ልጥፎች

#በአናርኪዝም ውስጥ ተስፋም፤ ሰላምም ሊበቅል አይችልም። #ኢትዮጵያኒዝም እና #ህወሃት።

  • #በአናርኪዝም ውስጥ ተስፋም፤ ሰላምም ሊበቅል አይችልም።   "ህግ ተላላፊወችን ጠላሁኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ።   እንዴት ናችሁ ማህበረ ቅንነት? ደህና ናችሁ ወይ? እጅግ አድካሚው፤ እጅግ አሰልቺው፤ እጅግም ግትሩ የዞግ የፖለቲካ ድርጅት ህወሃትን ተሸክማ የኖረች ኢትዮጵያ መጥኔ ለእሷ፤ ለትግራይ እናቶችም መጥኔ።   #የማይደመጥ የለ።   ህወሃት እና #ጠማዳ ድርጊቱን እያዳመጥኩ፤ እያዬሁም ነበር ያደኩት። ስለሆነም አንዲት ደቂቃ ለህወሃት ብኰሩና አቅም አፍስሼ አላውቅም። ተሰቃይተን ነው ያደግነው። ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ዘወትር ሲያለቅስ ይኖራል እንዲሉ።   ሰሜን ጎንደር ሙሉ ዘመኑን በህወሃት በጋመ የበቀል ወላፈን ሲንገረገብ ኖሯል። ይህ በስማ በለው ሳይሆን ኖሬበት፤ ህይወቱን ያዬሁበት ነው። ለረጅም ዓመታት በምድር የሚታዩ በደሎችን ፈጽሞ፤ ያ ሳያረካው ሲቀር ቅዳሜ ገብያን በስልጣን ዘመኑ አነደደ።    የክልሉን ወሰን በማንአለብኝነት ጥሶም ሰብዕናን ተዳፈረ። የህወሃት መራራ ስንብቱ በኢትዮጵያ መንበረ መንግሥቱ የተፈጸመው #ሐምሌ ፭ ነበር። ያን መሰል አዋራጅ ጥቃት ተሸክሞ መዝለቅ አልቻልንም። መቻልም ልክ አለው። ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። ፍቅርም ሲያልቅ ትዕግሥት ይሰደዳል።    ህወሃት ቢያውቅበት ለትግራይ ቅርቡ ጎንደር ነው። ሁለመናው ውህድ ነው። ሁለመናው ፌክ ያልሆነ ተፈጥሯዊ ነው። ጋብቻው፤ የሃይማኖቱ ሂደት፤ የመማር ማስተማሩ፤ የሊቃውንታት የመኖር ጥበብ ልዩ ነበር። ጎንደሬ አብዛኛው ሥሙ የኋንስ ነው። ይህ ደግሞ ፈቅዶ እና ወዶ የሚፈጽመው የጎንደሬ ንጥር ዕውነቱ ነው።   ሌላው እቴጌ ትግራይ በከፋት ቁጥር የቅርብ የልብ ...

"ኤምቪ ሆንድየስ" (MV Hondius)

  " ኤምቪ ሆንድየስ " (MV Hondius) የጤና መረጃ፡ የሃንታ ቫይረስ ስርጭት እና የዓለም ጤና ድርጅት ስጋት በአሁኑ ሰዓት " ኤምቪ ሆንድየስ " (MV Hondius) በተሰኘች የቱሪስት መርከብ ላይ የተከሰተው የሃንታ ቫይረስ ስርጭት ዓለም አቀፍ ትኩረትን ስቧል። ቫይረሱ በፈረንሳይ፣ ስፔን እና አሜሪካ በሚገኙ ተጓዦች ላይ እየታየ ሲሆን፣ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተለ ይገኛል። ዋናው ስርጭት የተከሰተው በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ በነበረችው MV Hondius በተባለች የደች (Dutch) መርከብ ላይ ነው። ከመግለጫው ጀምሮ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ እና አሜሪካ ውስጥ በሚገኙ ሆስፒታሎች ክትትል እየተደረገላቸው ነው። እስከ አሁን ድረስ በመርከቧ ላይ በነበሩ 3 ሰዎች ላይ የሞት አደጋ ደርሷል። እስካሁን በኢትዮጵያም ሆነ በጎረቤት አገራት የተመዘገበ ስርጭት የለም። ነገር ግን ቫይረሱ ከአይጥ ወደ ሰው የሚተላለፍ በመሆኑ ጥንቃቄ አስፈላጊ ነው። ቫይረሱ እንዴት ይተላለፋል ? ይህ ቫይረስ በዋነኝነት የሚተላለፈው በአይጥ ዝርያዎች ሲሆን፦ 1. በአይጥ ንክሻ ወይም አይጦች በነኩት ምግብ። 2. የአይጥ ሽንት ወይም ቆሻሻ ያለበትን አቧራ በመተንፈስ። 3. አሁን የተከሰተው " የአንዴስ " (Andes virus) ዝርያ በጣም አልፎ አልፎ ከሰው ወደ ሰው ሊተላለፍ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ። ...