ልጥፎች

ማንዴላይዝም የጽናት የእርቅ እና የምህረት እሽታ ካሪክለም ነው።

  ማንዴላይዝም የጽናት የእርቅ እና የምህረት እሽታ ካሪክለም ነው።    • "ባለቤቱ ያቀለለውን አሞሌ ባለዕዳው አይቀበለውም" ሆነ እንጂ።   #አገርኛ የመንፈስ ቴራፒ ነው። አገር የህይወት መንገድ ናት።   ከቶስ #ሰው መሆናችን ያላግባባን ምን ያግባባን?   " ፍቅራችሁ ያለ ግብዝነት ይሁን። ክፋውን ነገር ተጸየፋት፤ ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ፤ በወንድማማች መዋደድ፤ እርስ በእርሳችሁ #ተዋደዱ ፤ እርስ በእርሳችሁ #ተከባበሩ ። ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤ በተስፋ ደስ ይበላችሁ፤ በመከራ ታገሱ፤ በጸሎት ጽኑ፤ ቅዱሳንን በሚያስፈልጋቸው እርዱ፤ #እንግዶችን ለመቀበል #ትጉ ። (ሮሜ ምዕራፍ ፲፪ ቁጥር ከ፱ - ፲፫።)   ደቡብ አፍሪካ .... Religion in South Africa ... Religion in South Africa Wikipedia https://en.wikipedia.org › wiki › Relig... · "Religion in South Africa · Christianity (85.3%) · Traditional faiths (7.80%) · No religion (3.10%) · Islam (1.60%) · Hinduism (1.10%) · Others (1.10%)."   #ምዕራፍ ፲፱።   እኔ ከወንጌል ውስጥ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክታት ሁሉ ይመስጡኛል። ሮሜ ግን ይበልጥብኛል። ለመዝሙር የሚሆን ግጥምም ነበረኝ። የሆነ ሆኖ ዘመናችን ይቃኛል። ዛሬ ያለንበት ዘመን ከፊተኛው የፈተና ጊዜ ጋር እንደምን እንደሚገናኝ ያሳያል። የጎደለብንን፤ ያጎደልንበትን ሳስበው የሁሉም አሉታዊ መነሻ እና መድረሻ #የክፋ ሃሳብ ጽንት፤ ብቅለት፤ ስብለት ስለመሆኑ ያብራራልናል።...

ጭነት ያዬለበት #በአለን #ቁምነገራ ላይ ነው። #ኖረን ነው ፍዳው የጠና።

  ጭነት ያዬለበት #በአለን #ቁምነገራ ላይ ነው። #ኖረን ነው ፍዳው የጠና።   "እግዚአብሄር ለቁጣ የዘገዬ፤ ፍቅሩ የበዛ፤ ኃጢአትንና ዐመፃን ይቅር የሚል ነው።"   ዘኅልቁ ፲፬፤፲፰።   #ምዕራፍ ፲፱።    ዝም ብላችሁ እሰቡት ያለውን የማንነት ቀውሳም ሾተላይ። ከእራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ የማንነት ቀውስን ብትፈትሹት #እኛ እራሱ ለምን ተባልን ነው። እኛ ኢትዮጵውያን ይህም አለን፤ ያም ነበረን ወንጀል ነው የማንነት ቀውስ ፌስታ ላይ ላለ ሰብዕና። የክፋ ሃሳብ ሰራዊት ነው የማንነት ቀውስ ጠንሳሽ። አቤቱ ቅናት፤ በራስ የመተማመን አቅም ሙሽሽነትም።   አንድ አይሉ #ሁለት የፌደል ገበታ ከነ ሙሉ ሥርዓቱ ስዋሰው ስለምን ኖረን? ኧረ አቡጊዳን ስናክለው ሦስት ይሆናል። ጥርት ያለ በአርበኝነት የጸደቀ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ስለምን ኖረን?   የቤተ - እግዚአቤሄር ቋንቋ ሊቁ #ግዕዝ ስለ ምን ተፈጠረ? የዕውቀት መግቢያ በር #የየኔታ ማዕደ ገበታ ስለምን ኖረን? የአማርኛ ቋንቋ ቅኔው፤ ለዛው፤ ስልተ ምርቱ፤ #ዝልቅ የትርጓሜ አቅሙ ለምን ኖረው? በቅቶ ስለተገኜ በዓለም ዓቀፍ የፊደላት ቀን ተመራጭ ነው። በዩንቨርስቲ በሌሎች አገሮች ይሰጣል። የሥራ ቋንቋም በአደጉ አገሮች መሆን ችሏል። ብሄራዊ #የድል መታሰቢያ ቀናት ለምን ኖረን? ስለምን #ነፃ ህዝብ እና አገር ተባልን? ህመም በሽታ እኮ ነው።   ስልጡን የአመጋገብ ሥርዓታችን ስለምን አለን? በዶሮ ወጥ ላይ ሁሉ ተዘምቷል እኮ። ህብራዊ የሸማ የአለባበሥ ሥርዓታችን በጥበብ፤ በጥልፍ፤ በብር እና በወርቅ በቀደምቶቹ ስለምን አለን? ባህላዊ የተለያዩ መጠጣችን ለአዋቂም ለልጆችም ስለምን የእኛ ሆኑ? ቅኝ አለመገዛት ...

አድራሻ አድራሽ።

  • አድራሻ አድራሽ።   «ለቁጣ የዘገየ ፍቅሩም የበዛ ነው።"    እግዚአብሄር ለቊጣ የዘገየ፤ ፍቅሩሩ የበዛ፤ ኃጢያትን እና ዐመፃን ይቅር የሚል ነው።    (ዘኁልቊ ፲፬፤፰።)   1) አድራሻ #ጠብቆ ሲነበብ። የሃሳብ ዓላማ እና ግብ መዳረሻ፤ የቦታ መለያም። 2) አድራሽ #ላልቶ ሲነበበ አቀባይ፤ ፖስተኛ፤ መልዕክተኛ።    «ፕሬዝዳንት ትራምፕ የሕዳሴው ግድብ ጉዳይን "ቅድሚያ ሰጥተው" እንደሚመለከቱት ተናገሩ» ዘገባው የBBC ነው። ኢትዮጵያ አለመጋበዟ ይጎረብጣል። ለምን ስለምንን ያነሳሳል።   #ምዕራፍ ፲፱።   ኢትዮጵያ የመንፈስም፤ የፓን አፍሪካኒዝምም አዳራሽ አድራሽም ናት። በG7 ጉባኤ ላይ ያውም #ፈረንሳይ ላይ በተካሄደ ዕድሉን አለማግኜቷ ከተሟጋች አንፃር ሳይሆን እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁኔታው ሊያሳዝነን ይገባል።    የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚር አብይ የቀረበ ግንኙነት እንዳላቸው አያለሁና። የኢትዮጵያ የመንፈስ ልቅእና በልዕልና ያላት፤ ቀደምትነት፤ የአፍሪካ አንድነት እና በተመድ ምስረታ ላይ ያላት የሙሉዑነት ተሳትፎ፤ በነፃነት ዙሪያም ያለት ብቃት እና ክህሎት ዘመን #ሊጠቀጥቀው የማይገባ ዕንቁ ጉዳይ ነው።   ኢትዮጵያ የቀደመ ሥልጣኔዋ "ምን አላት እና ለካሪክለም የሚያበቃት" የሚል #የዛለ መንፈስ እንዳለ ባውቅም፤ ኢትዮጵያዊነት ግን ሊማሩት የሚገባ የዕውቀት ዘርፍ መሆን የሚችል የልቀት ማዕከል ነው። ከዚህ አንፃር የግብጽ እና የኬኒያ ውክልና የአፍሪካን አህጉራዊ አቅም የሚፈትን ገጠመኝ ነው ብዬ አስባለሁኝ። ኬኒያም ይሁን ግብጽ መወከላቸው እንዳለም ሆኖ፤ ኢትዮጵያን አግልሎ መነሳት ግን ትክክል ነው ብዬ እኔ በግሌ ...