ልጥፎች

Eine neue Friedens Arbeitsgruppe ist notwendig, um dieses globale Problem zu lösen.

ምስል
  ·        Eine neue Friedens Arbeitsgruppe ist notwendig, um dieses globale Problem zu lösen.     ·         Einleitung.  Sie sind bei mir. Mir gefallen ihre Hörfähigkeiten. Ich bin von ihren politischen und philosophischen Fähigkeiten beeindruckt. Die Art und Weise, wie Sie Mutterschaft in Ihre politische Führung integriert haben, ist erstaunlich; das ist meine Universität.  Ihre Persönlichkeit selbst ist eine Institution. Der Respekt und die Aufmerksamkeit, die sie allen Menschen entgegenbringen, sind erstaunlich; daher ist diese Begabung mein Alphabet.  Sie sind ein fähiger und fleißiger Politiker, den man in 100 Jahren nicht wiedersehen wird. Sie sind eine besondere Belohnung für unsere Zeit. ·         Unsere Welt braucht Trost.  Unsere ganze Welt ist im Moment krank. Unsere Welt trauert. Unsere Welt braucht einen Beruhigter. Unsere Welt braucht einen Vermittler. Deshal...

#ብልጽግና 50+ አግኝቶ ያሸንፋል። ስለሆነም #ብልፄው የስጋት ድግስን #የምርጫ መሳሪያው ሊያደርግ ፈጽሞ አይገባም።

ምስል
  #ብልጽግና 50+ አግኝቶ ያሸንፋል። ስለሆነም #ብልፄው የስጋት ድግስን #የምርጫ መሳሪያው ሊያደርግ ፈጽሞ አይገባም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ብልፅግና የ2018ትን ፯ኛ አገራዊ ምርጫን 50+ አምጥቶ ምርጫውን #ደልደል ብሎ ማሸነፍ ይችላል። ግን ነገር ግን የስጋት፤ የጭንቀት፤ የፍርሃትን መሳሪያነት ግን ሊተው ይገባል። ስጋት፤ ጭንቀት፤ ፍርሃት መፍጠር የብልጽግና ቋሚ ዘዴው ነው።   የ2013 ዓም ምርጫ ከመድረሱ በፊት ሙሉ ኦሮምያ፤ ስሜን ሽዋ ነደዋል። ያ …… ጭንቀት፤ ያ ……… ፍርሃት፤ ያ ……… "መጡባችሁ" አቅም ፈጥሮ ብልጽግናና ደልደል ብሎ፤ ኮራ ብሎ እንዲያሸንፍ አደረገው። ብልጽግናን ተመራጭ ያደረገው ቀውስ ነው። ብልጽግና ቀውሰኛ ፓርቲ ነው። የወረሰው ከፈጣሪው ከህወሃት ነው።    የዓለም ሚዲያወች የ2013 ዓም ምርጫው #በሰላም ተጠናቀቀ ሲሉም ተደመጡ። አይፈረድባቸውም። የአገራችን ፖለቲከኛም "ከገመትኩት በላይ ምርጫው በሰላም ተጠናቀቀ" ሲሉ አዳመጥኩኝ።   በወቅቱ ጽፌበታለሁኝ። የምርጫው ሽርጉድ ከመጀመራቸው በፊት ብዙ አስጨናቂ ክስተቶች ነበሩ። እነዛ አስጨናቂ ክስተቶች ከብልጽግና ሌላ ማንም የለንም ብሎ ህዝብ ብልጽግናን ተሰልፎ እንዲመርጥ አደረገው። ትወናው ይህ ነበር። የተሻለም ተፎካካሪ ነበር ለማለትም ይከብዳል። የኢትዮጵያ ፖለቲካ የድል መስመር ተስፋ ሁልጊዜ #እንደቆዘመ ነው።   የሆነ ሆኖ በ2013 ዓም በምርጫው ሰሞን ታጣቂወች ጸጥ ረጭ አሉ። ማገት የለ። መንገድ መዝጋት የለ። የሰው ግድያ የከተሞች ቃጠሎ የለ። ወቅቱ ጭምት ሆነ። ከወቅቱ ከፋኝ ኃይል ጋር በትብብር በዓይን #ጥቅሻ ስለሚግባቡ ብልጽግና የልቡ ደርሶ ተመረጠ። ...

እስኪ ልጅ ጋሻው መርሻ ይሞገት። በምን የመረጃ ጥናት 95% የአማራ ክልል ሰላም ነው እንዳለ አልገባኝም።

ምስል
  እስኪ ልጅ ጋሻው መርሻ ይሞገት። በምን የመረጃ ጥናት 95% የአማራ ክልል ሰላም ነው እንዳለ አልገባኝም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #እፍታ ።   አብን ነፍሱ ስለመኖሩ አላወቅኩም። ስለዚህ ሙግቴ በግለሰባዊ ዕይታ ብቻ ቢሆን እፈልጋለሁኝ። ግን ብዕሬ ከፈቀደች እና ካሰኛት ሳይለንት ዲስክርምኔሽን አልፈጽምባትም። እንዳሰኛ ትሰጥስጠው።   #ጠብታ ።   ልጅ ጋሻው መርሻ አንዳቤቴ ነው ሲባል ሰምቻለሁኝ። አንዳቤት ለእናት አገሩ ለኢትዮጵያ በየዘመኑ አርበኛ ማፍራት፤ የቤተክህነት ሊቀ - ሊቃውንትን ለእናታችን ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ማበርከት ተመክሮው ቢሆንም፤ እንደ ልጅ ጋሻው መርሻ #ፈንገጥ ያለ ሃሳብ አቅራባ ግን ሰምቼ አላውቅም። ስለሆነም አቶ ጋሻው መርሻን ሳዳምጠው ሁልጊዜ "የአንድአቤት" ሥያሜ ይገርመኛል።   አንድአቤትን በአካል አውቀዋለሁኝ። ብዙውን የጎንደርን ቀበሌ መንደሮች በእግሬ እየተጓዝኩ አውቃቸዋለሁ። የአንዳቤት የማይረሳኝ እርጎው ነው። ዛሬ የቅኒት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ቄራ የሆነው አርሲ ጢቾ አውራጃ አምኛ ወረዳ በተመሳሳይ የተመገብኩትን እርጎ አንዳቤት ላይ አግኝቸዋለሁ። እርጎ ከምለው አንጠልጥዬ በክብር የቅቤ እርጎ ብለው ዕውነቱን ያደረጀዋል።   የአንደቤትን ገበሬወች፤ የሴቶች ማህበር እና የወጣቶች ማህበርን አመራር ሳወያያቸው አንድአቤት እንደ ሥሙ ሆኖ ነበር ያገኜሁትኝ። እናቴን የእሽታ ልዕልቴን ለምን አንድአቤት ተባለ ብዬ ከሥራ ወደ ጎንደር ስመለስ ጠዬቅኳት። እሷም ከቤተሰብ የሰማችውን ነገረችኝ። በጥንት ጊዜ ገዢወች እየተዘዋወሩ ነበር ፍርድ የሚሰጡት።    አንድአቤትም እንደሌሎቹ ባድማወች የተጉላላ ፍትህ በማጣት የተቸገረ፤ ፍርድ የጎ...