርሽም አትሽኮርመም። ወርቃማው - ኮሽም ... እባክህ አትለግም? ጣፋጩ - ኮሽም ... አትበል ዝም።   ድንቡልቡል - ኮሽም ... ፈልግ እባክህ የአገር ልጅ ልባም። ፈገግ በልልኝ ዓጤ ኮሽም ... ላድርግህ! ኩርሽምሽም።   • ኮሽም ... ዱር በቀል ነው። ገበሬዎች ግን ገብያ ላይ ያውሉታል። ትንሽ ሆምጠጥ ይላል። ወደ ሎሚም ይወስደዋል። ቀለሙ ደመቅ ያለ ሉሚ ዓይነት ነው። መጠኑ ደግሞ ድቃቃ ወይንም ትንሽ ቲማቲም ያክላል።   • አትለግም ... መለገም ከሚለው ቃል የመጣ ሲሆን፣ ማድረግ፣ እየቻልክ አትስነፍ። ልበ ቅን ሁን። ትጋት ይኑርህ ለማለት ነው። ከዚህ ላይ ግን እኔ ልበላህ ፈልጌለሁ እና ለመበላትም ሆነ ለመወደድ ተዘጋጅ ለማለት ነው።   • ኩርሽምሽም ...ድቅቅ አድርጌ በፍቅር እያጣጣምኩኝ ልብላህ ለማለት ነው።    • ፈገግ በል … ሳቅ በል፣ ፍካ በል፣ ደስ ይበልህ፣ ፊትህ ይብራ …   ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/02/2026 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ ...

ዶቅማ ናልኝ የእማማ …

ምስል
  ዶቅማ ናልኝ የእማማ …   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       ***** ቅጠሉ ለሻይ ቅጠል፤ ፍሬው ለቀለም የሚጠቅም ይመስለኛል።    መልከ ... ቀና ወይንጠጅማ የእኔ ገናና የልጅነት ትዝታ ፋና። ቅርጸ¬ ~~~ የፅንሰት ሚስጢረ - ጎልማማ... እንቁላልማ። ሞላላ የሚበላ።   ዶቅማ...   … ገብያ ለገብያ ሲሄድ ወዳጁ ብዙ መንገዱ ገድ። አቤት ሲጣፍጥ ጣዕሙ ከሩቅ ሲጣራ ጠረኑ ይላል ኑ! ኑ~ ኑ~ ዶቅማ ~~~~~~ ጣፋጭ ዞማ።   ዶቅማ ...   በወለላይቱ ጎንደር አንድ የፍራፍሬ ዓይነት ነው። አንጀት የሚያለሰልስ ይመስለኛል። ቀለሙ ጥቁርማ የወይን ጠጅ ሆኖ፣ ዱር በቀል ነው፣ ነገር ግን ገብያ ላይ ይውላል - ይሸጣልም፣ ዶቅማ አንድ ኢትዮጵያዊ የሆነ የፍራ ፍሬ ዓይነት ነው።    ልክ እንደ ብርቱካን ተወዳጅም ፍሬ ነው። አብዛኛው የገጠሩ ነዋሪ የለመደው እና የሚመገበው ነው። በተጨማሪም በአመዛኙ ልጆች በፍቅር የሚበሉት ተወዳጅ ፍሬ ነው። አሁን አሁን ሳስበው ለጸጉር ቀለምም ሊሆን እንደሚችል አስባለሁኝ። ከኪሳችን ወይም ከደብተር ፖርሳችን ውስጥ እያለ ከፈረጠ ቀለሙ ቶሎ አይለቅም።   ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/06/2026   ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም።