ልጥፎች

#መፍቻ ።

ምስል
  #መፍቻ ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“   #ምዕራፍ ፲፰።       #ጠብታ ።   ዛሬን ለእኔ ሰጠሁት። ሚሞሪን እያሞቀ ከሚገኘው ለህትም ከበቃው ሦስተኛው የዓዋቂወች የግጥም መድበሌ ላይ የተወሰደ ነበረ። በደራሽ ጉዳዮች፤ በሰብአዊነት ጉዳዮች፤ በኢትዮጵያ ዕናቶች አመክንዮ ጉዳዮች ላይ አበክሬ ስለምሰራ እኔን ስቶር ውስጥ ወይንም ሚሞሪው ውስጥ አስቀምጬ በፌስቡክ ለ፮ ዓመታት፤ በሚዲያ ከ፳ ዓመታት በላይ፤ በፖለቲካ ከጋሜዬ ጀምሮ ተኖረበት። ለእኔ ቀን ሰጥቼው አላውቅም። ይህ ሚዲያ የእኔን እኔም ላስተዋውቀው ፈለግሁኝ። ስለሆነም ዛሬን አጠገብኩት። ጹሁፎቹም ሆኑ ግጥሞቹ ከ፲፭ ዓመታት በላይ የቆዩ ናቸው። ሳድስ ላይ ስለምገድፍ እሱን እና አንዳንድ ጉዳዮችን ለማጠናከር ሞክሬያለሁኝ። እርዕሶች ጭብጡ አልተቀየረም። ማስተካከያው ፩% እንኳን አይሆንም።   መክሊት መጸሐፌ ለውዷ እናቴ፤ ለበሞቴ ልዕልቴ፤ ለእሽታ ንግሥቴ ለእብዬ ሆዴ የተሰጠ ነው። ስለሆነም በባህል፤ በትውልድ፤ በትውፊት በማህበራዊ ኑሮ፤ በዕውነት ላይ ያተኮረ ነው። ፖለቲካ የለበትም።   #መፍቻ የመክሊት መጸሐፌ ማሳረጊያ ነው። ዛሬ ስክሪብቱ ላይ ሳነበው ገረመኝ። ከፊደል እርማት በስተቀር ቅንጣት አልተጨመረበትም። እንሆ መፍቻን ………   ግን የእኔ የቅንነት ውቦች ብሩሆቼም እንዴት አላችሁልኝ። ሁልጊዜም፤ ምንጊዜም ቅንነታችሁ #ቁሞ ያስተምረኛል። ዘለግ ስላለው ትዕግስታችሁ በትሁት አክብሮት አመሰግናችኋለሁኝ።    1) የነገ የፍላጎታችን #መፍቻ ምንድ ነው? 2) ወይንስ #ማን ነው? 3) ነገን ስናስብ ዛሬ ለነገ ምን እንዲያቆዬው? --- ምን #እንዲያሰናዳለት አዘጋጅተነዋል? 3) ነገ ለራሱ ብቻ...

ሾላ።

ምስል
  ሾላ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • እዚህ ሲዊዝ ሾላ አንድ የፍሬ ዐይነት ነው። እንደ እኛ የጫጫ አይደለም። የደላው ነው። ርጥቡም ደረቁም ይሸጣል። ጣፍጭነቱ ከሥኩር በላይ ነው። ብዙ የጤና ጥቅም እንዳለውም ይነገርለታል።   አዬ! ሾላ በላ ተበላ! ወፍን አታብላ ከእኔ ጋር ዋላ! በላ ተበላ ፍቅርዬ - ሾላ ፍሬህን ሳትሳሳ አብላ~~ ፍቅሬም ልክ የለው በጣም ከነፍሬህ ስገምጥህ ልዩ ጣም። ሾላ ተራ በርሬ አንተንም አባርሬ ስመለስ ከደብሬ ሞላ ጎተራዬ ኮረጆዬ። አንትን አግኝቼ ምንስ ሆኜ … እንደምታጠግበኝ ተማምኜ … ሾላ ፍሬ የትዝታ ልዩ ቀለበት ፍቅር አመጣ የልጅነት ---- የዛች ልዕልት እመቤት --- የእናት ሀገር ኢትዮጵያ ህይወት --- የክብርት መሰረት --- ናፍቆቱ አለው ምህረት --- የነፍስ ድህነት።   ሾላም ...   ሜዳ በቀል ሲሆን የገጠሩም ሆነ የከተማው ነዋሪ የሚያውቀው በልጅነት ወቅት እየተለቀመ የሚበላ ፍሬ ነው።    ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/06/2026   ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም።

አባ ወኔ ባንባ …

ምስል
  ባንባ …   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • ባልዘገይ ኑሮ ለጥር ጎንደር የሄዱ ቅን ወገኖቼ ሊዩት ይችሉ ነበር። ፋሲደስ ጥምቀተባህሩ ግቢ ይገኛል። የጎንደር ከተማ ከንቲባ ጽህፈት ቤት እንደ ቅርስ እና ውርስ አይቶ ጥንቃቄ ያደርግለት ዘንድ በጥትና አሳስባለሁኝ።    አሁን አሁን ሳስበው የዓጤወቹ ቤተኛ እንደነበር አስባለሁ። በንፋስ ጊዜ ዳንሱን ፯ኛ ርግብ በር መጸሐፌ ላይ ርዕስ ሰጥቼ ከድምጽ መግራት ጋር ቀልል ባለ ግራፊክ ለማስረዳት ሞክሬያለሁኝ። ጠረኑ ፍጹም ልዩ ነው። ከፍሬው በተጨማሪ የጎንደር ዩንበርስቲወች ምርምር ቢያደርጉበት ምርጫየ ነው።   • የባንባ ፍሬ ቅጠሉ ሰፋፊ ነው። ቀጥታ ብርቱካንማ አይደለም ተቀራራቢ ነው። አመቱን ሙሉ አረንጓዴ ነው። ሲበስል ሙክክ ያለ ነው። በራሱ ጊዜ መሬት ላይ ይወድቃል። ገብያ ላይ አይቼው አላውቅም።    የስሜን እና በጌምድርን አብዛኞን የገበሬ መንደሮችን ቆላ፣ ደጋ ወይና ደጋውን በአካል አውቃቸዋለሁኝ። ባንባን ግን አይቼ አላውቅም፤ ወይራ ፤ ሾላ ፤ አጋም ቀጋ፤ ሎሚ፤ በርቶ ሎሚ፤ ኮክ በጫካው ሁሉ በነፃ ይገኛል።   • አባ ወኔ ባንባ …    ጥላ ከለላ የአንባ ከእርጋ ጋር የተግባባ ደፋር ነው የማይባባ ስኩን የማያባባም ደጀን ብርቱካናማ ዳማ - ባንባ የዓጤው የትውፊት ዘገባ ና! እንወያይ እንግባባ። ፈልጌህ ነበር ላወርድህ --- ግን አልደረስኩብህም … ግን ለምን ላይላዩን አሰኜህ? እንደ ልቤ እንዳልሆንልህ … ስለምን ይሆን መራቕህ`? በል ተሎ ውረድ ጉድ ሳይወርድ። ተሎ! - ድረስ እንድትጎርስ። ባንባ ኮረጆዬን በል ሙላ! ተስፋዬ እንዲፈካ የዓጤው የትውፊት ዘገባ ማንነቴ እንዲጎላ አጃዬ ቲፍ ብ...

እንኮይ።

ምስል
  እንኮይ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • እንኮይም ለጤና ጠቃሚ ይመስለኛል። ቅጠሉም ሻይ ቅጠል ይሆናል ብየ ነው እማስበው። እንኮይም ለጤና ጠቃሚ ይመስለኛል። ቅጠሉም ሻይ ቅጠል ይሆናል ብየ ነው እማስበው። ጣፋጭነቱ የማንጎን ያህል አይደለም። ጠረኑ የሙሽራ ዓይነት ነው።   • ጣፋጭነቱ የማንጎን ያህል አይደለም። ጠረኑ የሙሽራ ዓይነት ነው። ራህብ ያስታግሳል፥ የቸኮሌት ያህል አቅም እንዳለው አስባለሁኝ።   • እንኮይ …   አንተ ለስላሴ ሉል እንኮይ የእመየ መሳይ … የውስጥነት - አወያይ። እንክብል ጠረንህ - ያምሮት የሲሳይ የሁነት ለዛ - የሰናይ ፍሬህ ያማረ ምርጥ - ዘር ጹዑመ ጤና - `ያገር የባላገሩ - ርስተ - መንበር። ጣፈጭ - ዘለላ የእኔ - ወለላ። አልጠግብህም ሁሌም የለህም - ልግም። እንኮይ ገር - ገራገር ልዩ የልጅነት የፍቅር - ክር ትዝታ - የምታከብር ህብረ - ዘር። የአድዮ - ቤተኛ የሰንደቃችን - ማህለኛ የእኛ - ሁነኛ።   • እንኮይም …   ዱር በቀል፡ ብሩህ ቢጫማ ቀለም ያለው፡ መጠኑ እንደ ኮሽም ወይንም እንደ ትንሽዬ ቲማቲም ሲሆን እንደ ኮሽም አይሆመጥጥም። ጣፋጭ ነው። በሌላ በኩል የኮሽም ሽፋኑ ትንሽ ኮስኮስ ይላል። የእንካይ ግን በጣም ለስላሳ ነው።    ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/02-06/2026   ጊዜ...

ኮሽም።

ምስል
  ኮሽም።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       • ሎሚ ከዚህ ቅዱስ መዳህኒት ይባላል። ኮሽምም ሎሚ ያለው አቅም ይኖረዋል ብየ አስባለሁኝ። ቅጠሉም እንደ ወይራ ቅጠል ለጤና ይጠቅማል ብየ አስባሁኝ። ኮሽምም ከእናት ዓለም ጎንደር የሚበቅል ፍራፍሬ ነው።   ኮሽም ... ኩርሽም አትሽኮርመም። ወርቃማው - ኮሽም ... እባክህ አትለግም? ጣፋጩ - ኮሽም ... አትበል ዝም።   ድንቡልቡል - ኮሽም ... ፈልግ እባክህ የአገር ልጅ ልባም። ፈገግ በልልኝ ዓጤ ኮሽም ... ላድርግህ! ኩርሽምሽም።   • ኮሽም ... ዱር በቀል ነው። ገበሬዎች ግን ገብያ ላይ ያውሉታል። ትንሽ ሆምጠጥ ይላል። ወደ ሎሚም ይወስደዋል። ቀለሙ ደመቅ ያለ ሉሚ ዓይነት ነው። መጠኑ ደግሞ ድቃቃ ወይንም ትንሽ ቲማቲም ያክላል።   • አትለግም ... መለገም ከሚለው ቃል የመጣ ሲሆን፣ ማድረግ፣ እየቻልክ አትስነፍ። ልበ ቅን ሁን። ትጋት ይኑርህ ለማለት ነው። ከዚህ ላይ ግን እኔ ልበላህ ፈልጌለሁ እና ለመበላትም ሆነ ለመወደድ ተዘጋጅ ለማለት ነው።   • ኩርሽምሽም ...ድቅቅ አድርጌ በፍቅር እያጣጣምኩኝ ልብላህ ለማለት ነው።    • ፈገግ በል … ሳቅ በል፣ ፍካ በል፣ ደስ ይበልህ፣ ፊትህ ይብራ …   ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/02/2026 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ ...

ዶቅማ ናልኝ የእማማ …

ምስል
  ዶቅማ ናልኝ የእማማ …   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“       ***** ቅጠሉ ለሻይ ቅጠል፤ ፍሬው ለቀለም የሚጠቅም ይመስለኛል።    መልከ ... ቀና ወይንጠጅማ የእኔ ገናና የልጅነት ትዝታ ፋና። ቅርጸ¬ ~~~ የፅንሰት ሚስጢረ - ጎልማማ... እንቁላልማ። ሞላላ የሚበላ።   ዶቅማ...   … ገብያ ለገብያ ሲሄድ ወዳጁ ብዙ መንገዱ ገድ። አቤት ሲጣፍጥ ጣዕሙ ከሩቅ ሲጣራ ጠረኑ ይላል ኑ! ኑ~ ኑ~ ዶቅማ ~~~~~~ ጣፋጭ ዞማ።   ዶቅማ ...   በወለላይቱ ጎንደር አንድ የፍራፍሬ ዓይነት ነው። አንጀት የሚያለሰልስ ይመስለኛል። ቀለሙ ጥቁርማ የወይን ጠጅ ሆኖ፣ ዱር በቀል ነው፣ ነገር ግን ገብያ ላይ ይውላል - ይሸጣልም፣ ዶቅማ አንድ ኢትዮጵያዊ የሆነ የፍራ ፍሬ ዓይነት ነው።    ልክ እንደ ብርቱካን ተወዳጅም ፍሬ ነው። አብዛኛው የገጠሩ ነዋሪ የለመደው እና የሚመገበው ነው። በተጨማሪም በአመዛኙ ልጆች በፍቅር የሚበሉት ተወዳጅ ፍሬ ነው። አሁን አሁን ሳስበው ለጸጉር ቀለምም ሊሆን እንደሚችል አስባለሁኝ። ከኪሳችን ወይም ከደብተር ፖርሳችን ውስጥ እያለ ከፈረጠ ቀለሙ ቶሎ አይለቅም።   ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/06/2026   ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም።

ወረተኝነትን ።

  ወረተኝነትን ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“ መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር ብቻ መጀመር…   --- የጀመሩትን ሳይጨርሱ አዲስ መጀመር መጀመር ብቻ መጀመር ... ወረተኝነትን መዘመር ቋሚ ባህሪን መወርወር ነውር ነው ነውር ማንነትን የሚሰረስር በርብር።    • ወረተኝነት ...   ፀያፍ ባህሪ ነው። አንድ ሰው የጀመረውን ፈፅሞ አዲስ መጀመር ሲገባው ሁልጊዜ ዬጀመረውን ሳይጨርስ እንደገና ደግሞ አዲስ መጀር ጥሩ ያልሆነ ባህሪ ነው።   ልጆች ጓደኛም ሲይዙ ቋሚ በሆነ ባህሪ ከጓደኞቻቸው ጋር በፍቅር ለረጅም ጊዜ መቆዬት አለባቸው። በዬጊዜው ከአዳዲስ ጓደኛ ጋራ የሚጓዙ ከሆነ ብዙም ጥሩ አይደለም።   በተለይ ጥሩ ካልሆኑት ጋደኞች አዳዲስ ባህሪያትን እዬወሰዱ ተፈሮዊ ባህሪያቸው ሊይጎብጥ ይችላል። በሌላ በኩልም በዬጊዜው መጀማመር ጊዜንም ይበላል ተፅእኖም አለው። ወላጆችም ልጆች ከወረት ጋር እንዳይጣበቁ በቅርብ መርዳት ይኖርባቸዋል።    • ነውር ...   እጅግ በማህበርሰቡ ዘንድ የተጠላ የተወገዘ የማይወደድ የተከለከለ ፀባይ ማለት ልቻል ይሆን።   ሰኔ 14 ቀን 2001 ዓ.ም ክላይነአንደልፊንገን ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ...

ብሩህ ህይወትስ ….

ምስል
  ብሩህ ህይወትስ ….   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“     እዮራዊው ዘዴ ነው የክቴ፤ ዝባድ ውዴ። ልበ-ሙሉነት የውስጣዊነት ስስቴ በራስ መተማመን የመስተጋብር ህብስቴ የጀግንነት ቤተ - ስልቴ።   ማስተዋል ቢሆን የጎዳናየ - ድሌ ነው የደሜ - ሞራላዊው የአደራ ------ ውሌ። መታገስ . ም . እኮ ይምጣልኝ ስስቴ ..... ነው ዘንጣፋ ልስልሴ የግርማ ሞገስ ግሤ የክብር ካባ ልብሴ።   ጥሩ ዐይነት ነው ብር አንባሬ የአወንታዊነት ማተብ የክሬ። የቀለሜ --- ቀንድሌ --- ዓውድ ዐመቴ --- ትህትናት ሆይ! አለልኝ፤ መጠሬየ የአንጀቴ ስዋሰው ግጥሜ፤ ማድመጥ … ቢሆን … ክህሎቴ ፈርጤ፤ ከሁሉ የሚበልጥ የልኬ፤ ዬህሊናጆሮ ልዩ ጌጥ።   - የደግነት ዓውራነት … ትጉህነትም አለህኝ አብነት ... ... የትውልዱ ግንባታ መሰረት! የተስፋ ቅመም የህብረት ዀህተ - ብርኃናት።   * አብነት ... ለጥሩ እና ለመልካም ነገር አርያ፡ ምሳሌ መሆን ማለት ነው።    ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።   ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/06/2026 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም።

ወረተኝነትን ።

  ወረተኝነትን ።   “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“   መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር መጀመር ብቻ መጀመር…   --- የጀመሩትን ሳይጨርሱ አዲስ መጀመር መጀመር ብቻ መጀመር ... ወረተኝነትን መዘመር ቋሚ ባህሪን መወርወር ነውር ነው ነውር ማንነትን የሚሰረስር በርብር።    • ወረተኝነት ...   ፀያፍ ባህሪ ነው። አንድ ሰው የጀመረውን ፈፅሞ አዲስ መጀመር ሲገባው ሁልጊዜ ዬጀመረውን ሳይጨርስ እንደገና ደግሞ አዲስ መጀር ጥሩ ያልሆነ ባህሪ ነው።   ልጆች ጓደኛም ሲይዙ ቋሚ በሆነ ባህሪ ከጓደኞቻቸው ጋር በፍቅር ለረጅም ጊዜ መቆዬት አለባቸው። በዬጊዜው ከአዳዲስ ጓደኛ ጋራ የሚጓዙ ከሆነ ብዙም ጥሩ አይደለም።   በተለይ ጥሩ ካልሆኑት ጋደኞች አዳዲስ ባህሪያትን እዬወሰዱ ተፈሮዊ ባህሪያቸው ሊይጎብጥ ይችላል። በሌላ በኩልም በዬጊዜው መጀማመር ጊዜንም ይበላል ተፅእኖም አለው። ወላጆችም ልጆች ከወረት ጋር እንዳይጣበቁ በቅርብ መርዳት ይኖርባቸዋል።    • ነውር ...   እጅግ በማህበርሰቡ ዘንድ የተጠላ የተወገዘ የማይወደድ የተከለከለ ፀባይ ማለት ልቻል ይሆን።   ሰኔ 14 ቀን 2001 ዓ.ም ክላይነአንደልፊንገን ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን...

„ላሜ ... ቦራ“

ምስል
  „ላሜ ... ቦራ“         “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“   „ላሜ ቦራ“ ...   የ ~~ አባቴን ነገር አደራ የ ~~ እናቴን ነገር አደራ የ ~~ እህቴን ነገር አደራ የ ~~ ወንድሜን ነገር አደራ!   „ላሜ ቦራ“ . .. የ ~~ እቴቴን ነገር አደራ የ ~~ አባዬን ነገር አደራ የ ~~ እታታን ነገር አደራ የ ~~ ወለላን ነገር አደራ!   „ላሜ ቦራ“ ...   የ ~~ ጋሽዬን ነገር አደራ የ ~~ መኩሬዬን ነገር አደራ የ ~~ ጥላዬን ነገር አደራ የ ~~ ክንድዬን ነገር አደራ!   „ላሜ ቦራ“ ...   የ ~~ እቴ አንጀቴን ነገር አደራ የ ~~ እታለምን ነገር አደራ የ ~~ እትዬን ነገር አደራ የ ~~ እቴዋዬን ነገር አደራ!   „ላሜ ቦራ“ ...   የ ~~ ትልቋን ማሚ ነገር አደራ! የ ~~ ታሪኬን ነገር አደራ! የ ~~ ባንዴራዬን ነገር አደራ! የ~~~~~~ የ አፈሬን ነገር አደራ   „ላሜ ቦራ“ ~~~~   እንዳትረሽ አደራ አደራ! ተቀባይ ሁኝ አደራ! አደራ! አውጭም ሆኝ አደራ!   • „ላሜ ቦራ“ ...    ላሜ ቦራ በልጅነቴ አንድ መጽሐፍ ውስጥ ያገኛሁት ታሪክ ነው። ታሪኩ ... አንዲት ወላጅ ልጆቿን ትታ እንድትሄድ ሞት ያስገድዳታል። በዚያ ወቅት ጭንቀት በያዛት ጊዜ ላሜ ቦራ የምተባለውን ላሟን ትጠራ...

የዕውቀት ሀይቅ ጥልቅ።

ምስል
    “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“   የዕውቀት ሀይቅ ጥልቅ።   ምንም አያሳፍራም መጠየቅ? ያልገባኝን ብጠይቅ ... ዕውቀት እንደ ሆነ አያልቅ። ዕውቀት ምንጊዜም ነው--- ብርቅ ጣፈጭ መረቅ የሚያደምቅ። የዕውቀት ሀብል ወርቅ ሁልጊዜ የሚያፈልቅ። ድንቁርናን ያደቀቀ ስንፍናን ያማቀቀ ጥብብን ያጠለቀ። ፍጹም ደማቅ! ነው ትልቅ! የሚያልቅ ማይጠገብ ድንቅ የዕውቀት ሀይቅ። ነው ጥልቅ! ዓለምን የሚያደምቅ ቀለማም የሚያበራ ፍልቅ፣ የማያልቅ! * ማላቅ … ትልቅ ፣ ታዋቂ የሚያደርግ። የሚያስከብር: * ዕወቀት ... ከትምህርት የሚገኝ፣ የሰለጠነ አእምሮ ውጤት ነው። ሌባ የማይዘርፈው የህሊና ሀብትም ነው። በሁሉም የሙያ ዘርፎች መሰረቱ ጥልቅ ሰፊ ነው። ይህ በቀለም ትምህርት ወይንም ሃይማኖት ገብ በሆነ ሁኔታ የሚገኝ የዕውቀት ዘርፍን ይተረጉማል። ሊቃውንት የሚባሉ መደቦችንም ይፈጥራል። ከዚህ ውጪ ግን በፈጣሪ ጸጋ ከምንም የእውቀት ዘርፍ ጋር ሳይገናኝ እስከ ዊዝደም የሚያደርስ የዕውቀት ዐይነት ይኖራል፨ ይህ ሊህቅነት ይባላል። ኢትዮጵያን ያበጃት ይህ የማይመረመር የፈጣሪ ሥጦታ ልቅና ነው። ዘመን አመጣሹ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ይህን ዕውቅና አይሰጠውም። ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን። ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02/02/2026 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። ዕውነት ወጌሻ አያስፈልገውም።