#ኢህአፓ የ2018/ ግንቦት 24 የምርጫ ዕድሉን #ማፍሰስ አይኖርበትም የሚል እምነት አለኝ።
#ኢህአፓ የ2018/ ግንቦት 24 የምርጫ ዕድሉን #ማፍሰስ አይኖርበትም የሚል እምነት አለኝ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፰ ። #ጠብታ ። አንድ የፖለቲካ ድርጅት የመደራጀት ሚስጢሩ ለፖለቲካ ሥልጣን ነው። አንድ የፖለቲካ ድርጅት የትግሉ ስትራቴጂ መስመር ሰላማዊ ትግልን መርጦ በኢትዮጵያ ሥራ ላይ በሚገኜው ህገ - መንግሥት (ተቀበልነውም// አልተቀበልነውም) ሥር ለመሆን ከፈቀደ፤ እና የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ ፈቃዱን ከሰጠው ዕድሉን ሳያፈስ ወይንም #ሳያሻግተው ሊጠቀምበት ይገባል። ኢህአፓ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅት ታሪክ ውስጥ ብዙ የፖለቲካ ሊቃናትን ያፈራ፤ የፖለቲካ ድርጅትን ጽንሰ ሃሳብ ያስተማረ፤ ተደራጅቶም የታገለ፤ ያታገለ #የትውልድ ፓርቲ ነው። እርግጥ ነው የአደረጃጀት ባህሉ አዲስ ከመሆኑ አንፃር የተለያዩ አንጃወች በየዘመኑ ተከስተዋል። በትግሉም ብዙ የኢትዮጵያ ወጣቶች ተገብረውበታል፤ ታስረዋል፤ ተሰደዋል፤ ወዘተረፈ ፈተና አስተናግዷል። የየትኛው የኢህአፓ መሪ እንደሆን ባላውቅም አንድ የኢህአፓ አካል አገር ቤት በሰላማዊ ፓርቲነት ተመዝግቦ እየታገለ ይገኛል።ለእኔ የተፎካካሪ ፓርቲነት አቅም እንዳለውም አስባለሁኝ። የኢህአፓ ወጣት መሪወች የሚያደርጉትን ቃለ ምልልስ አዳምጣለሁኝ። እኔ እምጽፈው 4/5/6 የፖለቲካ ድርጅቶች በመቀያዬር የሚታወቁ የኢህአፓ የወቅቱ አካላትን አይደለም። እነኝህ አካላት የድርጅት የማንነት #ቀውስ ስለሚፈትናቸው ለድርጅቱ ፈተና እንጂ ትሩፋት እንደማይሆኑ አስባለሁኝ። ስለሆነም ከእነሱ እምጠብቀው በጥበጥ አድርገው አንጃ መፍጠር ወይንም መንገድ ማሳትን ነው። ሱሰኞችም ናቸው ለዘር...