#ኢትዮጵያዊነት በራስ መተማመን ነው። (Confidence) (Vertraun) ነው። #ኢትዮጵያዊነት ተፈጥሮኛ ዲፕሎማትም ነው። እኛ ነው ልኩ መሆን ያቃተን። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፱። ማህበረ ትህትና እንዴት አደራችሁ? እንደምን አረፈዳችሁ? እንዴትስ ዋላችሁ? ሁለት ተወራራሽ ዕርዕስ በአንድ ጭብጥ። #ለአፍታ ። እስቲ እኛን በእኛነት፤ እኔ በእኔነት፤ ሁላችንንም በሁለመናነት አመጣጥኖ፤ ቀምሮ፤ መጥኖ ያበጀንን ኢትዮጵያዊነትን መርምሩት። ቅጥልጥል፤ ቀንድ እና ልጥፍጥፍ የሚያሰኛቸውን ወገኖቼን አይመለከትም ጥያቄው። እንደ ሰው አስበን፤ ሰው ሆነን እንዘልቅ ዘንድ ውስጣችን እራስ እጉሩ ያሰበለ እንዲሆን ያደረገውን ጀግናውን ማንነት ከህሊናችን ሁነን እንሰበው። #አይደፈሬው ደፋሪውን ያስተምራል። ሁልጊዜ፤ ለምንግዜም ኢትዮጵያዊነት ኦክስጅናችሁ ሲሆን፤ የትኛውንም የፈተና ጋራ የመበገር አቅም ታገኛላችሁ። ኢትዮጵያዊነት የተደራጄ ተፈጥሯዊ የአቅም ልዩ መክሊት ነው። በኢትዮጵያዊነት ውስጥ የተመጣጠነ፤ ህብራዊ የሆነ ቀለማም መሳጭ ጸጋ አለ። ረቂቅ የሆነ በራስ የመተማመን አቅም አለ። ይህ አቅም ዩንቨርስቲ ገብታችሁ ብትማሩት የማታገኙት እንደ ላሊበላ አለት ጸንቶ የሚያጸና፤ ረግቶ የሚያረጋ #የመሰጠት ዲካ ነው። #እርግጥ ነው ኢትዮጵያዊነት ተፈሪ ማንነት ነው። በልኩ መሆን ሲሳን ይፈሩታል። ይገባልም። እርግጥ ነው ኢትዮጵያዊነት የሚቀናበት ማንነት ነው። ኢትዮጵያዊነት በጥበብ ውስጥ የሚዘልቅ የዊዝደም ጎዳና ነው። በኢትዮጵያዊነት ውስጥ መንፈስ ሲቀማጠል ይደለዋል። ለምን? እርግጠኛ የሚያደርግ ልዩ ኢነርጂ ስላለው። ኢትዮጵያዊነት ...