ልጥፎች

የጨዋ ህዝብን መንፈስ #ማዋለል ለምን? የመልሰን "#እናጤነዋለን" ቀጠሮው ለመቼ? #መወሰን ያቃተው ነፍስ መኖር አልጀመረም።

  የጨዋ ህዝብን መንፈስ #ማዋለል ለምን? የመልሰን " #እናጤነዋለን " ቀጠሮው ለመቼ? #መወሰን ያቃተው ነፍስ መኖር አልጀመረም።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ። "   #ምዕራፍ ፲፱።   ይገርመኛል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁልጊዜ #በቀጠሮ ። "ቁርጥ ያጠግባል" ይላል ባለ ቅኔው ጎንደሬ። ይህ አሳረኛ ህዝብ እየተገበረ አሳሩን አዬ። ፍቅሩን በንጹህ ልቡ ቢሰጥም፤ መዝኖ ቢያስተዳድርም ስቃዩ ሊያባራ አልቻለም። መሻልን ለማሳዬት ሆኖ መገኜት ነው። ኢትዮጵያን ያህል አገር ለመምራት እራስ ሲታጭ ምን አለኝ ብሎ መነሳትን በእጅጉ ይጠይቃል። አገር ሱቅ በደረቴ አይደለችም።   #እፎካከራለሁ ስትል አቅምህን ነው እምታቀርብ እንጂ አንደበትህን አይደለም። ሙሉ አገርን ለመምራት የሰከነ፤ የሚዘልቅም ራዕይ፤ የተሰናዳ የተግባር ቅደም ተከተል፤ ብቁ መንፈስ እና ተመክሮ ይጠይቃል። ከምትፎካከረው፤ ከምታጣጥለው፤ ከምታቃልለው ይሁን፤ ከምታከብረው የፖለቲካ ድርጅት መሻልህን ህዝብ መስማት ሳይሆን ማዬት ይሻል።   የኢትዮጵያ ህዝብ ይሁን ኢትዮጵያ ፍቅሩንም፤ ክብሩንም፤ ዕውቅናውንም ለሁሉም በገፍ ሰጥቶ አይቷል። ተፈታትሿል። የኢትዮጵያ ህዝብ ስልጡን ህዝብ ነው። ቅኑ እና ቀናው ህዝባችን ምን እንዳለው፤ ምን ደግሞ እንደሌለው ያውቃል። በዝምታው ውስጥ እራስ እግሩ ብልህነት #ተደላድሎ የሰከነበት ህዝብ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ፍጹም አድማጭም ነው። ፍጹም ቻይ ህዝብም ነው።    የሚገርመኝ ግን በመንፈሱ ስለምን በተለያዩ በሚዋልሉ፤ በሚያረገርጉ፤ እርስ በርስ በሚጠላለፋ ሃሳቦች፤ መሻቶች እና ፍላጎቶች ይሁኑ አቋሞች ላይ #እንዲቀጣ እንደሚደረግ አላውቅም።    መወሰን ያቃተው ነፍስ መኖርን አልጀመረም። 15 ቀ...

"#ማንም ዜጋ መለመን የለበትም።" (ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ።) እንደ ምኞተወት ያድርግልን። አሜን።

  " #ማንም ዜጋ መለመን የለበትም።" (ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ።) እንደ ምኞተወት ያድርግልን። አሜን።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   #እፍታ ።   ትሁታዊ ሰላምታ አቀርባለሁኝ ለቤተ - ቅንነት እንዴት አደራችሁ? እንደምን አረፈዳችሁ? ለመጀመሪያ ጊዜ ይመስለኛል በአዲስ አበባ ከንቲባ ጽ/ቤት ዙሪያ የምጽፈው። የሚሞገቱበት ጠፍቶ ሳይሆን፤ በሴት የፖለቲካ ሊቃናት ላይ በአንፃራዊነት ለዘብተኛ ነኝ። የኢትዮጵያ ሴት የፖለቲካ ሊቃናት አዋን መድረክ አግኝተው፤ ወጥተው እኔ ታክዬ #ቲካቲካ የተገባ ነው ብዬ አላምንም።    የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሴቶችን ተጫኝ፤ የገበርዲን እና የከረባትም ስለሆነ ንጥረ ነገር የጎደለበት፤ የእናታዊ ጸጋ የተነነበት ስለሆነ ስኬቱም ሲትበሰበስ ነው የኖረው። በሰሞኑ የምግብ ማዕከል ምርቃት እና ንግግር መነሻነት ዛሬ የተሰማኝን ለመግለጽ አህዱ ብያለሁኝ።   #መቅድም ።   ከንቲባ አዳነች አበቤ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ "ድረሽልኝ" ባሏቸው የኃላፊነት ደረጃወች ሁሉ በመገኜት የልብ አድራሻቸው ብቻም ሳይሆኑ፤ የቅርብ፤ የሚያምኑት፤ የማይጠረጥሩት ሰብ ከኖራቸው፤ ከንቲባ አዳነች አበቤ ነው ሊሆኑ የሚችሉት።   በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃወች ፈቃዳቸውን በመፈጸም ቁጥር ፩ የጠሚሩ አጋር ይመስሉኛል - የዛሬዋ የመዲናችን የአዲስ አበባ ከንቲባ። ናቸው አላልኩም። ሊሆኑ ይችላሉ፤ ይመስሉኛል ነው ያልኩት። እምከታተለው በርቀት ስለሆነ።    #እንደ በር።   ዕድሜ ልኩን ታግሎ ኦነግ አንዲት አቅም ያላት አንስት ፖለቲካ ማብቀል አልቻለም። ኦፌኮ ጋር ፕሮፌሰር ዶር. መራራ ጉዲናን በአካል ሳገኝ በወጣቶች ፖለቲከኞች...

#በአናርኪዝም ውስጥ ተስፋም፤ ሰላምም ሊበቅል አይችልም። #ኢትዮጵያኒዝም እና #ህወሃት።

  • #በአናርኪዝም ውስጥ ተስፋም፤ ሰላምም ሊበቅል አይችልም።   "ህግ ተላላፊወችን ጠላሁኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ።   እንዴት ናችሁ ማህበረ ቅንነት? ደህና ናችሁ ወይ? እጅግ አድካሚው፤ እጅግ አሰልቺው፤ እጅግም ግትሩ የዞግ የፖለቲካ ድርጅት ህወሃትን ተሸክማ የኖረች ኢትዮጵያ መጥኔ ለእሷ፤ ለትግራይ እናቶችም መጥኔ።   #የማይደመጥ የለ።   ህወሃት እና #ጠማዳ ድርጊቱን እያዳመጥኩ፤ እያዬሁም ነበር ያደኩት። ስለሆነም አንዲት ደቂቃ ለህወሃት ብኰሩና አቅም አፍስሼ አላውቅም። ተሰቃይተን ነው ያደግነው። ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ዘወትር ሲያለቅስ ይኖራል እንዲሉ።   ሰሜን ጎንደር ሙሉ ዘመኑን በህወሃት በጋመ የበቀል ወላፈን ሲንገረገብ ኖሯል። ይህ በስማ በለው ሳይሆን ኖሬበት፤ ህይወቱን ያዬሁበት ነው። ለረጅም ዓመታት በምድር የሚታዩ በደሎችን ፈጽሞ፤ ያ ሳያረካው ሲቀር ቅዳሜ ገብያን በስልጣን ዘመኑ አነደደ።    የክልሉን ወሰን በማንአለብኝነት ጥሶም ሰብዕናን ተዳፈረ። የህወሃት መራራ ስንብቱ በኢትዮጵያ መንበረ መንግሥቱ የተፈጸመው #ሐምሌ ፭ ነበር። ያን መሰል አዋራጅ ጥቃት ተሸክሞ መዝለቅ አልቻልንም። መቻልም ልክ አለው። ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። ፍቅርም ሲያልቅ ትዕግሥት ይሰደዳል።    ህወሃት ቢያውቅበት ለትግራይ ቅርቡ ጎንደር ነው። ሁለመናው ውህድ ነው። ሁለመናው ፌክ ያልሆነ ተፈጥሯዊ ነው። ጋብቻው፤ የሃይማኖቱ ሂደት፤ የመማር ማስተማሩ፤ የሊቃውንታት የመኖር ጥበብ ልዩ ነበር። ጎንደሬ አብዛኛው ሥሙ የኋንስ ነው። ይህ ደግሞ ፈቅዶ እና ወዶ የሚፈጽመው የጎንደሬ ንጥር ዕውነቱ ነው።   ሌላው እቴጌ ትግራይ በከፋት ቁጥር የቅርብ የልብ ...