የጨዋ ህዝብን መንፈስ #ማዋለል ለምን? የመልሰን "#እናጤነዋለን" ቀጠሮው ለመቼ? #መወሰን ያቃተው ነፍስ መኖር አልጀመረም።
የጨዋ ህዝብን መንፈስ #ማዋለል ለምን? የመልሰን " #እናጤነዋለን " ቀጠሮው ለመቼ? #መወሰን ያቃተው ነፍስ መኖር አልጀመረም። "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ። " #ምዕራፍ ፲፱። ይገርመኛል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁልጊዜ #በቀጠሮ ። "ቁርጥ ያጠግባል" ይላል ባለ ቅኔው ጎንደሬ። ይህ አሳረኛ ህዝብ እየተገበረ አሳሩን አዬ። ፍቅሩን በንጹህ ልቡ ቢሰጥም፤ መዝኖ ቢያስተዳድርም ስቃዩ ሊያባራ አልቻለም። መሻልን ለማሳዬት ሆኖ መገኜት ነው። ኢትዮጵያን ያህል አገር ለመምራት እራስ ሲታጭ ምን አለኝ ብሎ መነሳትን በእጅጉ ይጠይቃል። አገር ሱቅ በደረቴ አይደለችም። #እፎካከራለሁ ስትል አቅምህን ነው እምታቀርብ እንጂ አንደበትህን አይደለም። ሙሉ አገርን ለመምራት የሰከነ፤ የሚዘልቅም ራዕይ፤ የተሰናዳ የተግባር ቅደም ተከተል፤ ብቁ መንፈስ እና ተመክሮ ይጠይቃል። ከምትፎካከረው፤ ከምታጣጥለው፤ ከምታቃልለው ይሁን፤ ከምታከብረው የፖለቲካ ድርጅት መሻልህን ህዝብ መስማት ሳይሆን ማዬት ይሻል። የኢትዮጵያ ህዝብ ይሁን ኢትዮጵያ ፍቅሩንም፤ ክብሩንም፤ ዕውቅናውንም ለሁሉም በገፍ ሰጥቶ አይቷል። ተፈታትሿል። የኢትዮጵያ ህዝብ ስልጡን ህዝብ ነው። ቅኑ እና ቀናው ህዝባችን ምን እንዳለው፤ ምን ደግሞ እንደሌለው ያውቃል። በዝምታው ውስጥ እራስ እግሩ ብልህነት #ተደላድሎ የሰከነበት ህዝብ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ፍጹም አድማጭም ነው። ፍጹም ቻይ ህዝብም ነው። የሚገርመኝ ግን በመንፈሱ ስለምን በተለያዩ በሚዋልሉ፤ በሚያረገርጉ፤ እርስ በርስ በሚጠላለፋ ሃሳቦች፤ መሻቶች እና ፍላጎቶች ይሁኑ አቋሞች ላይ #እንዲቀጣ እንደሚደረግ አላውቅም። መወሰን ያቃተው ነፍስ መኖርን አልጀመረም። 15 ቀ...