ከዚህ በኋላስ? "በዋግ ኽምራ ዞን ታጣቂዎች ሁለት ወረዳዎችን በመቆጣጠራቸው በርካታ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው ተነገረ" BBC.".
"በዋግ ኽምራ ዞን ታጣቂዎች ሁለት ወረዳዎችን በመቆጣጠራቸው በርካታ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው ተነገረ" BBC. https://www.bbc.com/amharic/articles/cjeg35z91ywo 10 ሰኔ 2026 የንባብ ጊዜ: 5 ደቂቃ "በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን 'የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ' (አዴን) ታጣቂዎች አበርገሌ እና ፃግብጂ ወረዳዎችን "ሙሉ ለሙሉ" መቆጣጠራቸውን እና ማኅበረሰቡ በስጋት ሸሽቶ መፈናቀሉን የአካባቢው አስተዳደር እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ከሁለት ዓመት በፊት ከመንግሥት ጋር የሰላም ስምምነት ፈርመው የነበሩት የአገው ታጣቂዎች ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምረው ሁለት ወረዳዎችን እንደተቆጣጠሩ አምስት የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዞኑ ፀጥታ መምሪያ ተናግረዋል። የአዴን ኃላፊዎች ወረዳዎቹን እንደተቆጣጠሩ ለቢበሲ አረጋግጠው፤ ነዋሪዎች ግን አልተፈናቀሉም በማለት አስተባብለዋል። በአበርገሌ ወረዳ ሚያዚያ 12/2018 ዓ.ም. በአካባቢው ሚሊሻዎች እና በታጣቂዎች መካከል "በከባድ መሣሪያ" የታገዘ ግጭት ከተቀሰቀሰ በኋላ የአዴን ኃይሎች በከፊል ተቆጣጥረውት የነበረውን ወረዳ ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠራቸው ተነግሯል። ቀኑን ሙሉ ውሏል በተባለው ውጊያ የአዴን ኃይሎች ከ"ህውሓት ታጣቂዎች" ጋር "ተቀናጅተው" እንደተሳተፉ ነዋሪዎች እና የዞኑ አስተዳደር ለቢቢሲ አመልክተዋል። የአዴን የሚዲያ እና ኮምዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ካሴ ከህውሓት ኃይሎች ጋር ተጣምረው መዋጋታቸውን አስተባብለው፤ "አመራሮቻችንን አፍነው ለመውሰድ ሲሞክሩ" ግጭቱ ተቀስቅሷል በማለት "ተገፍተን ነው [ወደ ግጭት] የገባነው" ...