#መፍቻ ።
#መፍቻ ። “አድርገህልኛል እና አመሰግንለሁኝ።“ #ምዕራፍ ፲፰። #ጠብታ ። ዛሬን ለእኔ ሰጠሁት። ሚሞሪን እያሞቀ ከሚገኘው ለህትም ከበቃው ሦስተኛው የዓዋቂወች የግጥም መድበሌ ላይ የተወሰደ ነበረ። በደራሽ ጉዳዮች፤ በሰብአዊነት ጉዳዮች፤ በኢትዮጵያ ዕናቶች አመክንዮ ጉዳዮች ላይ አበክሬ ስለምሰራ እኔን ስቶር ውስጥ ወይንም ሚሞሪው ውስጥ አስቀምጬ በፌስቡክ ለ፮ ዓመታት፤ በሚዲያ ከ፳ ዓመታት በላይ፤ በፖለቲካ ከጋሜዬ ጀምሮ ተኖረበት። ለእኔ ቀን ሰጥቼው አላውቅም። ይህ ሚዲያ የእኔን እኔም ላስተዋውቀው ፈለግሁኝ። ስለሆነም ዛሬን አጠገብኩት። ጹሁፎቹም ሆኑ ግጥሞቹ ከ፲፭ ዓመታት በላይ የቆዩ ናቸው። ሳድስ ላይ ስለምገድፍ እሱን እና አንዳንድ ጉዳዮችን ለማጠናከር ሞክሬያለሁኝ። እርዕሶች ጭብጡ አልተቀየረም። ማስተካከያው ፩% እንኳን አይሆንም። መክሊት መጸሐፌ ለውዷ እናቴ፤ ለበሞቴ ልዕልቴ፤ ለእሽታ ንግሥቴ ለእብዬ ሆዴ የተሰጠ ነው። ስለሆነም በባህል፤ በትውልድ፤ በትውፊት በማህበራዊ ኑሮ፤ በዕውነት ላይ ያተኮረ ነው። ፖለቲካ የለበትም። #መፍቻ የመክሊት መጸሐፌ ማሳረጊያ ነው። ዛሬ ስክሪብቱ ላይ ሳነበው ገረመኝ። ከፊደል እርማት በስተቀር ቅንጣት አልተጨመረበትም። እንሆ መፍቻን ……… ግን የእኔ የቅንነት ውቦች ብሩሆቼም እንዴት አላችሁልኝ። ሁልጊዜም፤ ምንጊዜም ቅንነታችሁ #ቁሞ ያስተምረኛል። ዘለግ ስላለው ትዕግስታችሁ በትሁት አክብሮት አመሰግናችኋለሁኝ። 1) የነገ የፍላጎታችን #መፍቻ ምንድ ነው? 2) ወይንስ #ማን ነው? 3) ነገን ስናስብ ዛሬ ለነገ ምን እንዲያቆዬው? --- ምን #እንዲያሰናዳለት አዘጋጅተነዋል? 3) ነገ ለራሱ ብቻ...