ኢትዮጵያ የየትኛውም አገር #ፖስተኛ አይደለችም። ፈላስፊቷ ኢትዮጵያ በአንድ የፖለቲካ ድርጅት #አትወከልም፤ ልትወቀስም ይሁን ስሟ ሊጎድፍ አይገባም።
ኢትዮጵያ የየትኛውም አገር #ፖስተኛ አይደለችም። ፈላስፊቷ ኢትዮጵያ በአንድ የፖለቲካ ድርጅት #አትወከልም ፤ ልትወቀስም ይሁን ስሟ ሊጎድፍ አይገባም። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፰ የትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ገዢ ይሁን መሪ፤ የትኛውም ተፎካካሪ ይሁን ተቃዋሚ፤ የትኛውም #ተጠማኝ ይሁን ተደማሪ የፖለቲካ ድርጅት #ቀንጣውን ፤ ብቻውን ወይንም ያደራጀው ተቋም፤ የኢትዮጵያ ውክል አካል እኔ ብቻ ነኝ ሊል አይችልም። ቢያጠፋም ቢያለማም በፖለቲካ ድርጅቱ #ሥም እንጂ በአገረ ኢትዮጵያ ሊሆን አይገባም። ፈጽሞ። አገርን ማክበር እራስን ከማክበር፤ ከማስከበርም ሊነሳ ይገባዋል። #ለምንድን አንድ ፖለቲካ ድርጅት ብቻውን ኢትዮጵያን ሊወክል የማይችለው? በስሱ እስቲ …… 1) አቅሙ ኢትዮጵያን ሊመጥን ስለማይችል። 2) ክህሎቱ ደረጃው በኢትዮጵያ ልክ ስለማይሆን። 3) የውስጡ ጥራት የኢትዮጵያን ተፈጥሮ ልክ ሊሆን ስለማይችል። 4) አንድም የፖለቲካ ድርጅት የሺ ዘመናት ታሪክ፤ ትውፊት፤ ባህል የሌለው ስለሆነ። 6) የፖለቲካ ድርጅት ፍልስፍና ኢትዮጵያዊ ሳይሆን #በትውስት ከሌሎች የተቀዳ፤ የተቀሰመ ስለሆነ ከኦርጋኒኳ ኢትዮጵያ ጋር ፈጽሞ ሊግባባ፤ እኩል ሊቀመጥ ስለማይችል። 7) ዕድሜ ዘለቅ ያልሆነ፤ ዛሬ ተገንብቶ መፈጠሩ ሳይጠናቀቅ፤ በአንጃ፤ በሽኩቻ፤ በቅናት፤ አሳሩን የሚያይ ተቋቷም የድንቂትን ኢትዮጵያ ማንነት ውክል ሊሆን ስለማይችል። ስምንተኛ) የአንድ አገር ህዝብ ሙሉው የፖለቲካ ድርጅት አባል ሆኖ ስለማያውቅ፤ ጥቂቶች የብዙኃኑን ተፈጥሯዊ ማንነት ጠቅላይ ሊሆኑ ስለማይገባ። 9) ሃሳቡ በዝምታ ውስጥ ያሉ የሚሊዮኖችን ድምጽ #አፋኝ እና ጠቅጣቂ ስለሆነ።...