ልጥፎች

#ለመክሰስ ያልበቃን፤ ይህ ተይዞ ነው #ስንካሰስ ውለን የምናድረው። ቤታቸውን እስኪ #ከውስጡ ሆነን እንየው። ሰውኛነት ከእኛ ጋር ከሆነ።

ምስል
  #ለመክሰስ ያልበቃን፤ ይህ ተይዞ ነው #ስንካሰስ ውለን የምናድረው። ቤታቸውን እስኪ #ከውስጡ ሆነን እንየው። ሰውኛነት ከእኛ ጋር ከሆነ።    "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፰።       #ለመክሰስ ያልበቃን፤ ይህ ተይዞ ነው #ስንካሰስ ውለን የምናድረው። ቤታቸውን እስኪ #ከውስጡ ሆነን እንየው። ሰውኛነት ከእኛ ጋር ከሆነ። "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።" #ምዕራፍ ፲፰። #ስንት #እኛወች ይሆን #ያለነው ? #ስንትስ #ስንቶችስ ነን። ቀና ብሎ ለመሄድስ ያስችለን ይሆን?? አደጋው ብቻ አይደለም። #መኖራቸው ብዙ ይናገራል። የለበሱት፤ የቤታቸው ሁኔታ ይናገራል። የከረባት፤ የገበርዲን፤ የሽብሽቦ፤ የሚኒ፤ የኩላኩል፤ የልብስ ፋሽን፤ የስታይሊንግ ዓይነታችን እና #ዕውነቱ #ገብያ ላይ ሲሆን እኛ ይህን ኑሮ እንመስላለን። ቢቀድም የውስጣችን መጎሳቆል፤ እኛን እና እኛን የሚያፎካክር፤ የሚያቧክሰን፤ ፊት የሚያዞር፤ ከመቃብርህ፤ ከመቃብሬ የሚያስብለን ምንም ፋክት፤ ምንም ዕውነት ባልኖረ ነበር። ከዚህ በላይ የእኛነት ገላጭ ራዲዮሎጂ የለምና። ልብ እያለን በልባችን ላይ #ሸፍተን ፤ ማስተዋል ተሰጥቶን በቅጽበታዊነት ስንካሰስ ዘመኑ እንሆ የተደከመበት፤ የተለፋበት በግልም በጋራም የተለፋበት፤ ሳያፈራ፤ ወቅታት #ዕንቡጣቸው ጠውልጎ፤ ወራት ቡቃያውን #ማስቻል አቅቷቸው፤ በሳምንታት ዘሩ #ለችግኝ ሳይደርስ እዛው መክኖ ይቀራል። ያፈሰስነው - ጉልበት፤ የምንጋጭበት ወዘተረፈ ገመና፤ በከንቱ የባከነው አቅም፤ ወጣትነታችን ተምሎበት መኖ የቀረበት ዕውነቱ ይህ ነው፤ በምስሉ የምታዩት። ይህም ሆኖ፤ ዛሬም እኛ ግን እራሳችን #ሽሽት ላይ ነን። እኛን በእኛ ውስጥ እንዳናዬው ግርዶሹ ዕውነትን፤...

#እኔን። #የጋሞሞይቱ #ገራገሯ #እንስፍስፏ #እናት እናት ሆይ!

ምስል
  #እኔን ።    #የኢትዮጵያ መንግሥት፤ #የኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት፤ #የኢትዮጵያ ሴቶች፤ በጋራ እና በወል ብሄራዊ ንቅናቄ ሊያደርጉበት የሚገባ እጅግ አሰቃቂ ክስተት ነው።    #ለመሆኑ ----    #የጋሞሞይቱ #ገራገሯ #እንስፍስፏ #እናት እናት ሆይ! እንደምን ውለሽ አደርሽ ወይ?   "አቤቱ አምላካችን ሆይ! እንደ ቸርነትህ ብዛት ምህረትን ላክልን።" አሜን።       #የጋምይቱ ደጊቱ እናትዋ ሆይ!   ይህን የመሰለ የሰው ልጅ ሊሸከመው #የማችልወን አሳር በየትኛው አቅምሽ ቻልሽው ይሆን - አንቺ የደጋጎች እናት? ልበ ንጹኋ የጋሞ እናት ሆይ! እንደምንስ #መሽቶ ይነጋልሽ ይሆን?    ሳታስቢው፤ ሳታቅጂው ይህን የመሰለ የዕንባ #ናዳን እንደምን ተሸከምሽው ይሆን? እንደምንስ? እንዴትስ ባለ ሁኔታ በዚህች ደቂቃ ትሆኚ ይሆን?   እናት ሆይ! ማን ካጠገብሽ አለ? ማንስ በቅርበት #እያጽናናሽ ይሆን? ማንስ #አይዞሽ እያለሽ ይሆን?   በዚህ ሁለመናው በከበደ፤ ሁለመናው በጨለመ #ጨቀጨቅ ማት ውስጥ ሆነሽ ምን ታስቢ ይሆን? #እኔን ! #እኔን ! አንቺ ከልተመታሜ፤ አንቺ ባተሌ፤ አንች ትጉህ፤ አንቺ #የገርነት መለኪያ እንዴት እየሆንሽ ይሆን? ፈጣሪ አምላክ የራሄል #ዕንባ ያዳመጠ አምላክ ለአንቺ ይደርስልሽ ዘንድ እማጸነዋለሁኝ።   ዕንባሽ፤ ጭንቀትሽ፤ ስቃይሽ፤ ሃዘንሽ ሁሉ ድቅን ይልብኛል። አንቺ ብርቱ የጋሞ እናት ሆይ! እግዚአብሄር አምላክ #መጽናናቱን ይስጥሽ። አሜን።   አንቺ #ገራገር የጋሞ እናት ይህን መከራ ፈጣሪ አምላክ #የመጨረሻ ያድርግልሽ። አሜን። አንቺ ደግ #የጋሞዊቱ ሩህሩ...

ኢትዮጵያ የየትኛውም አገር #ፖስተኛ አይደለችም። ፈላስፊቷ ኢትዮጵያ በአንድ የፖለቲካ ድርጅት #አትወከልም፤ ልትወቀስም ይሁን ስሟ ሊጎድፍ አይገባም።

  ኢትዮጵያ የየትኛውም አገር #ፖስተኛ አይደለችም።   ፈላስፊቷ ኢትዮጵያ በአንድ የፖለቲካ ድርጅት #አትወከልም ፤ ልትወቀስም ይሁን ስሟ ሊጎድፍ አይገባም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰   የትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ገዢ ይሁን መሪ፤ የትኛውም ተፎካካሪ ይሁን ተቃዋሚ፤ የትኛውም #ተጠማኝ ይሁን ተደማሪ የፖለቲካ ድርጅት #ቀንጣውን ፤ ብቻውን ወይንም ያደራጀው ተቋም፤ የኢትዮጵያ ውክል አካል እኔ ብቻ ነኝ ሊል አይችልም። ቢያጠፋም ቢያለማም በፖለቲካ ድርጅቱ #ሥም እንጂ በአገረ ኢትዮጵያ ሊሆን አይገባም። ፈጽሞ። አገርን ማክበር እራስን ከማክበር፤ ከማስከበርም ሊነሳ ይገባዋል።   #ለምንድን አንድ ፖለቲካ ድርጅት ብቻውን ኢትዮጵያን ሊወክል የማይችለው? በስሱ እስቲ …… 1) አቅሙ ኢትዮጵያን ሊመጥን ስለማይችል። 2) ክህሎቱ ደረጃው በኢትዮጵያ ልክ ስለማይሆን። 3) የውስጡ ጥራት የኢትዮጵያን ተፈጥሮ ልክ ሊሆን ስለማይችል። 4) አንድም የፖለቲካ ድርጅት የሺ ዘመናት ታሪክ፤ ትውፊት፤ ባህል የሌለው ስለሆነ። 6) የፖለቲካ ድርጅት ፍልስፍና ኢትዮጵያዊ ሳይሆን #በትውስት ከሌሎች የተቀዳ፤ የተቀሰመ ስለሆነ ከኦርጋኒኳ ኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ሊግባባ፤ እኩል ሊቀመጥ ስለማይችል።   7) ዕድሜ ዘለቅ ያልሆነ፤ ዛሬ ተገንብቶ መፈጠሩ ሳይጠናቀቅ፤ በአንጃ፤ በሽኩቻ፤ በቅናት፤ አሳሩን የሚያይ ተቋቷም የድንቂትን ኢትዮጵያ ማንነት ውክል ሊሆን ስለማይችል።   ስምንተኛ) የአንድ አገር ህዝብ ሙሉው የፖለቲካ ድርጅት አባል ሆኖ ስለማያውቅ፤ ጥቂቶች የብዙኃኑን ተፈጥሯዊ ማንነት ጠቅላይ ሊሆኑ ስለማይገባ።   9) ሃሳቡ በዝምታ ውስጥ ያሉ የሚሊዮኖችን ድምጽ #አፋኝ እና ጠቅጣቂ ስለሆነ።...