#አፍሪካዊው #የፈረንሳይ ቡድን፣ #አውሮፓዊውን #የሞሮኮ ቡድን ሁለት #ለልሙጥ ሸኜው።
#አፍሪካዊው #የፈረንሳይ ቡድን፣ #አውሮፓዊውን #የሞሮኮ ቡድን ሁለት #ለልሙጥ ሸኜው። ፈረንሳይ 2: ሞሮኮ 0 'አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። የአፍሪካን ድጋፍ ያላስፈለጋቸው የሞሮኮ መንፈስ ዛሬ የፊፋው ፕሬዚዳንት በተገኙበት ወሳኝ የጨዋታ ምዕራፍ በተካሄደው ውድድር በፈረንሳይ #ጥንግ ድርብ ነጥብ ሞሮኮወችን #በልሙጥ ተሸኝተዋል። ፈረንሳዮች በጨዋታ መግቢያ ደቂቃወች ላይ የሞከሯቸው ሁለት የግብ ጥረቶች ባይሳኩም። በተጨማሪም የቅጣት ምት አግኝቶ ማፔ #ቢስትም ፣ ማፔ ይህን አካክሶ #በ59ኛው ደቂቃ ላይ ተስፋ ቀና ብሎ ፍሰሃውን ሲያውጅ #በ65ኛው ደቂቃ ላይ ለጥንድ ድል በቁና እና ድሉ ተበሰረ። ለዛውም በመደበኛ የጨዋታ ጊዜ። በውነቱ በፈረንሳይ በኩል ብዙ ወርቅ የግብ ዕድሎች ቢሳኩ ኖሮ #አውሮፓዊው የሞሮኮ ቡድን መንፈሱ ለረጅም ጊዜ #ለሽ ይል ዘንድ ይፈረድበት ነበር። የሞሮኮ ቡድን እኔ እንደ ገመትኩት አስልተው የገቡት መደበኛውን የጨዋታ ጊዜ ተራዝሞ፣ ተጨማሪ ደቂቃ ታክሎ፣ #በፔናሊቲ መለያዬትን #የናፈቁ ይመስላሉ። #የረባ የጎል ጥረት አላደረጉም። ጨዋታው በፈረንሳይ የበላይነት #ፈርሰስ ብሎ፣ #ተረጋግቶ ነበር የተከወነው። ፈረንሳዮች ሁሎችም የኮከብነት አቅም አላቸው። ይህን አቅም በቲም ወርክ አፋፍተው እቴጌዋ ድንቡልቡሊት እንዳትከፋባቸው በወል ጥረት፣ በግል ኃላፊነት እና ተጠያቂነት #ጥፍጥ ያለ ጨዋታ የማሳየት ባህላቸው ጠንካራ ነው። ጎሉም አያመልጣቸው፣ የጨዋታ ትዕይንትም አይደርቅባቸው። #የሲዳን ተተኪወች ሁልጊዜም በጥንካሬ እየገሰገሱ ነው። ከፓራጓይ ጋር የገጠማቸው ቻሌንጅ...