ልጥፎች

ዕንባ በጎርፍነት። መታመን ሲነጥፍበት።

  ዕንባ በጎርፍነት። መታመን ሲነጥፍበት።    «… ዓይኖቼ በሰወች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኽውንን ማዳንህን አይተዋልና፤ …» (ሉቋስ ምዕራፍ ፪ ከ፳፱ ጀምሮ …)   https://www.youtube.com/watch?v=LZGo2sNn_7s&t=156s «መጨረሻውን መገመት የማይቻል አሳዛኝ ታሪክ #story #lovestory #ethiopianpodacst #ethiopia ,»   #መግቢያ ።   አመንዝራነት #ዙነት ነው። ደዌም። ስሜቱን መቆጣጠር የማይችል ሰብዕና በሞቱ ውስጥ አዘውትሮ የሚኖር ይመስለኛል። በተለይ እሱን አምነው የተከዱ ነፍሶች ግን ሰማዕታት ናቸው። ምክንያቱም የተፈጠሩበት መክሊት፤ ጥሪ፤ መልዕክት ሁሉ በመከዳታቸው ውስጥ አለና ሊደረመስ ይችላል። ለዚህ ወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው ሰብዕና በከረባቱ ይኖራል፤ በገበርዲኑም ይኖራ፤ ባለፈም የፖለቲካ ሰብዕናም ውስጥ ዘው ማለትም ይኖራል። ሁሉም ግን ወና ነው። #ቃ ያለም።   አንጎልማ ዲንቢጥም አላት። ሰውነት ህሊናዊነት ነው። ስሜትን መግዛት እንደምን ይሳናል? አመንዝራነት ህሊናን ወደ ዲንቢጥ ተፈጥሮ መልስልኝ የማለት ያህል ነው። ለዛውም በወግ በማዕረግ የተዳረ፤ የተኳለ ሰብዕና ውስጡ ጽዳት ከሌለው፤ አባትነቱም አባት አይሆንም። ባልነቱም እንዲሁ የግፋፎ ካንፓኒነት ይሆናል።   እሙኃይ ዓለምነሽ ለመጨረሻ ጊዜ ልጃቸውን የጠየቁት ---- "ትልቁ የዓለማችን #ዓውሬ ማን ነው ብለው ጠየቋት።" ዕጸገነትም የምታውቀውን ዘረዘረች። እናት መለሱላት። "የዓለማችን ትልቁ አውሬ #ሰው ነው አሏት።" እኔም እስማማለሁኝ። የምለየው የአውሬነቱ ሥራ አስኪያጅ ክፋ ሃሳብ ነው ብዬ አስባለሁኝ።   አውሬው ደግሞ አግብቶ ወግ አይቀርም ደግሞ ድጋሚ ትዳር ሲይዝ...

#ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ #ሐዋርያ ነው - ለእኔ። አዶናይወዲላን።

ምስል
      #ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ #ሐዋርያ ነው - ለእኔ። አዶናይወዲላን።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   ክፋ ሃሳብ በእጅጉ እየፈተናት በምትገኜው እቴጌ ዓለማችን ስፖርት ነፍስ ሆኖ፤ ነፍስ ሰጥቶ፤ ፍቅር ሆኖ፤ ፍቅር ሰጥቶ ይሞግተዋል ክፋ ሃሳብን። ከስፖርት ውስጥ አንዱ እግር ኳስ ነው። ዕውነተኛው የፍቅር ተፈጥሮ የሚገኘውም #ከእናት እና #ከስፖርት #ማልያ ነው ብዬ አስባለሁኝ። ለዚህ ነው አዘውትሬ ልብ ሳይሆን እናት ትሁን የፍቅር ተፈጥሮ የምለው።   በዓለማችን ክፋ ሃሳብን ሞግቶ የሚያሸንፍ፤ ዕለታዊ ተግባሩ የፍቅር ተፈጥሮ የሆነ የማስተማሪያ፤ የሚዲያ፤ ዓለም ዓቀፍ ተቋም ባይኖርም የስፖርት ማልያ ግን ይህን ኃላፊነት ለመወጣት አዘውትሮ ይጥራል።   የዓለም የሳቅ ጊዜ የዕውነተኛው አለ፤ ወይንም ተገኜ ከተባለ ከስፖርት ፍቅር እና ከእናት የሚፈልቀው ወይንም የሚመነጨው #ንጽህና ስለመሆኑ አምናለሁኝ። እግር ኳስ ፍጹም ልዩ ነው። #የሐሤት ተልዕኮ የተሰጠው። የዓለምን ሙሉ አደብ በፍቅር የሚገዛ።   እኔ እግር ኳስ እወዳለሁኝ። ለረጅም ጊዜ በአምደኝነት በተሳተፍኩባቸው ፔጆች፤ በራሴም ሚዲያ ዘገባውን እሰራለሁኝ። ማዬት በማልችልበት ጊዜ ከስደት ወደ ስደት ሂጄ የአውሮፓን እና የዓለም ዋንጫን እከታተል ነበር። በፍቅር፤ በጉጉት ከውስጤ ደስ ብሎኝ የምመለከተው የመኖር አርት ቢኖር #እግር ኳስ ነው።   የዓለምን አርቲቡርቲ፤ የዓለምን ኳኳቴ፤ የዓለምን የክፋ ሃሳብ ፈተናን ረሳ አድርጋችሁ ወደ ዕውነተኛው የመፈጠራችን ሚስጢር፤ ወደ ንጽህናችን የሚወስደን ጎዳና ቢኖር ለእኔ እግር ኳስ ነው።   የእግር ኳስ ፍቅር #አያረጅም ። የእግር ኳስ ፍቅር...

#የአገር መሪን የሥልጣን ጊዜ ስለመገደብ የእኔ ዕይታ። "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ።"

  #የአገር መሪን የሥልጣን ጊዜ ስለመገደብ የእኔ ዕይታ።    "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ።"   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   ብዙ ተቃዋሚወች ይሁኑ ተፎካካሪወች ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን አቅልሎ የማዬት የወል ባህሪ አይባቸዋለሁ። ልምድ እንደሌላቸውም ሲናገሩ አድምጫለሁኝ።    በቂ ልምድ አላቸው። ሚሊተሪ ላይ ሠርተዋል፤ በተመድ ፕሮጀክት ተሳትፈዋል፤ ከኢንሳ መስራችነትም አሉበት በዛው ተቋም መሪነቱም ታክሎ ልምድ ይገበይበታል፤ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂን በሚር ደረጃ መርተዋል፤ የኢህአዴግ የፓርላማ አባል ነበሩ፤ በኦሮሚያ የተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ሠርተዋል። ይህ በቂ ነው።    የኢትዮጵያ መሪ ከሆኑ በኋላ እሳቸው የሚያምኑበትን መስመር ተግተው ነው የሚሠሩት። ቢሮክራሲው ላይ የሉበትም መስክ ላይ፤ ፕሮጀክት ተኮር ጉዳዮችን ይወጥናሉ፤ ይፈጽማሉም። ዳሽ የሆነው ሰብአዊነት ላይ ነው የማጽናናት፤ አይዟችሁ የማለት፤ በተከፋት ቀዬ በህዝባቸው ውስጥ ተገኝተው ጥግ የመሆን አቅም አለመኖር። እስር ላይ ያለው የማይገፋ ተራራ። ሌላው ዳሽ የሆነው የቢሮ አስተዳደራዊ ሥራም ነው። በተጨማሪም የሌሎችን መከፋት #አቅለው ማዬታቸው፤ ለመፍትሄው አለመትጋታቸው ዳሽ ነው።    ጠቅላይ ሚር መለስ ዜናዊ የትኛው ተቋም ላይ ሠርተዋል? ከጫካ ህይወት ቤተ- መንግሥት። በቃ! ዕውነቱ ይሄ ነው። ያለውን #ዕውነት #ማስከፋት አያስፈልግም። ከዚህም ሌላ መሪነት ፈቃደ እግዚአብሄር፤ ቅብዓ ስለመኖሩም ማመን ያስፈልጋል።    የሆነ ሆኖ አገራዊ ምክክሩ ለምን እንዳስፈለገ፤ ከዛ በፊት ለሙከራ አቋቁመው ያፈረሷቸው ኮሚሽኖች ሁሉ በመደዴ ታስበው የተከ...