ልጥፎች

EBS መሥራቹን አጣ፨

ምስል
  የምንኖረው #ለጤዛዊ ጊዜ ለአፍታ ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ይቺ ዓለም እንዲህም፤ እንዲያም ናት። ስትሞቅ /// ስትቀዘቅዝ፤ ለብ ስትል፤ /// ፍላት ሲያሰኛም እንዲህም እንዲያ ሲያሰኛት ትቆይ እና መራራ ስንብትን ጎምዛዛ ጠምቃ እንዲህ #ዕንባ ታራጫለች። ለብሰን - ስንታይ፤ ቁመን - ስንታይ፤ ስንሞግት ///ስንሞገት፤ ስንስቅ // ሲከፋን ቋሚ ጊዜ የተሰጠን ይመስለናል። ግን የአፍታወች ነን።    ጸጥ እረጭ ካለው ቅዝቃዜ ውስጥ ከተማችን ስለመሆኑ፤ ትዳር ጎጇችን ስለመሆኑ በህይወት እያለን ትዝ የማይለን ብዙወቻችን ነን። ጥልቀት ያለው መራራ ስንብት የፍጥረታት ሁሉ ተመስጥሮ አብሮን የተፈጠረ ስለመሆኑ እንዘናጋለን። ለዚህም ነው ሞት ሁልጊዜ አዲስ የሚባለው።   የሚዲያ ሰብዕና በፈተና #የታጠረ ነው። የመጨረሻው የፈተና ተጋድሎ እንዲህም፤ በዚህም ሁኔታ ይጠናቀቃል። የሚዲያ ተግባር በብክነት የተሞላ ነው። የሚዲያ ሰብዕና የመጨረሻው እረፍት በዘለቄታ እንዲህ ይጠናቀቃል። እንዲህም ይደመደማል። ይደመደማልም። የሠራ ሰብዕና፤ የተጋ ሰብዕና፤ በአዲስ ጎዳና፤ እሸት ሃሳብን አዝምሮ፤ አብስሎ ያሰበለ ሊቀ - ትጉኃን #አሻራው የተሟላ ስለሚሆን፤ ሞተ ከሚባል፤ ከድካሙ #አረፈ የሚለው ትርጉም የሚሻል ይመስለኛል። ሁላችንም ከጽንሰታችን ጀምሮ ተጓዦች ነን። እንከታተላለን።    ትልቅ ሰው በስጋ ቢለይም ሁልጊዜ ተግባሩ፤ ትጋቱ በቋሚነት ይቀጥላል። በብዙ ሁኔታ በዘርፋ በርካታ ባለሙያወችን በማብቀል እናም ተተኪ በመፍጠር የትውልድ በሆነ #ቀና ዕሳቤ ለትውልድ የሚሆን፤ የሚበረክት ተግባርን ፈጽሞ፤ በታታሪነት ተግቶ፤ አስብሎ የአረፈ ሰብዕና በሚሊዮኖች ልበ - ህሊና ው...

#ሁለት ቤተ - አብኖች #ኢህአፓን ወክለው የ2018ቱን ዓም ምርጫ እንደምወዳደሩ አስታወቁ።

  #ሁለት ቤተ - አብኖች #ኢህአፓን ወክለው የ2018ቱን ዓም ምርጫ እንደምወዳደሩ አስታወቁ።   የዘገባው ምንጭ #ሪፖርተር ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። የፓርላማ አባሉ ዶር አበባው ደስአለው እና ዶር. ይህዓለም ታምሩ (የሚያምር ሥም።) ሁለቱም ቤተ - አብኖች የነበሩ ሲሆን አሁን ኢህአፓን ወክለው በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ የምርጫ ሥርዓት ውስጥ #ሊወዳደሩ እንደወሰኑ ዘገባው ያመለክታል። በተጨማሪም ዶር. ይህዓለም ታምሩ የአዲስ አበባ የአብን ጽ/ቤት ኃላፊ እንደነበሩ መረጃው ይጠቁማል።   በውነቱ የእኔ ሁሉም ሚዲያ ጸጋዬ ራዲዮን ጨምሮ ዘገባ አይሠራበትም። ስለሆነም የምርጫ ዘገባም፤ በምርጫ ዙሪያም ያሉ ንቅናቄወችን በጥሞና መከታተሉ ይበጃል። ባለፈውም የፈጸምኩት በዝምታ ነው። አንዳንድ ኮሚክ ሁነት ሲገጥም ብቻ ነበር ሐተታ እጽፍ የነበረው። የተወዳደሩክት #ለማሸነፍ አልነበረም ልሸነፍ ነው የሚል ቧልት አዳመጥኩና ፃፍኩኝ። ሌላም "የብልጽግና አባል #አይደለሁም ግን ወክዬ እወዳደራለሁ" ያሉም ተወዳዳሪ እንዲሁ ገርሞኝ ጽፌ ነበር።    እንጂ በምርጫ ዙሪያ ብዙም መሳተፍ አልሻም። የሆነ ሆኖ በኢህአፓ ላይ ያለው የሚዲያ ጫና ገርሞኝ ስለነበር፤ አንጋፋ መሪወቹንም የኢህአፓ በአካል ስለማውቃቸው በህይወት እያሉ ወጣት ተተኪወቻቸው በፓርላማ የመወዳደር ዕድላቸውን እንዳያፈሱ ትናንት ዘለግ አድርጌ መፃፌ ይታወቃል።    በተጨማሪም "ለህዝቤ የፈየድኩት ነገር ስለለ መጪውን ምርጫ አልሳተፍም" ያሉትን ዶር ደስአለኝ ጫኔ ከምርጫ እራሳቸውን ማግለላቸውን አክብሬ ምክንያታቸው ስላላሳመነኝ ትናንት በዚህ ዙሪያ ስለፃፍኩኝ፤ የጓዶቻቸው ለመሳተፍ #መፍቀድ ተያያዥ ስለሆነ ነው ለመዘገብ የወደድኩት...

#ኢህአፓ የ2018/ ግንቦት 24 የምርጫ ዕድሉን #ማፍሰስ አይኖርበትም የሚል እምነት አለኝ።

ምስል
  #ኢህአፓ የ2018/ ግንቦት 24 የምርጫ ዕድሉን #ማፍሰስ አይኖርበትም የሚል እምነት አለኝ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       #ምዕራፍ ፲፰ ።   #ጠብታ ።   አንድ የፖለቲካ ድርጅት የመደራጀት ሚስጢሩ ለፖለቲካ ሥልጣን ነው። አንድ የፖለቲካ ድርጅት የትግሉ ስትራቴጂ መስመር ሰላማዊ ትግልን መርጦ በኢትዮጵያ ሥራ ላይ በሚገኜው ህገ - መንግሥት (ተቀበልነውም// አልተቀበልነውም) ሥር ለመሆን ከፈቀደ፤ እና የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ህጋዊ ፈቃዱን ከሰጠው ዕድሉን ሳያፈስ ወይንም #ሳያሻግተው ሊጠቀምበት ይገባል።   ኢህአፓ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ድርጅት ታሪክ ውስጥ ብዙ የፖለቲካ ሊቃናትን ያፈራ፤ የፖለቲካ ድርጅትን ጽንሰ ሃሳብ ያስተማረ፤ ተደራጅቶም የታገለ፤ ያታገለ #የትውልድ ፓርቲ ነው። እርግጥ ነው የአደረጃጀት ባህሉ አዲስ ከመሆኑ አንፃር የተለያዩ አንጃወች በየዘመኑ ተከስተዋል። በትግሉም ብዙ የኢትዮጵያ ወጣቶች ተገብረውበታል፤ ታስረዋል፤ ተሰደዋል፤ ወዘተረፈ ፈተና አስተናግዷል።   የየትኛው የኢህአፓ መሪ እንደሆን ባላውቅም አንድ የኢህአፓ አካል አገር ቤት በሰላማዊ ፓርቲነት ተመዝግቦ እየታገለ ይገኛል።ለእኔ የተፎካካሪ ፓርቲነት አቅም እንዳለውም አስባለሁኝ። የኢህአፓ ወጣት መሪወች የሚያደርጉትን ቃለ ምልልስ አዳምጣለሁኝ። እኔ እምጽፈው 4/5/6 የፖለቲካ ድርጅቶች በመቀያዬር የሚታወቁ የኢህአፓ የወቅቱ አካላትን አይደለም።    እነኝህ አካላት የድርጅት የማንነት #ቀውስ ስለሚፈትናቸው ለድርጅቱ ፈተና እንጂ ትሩፋት እንደማይሆኑ አስባለሁኝ። ስለሆነም ከእነሱ እምጠብቀው በጥበጥ አድርገው አንጃ መፍጠር ወይንም መንገድ ማሳትን ነው። ሱሰኞችም ናቸው ለዘር...

#በአገራቸው ፓርላማ #ስደት ላይ የነበሩት የህዝብ ተመራጭ እንደራሴ ዶር ደስአለኝ ጫኔ #በቃኝ! አሉ።

ምስል
  #በአገራቸው ፓርላማ #ስደት ላይ የነበሩት የህዝብ ተመራጭ እንደራሴ ዶር ደስአለኝ ጫኔ #በቃኝ ! አሉ።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፰።   የዜግነት እርቦ፤ የዜግነት ሲሶ፤ የዜግነት እኩሌታ ያዬሁበት የፓርላማ ጊዜ ነበር ዶር ደሳለኝ ጫኔ እና አራት ጓዶቻቸው በህዝብ ሙሉ ድምጽ ተመርጠው አህዱን …… ክለቱን……… ሰለስቱ……… አርባዕቱ ………፭ኛው ዓመት እንሆ በጣት የሚቆጠሩ ወራት ቀሩ።   ለኢትዮጵያ ፓርላማ #የመተንፈሻ #ቧንቧ የነበሩት የህዝብ እንደራሴው ዶር ደስአለኝ ጫኔ #በቃኝ ! ሲያንስ ነው ባይ ነኝ። ለምን? ያን ሁሉ ግልምጫ፤ ያን ሁሉ ስላቅ፤ ያን ሁሉ መዘባበቻነት፤ ያን ሁሉ ግልምጫ፤ ያን ሁሉ መታፈን፤ ያን ሁሉ የሰው ክቡሩነት የተናቀበት ሂደት ተሸክመው እዚህ መድረሳቸው የሚገርመኝ፤ የሚደንቀኝ ገጠመኝ ነበር።   እኔ በተፈጥሮዬ መጀመሪያ የማዬው #ገጽን ነው። ገጹ የተከፋ የማንኛውም ሰብዕ ሁነት ከተመለከትኩ፤ ከዛች ቅጽበት ጀምሮ #ወራጅ አለ ነው።   #እንዲህም ሆነላችሁ።    በአንድ ወቅት ህዝባዊ ስብሰባ በርን ነበር። ከቪንተርቱር በርን በራሴ ወጪ ተጓጉዤ ሄድኩኝ። የጋበዙኝ ሰወች፤ ለማደሪያም ቦታ እንደተዘጋጀልኝ ተነግሮኝ ነበር የሄድኩት። ቃል የገቡት ግን አልተገኙም። እኔ ግን ቀድሜ ተገኜሁኝ። የተፈለግሁበት መሠረታዊ ምክንያት #አሽሙር እንዳደምጥ ነበር። እኔ ሥርጉተሥላሴ የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ቁሮ እንጨት ወይንም ልጥፍ ከሰል ለመሆን መቼውንም አልፈቅድም። የራሴ እንደራሴ እራሴው ነኝ።    እናላችሁማ #ቆፍጣናዋ ጎንደሬ የሄደችው " #የፈራ ይመለስ" 500 ወጣቶች ቲሸርት በራሳቸው ወጪ አሰርተው የበዓቴ አንበሶች ህ...