ልጥፎች

#ስሜናዊነቴ ህወሃትን ቤቴ ለማለት ከሆነ በአፍንጫዬ ይውጣ።

  #ስሜናዊነቴ ህወሃትን ቤቴ ለማለት ከሆነ በአፍንጫዬ ይውጣ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።   #እፍታ ለአፍታ። አወን እርግጥ ነው በአባቴም በእናቴም ስሜናዊ ነኝ። ስሜናዊነቴ አንዱ ማንነቴ ነው። ግን ያን ጊዜ የማይስተምረውን የጭካኔ አስኳል ጋር ለሠርግ - መልስ፤ ለቅልቅል እና ለግጥግጥ ከሆነ ስሜናዊነቴ በአፍንጫዬ ይውጣ።   የሚገርመኝ የጽጥምዶ ባላንበራሶች ዛሬ ደርሰው የወልቃይት፤ የጠገዴ፤ የአዲረመጥ፤ የአዳርቃይ፤ የጠለምት፤ የራያ ተቆርቋሪ ሆነው መምጣታቸው ነው። እንደ ሽንብራ ቂጣ መገላበጡ የእውነትን ልክ #ሊከልሰው ፈጽሞ አይችልም።   ዛሬም ህወሃት ከዛ #ከታቆረ ሃሳቡ ፈቀቅ ሊል ያልቻለ፤ ድውይ ድርጅት መሆኑ ዓለምም እያዬው ነው። ኡኡታው፤ ለማሳጣት ከፍ ዝቅ ማለቱ፤ መሸነፋን ለመቀበል አቅል አጥቶ መክለፍለፋ ዘመን ሊያስተምረው አልቻለም። እንጂማ ቢገባው የእሱ አንቱነት ከግንቦት መግቢያ 2023 ጀምሮ ማክተሙን አላወቀም።    #ለማንኛውም ሰብ ይሁን ተቋም እኔ የምለው ……   1) መውደቅን መቀበል ብልህነት ነው። መሸነፍን መቀበል ብልህነት ነው። ምክንያቱም በመውደቅ ውስጥ መነሳት፤ በመሸነፍ #ከርስ ውስጥ ማሸነፍም ስለሚቻል።   መሸነፍ ብቻውን አይቆምም። የሙሉ ዕድሜ ተመክሮ መግቦ ነው። በመሸነፍ ውስጥ እራስን የማየት አጋጣሚ ይገኛል። መሸነፍን ለሚቀበል። ዕውቅናም ለሚሰጥ። ይህ ሲሆን በመሸነፍ ውስጥ ዳግም ጥፋትን ላለማጨት ህሊናን ያሰናዳል።   2) መውደቅም ቢሆን ከብዙ ኪሳራ ጋር ቢሆንም፤ እራስን ከወደቁበት ረግረግ ለማውጣት የጥሞና፤ የተደሞ ጊዜ ቢሰጠው በአዲስ አቅም፤ በእሸት ጉልበት አገግሞ ቀና ማለት ይቻላል። ግን ...

ቅጽበታዊው #ስምረት ፓርቲ ገና ጮርቃ እኮ ነው። በደል ይረሳል ወይንስ #ይለመዳል? አዲስ ልብስ #የጭካኔን ገመና አይሸፍንም።

  ቅጽበታዊው #ስምረት ፓርቲ ገና ጮርቃ እኮ ነው። በደል ይረሳል ወይንስ #ይለመዳል ? አዲስ ልብስ #የጭካኔን ገመና አይሸፍንም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።   #ጠብታ ።   እኔ ሥርጉተ ሥላሴ የአዳዲስ የፖለቲካ ድርጅት ምሥረታ የሚያስፈነድቀኝ፤ የአዳዲስ የፖለቲካ ድርጅቶች ምርጫ በመጣ ቁጥር በአዲስ ማራኪ ሥያሜ መዋህድ ይሁን መቀናጀት ፋሲካዬ ነው ብዬ አቅም የማባክን ሰው አይደለሁም። ይህን አፍንጫህን ላስ አቶ ሂደት ላይ ጽፌዋለሁኝ ሌላ ጊዜም ስለ አጤ ሂደት እንዲሁ ጽፌለሁኝ። በከንቱ እምናፈሰው አቅም ቁስ ጉዳይ አይደለም። እሱ ቀላል ነው። መኖሩን በእስር፤ በመታገት፤ በመሰወር፤ ነፍሱን በማጣት ለሚቀማው ትውልድ ጠቃሚ መንገድ አለመሆኑን ቀድሜ ተረድቸዋለሁኝ። ትርፈ ቢስ አልቦሽነቱን ትርጉሙም፤ ሚስጢሩም ገብቶኛል። እንኳን መላ አካለት በጭካኔ፤ በመታበይ በዝና ሱስ፤ በሚዲያ ንግሥና መውደቅ መነሳት ላይ አቅም ላባክን።   #ቆባ ላይ ያለ ድርጅት ልኩን በልኩ ቢያደርገው።   የአባ ሻንቆ ፍታውራሪ አርበኛ መለሰን በዓት ትናት የተፈጠረ ሩብ ዓመት ያላስቆጠረ የፖለቲካ ድርጅት ለዚህ ግዙፍ ሚስጢርን አቅፎ ለተቆረቆረ በዓት ባለቤት ነኝ ብሎ ሲነሳ ከትከት ብዬ #ስቄያለሁኝ ። ያን ሁሉ የማይካድራ ደም በከንቱ ያፈሰሰ፤ በድፍን ወሎ፤ በወገራ ጭና፥ በንፋስ መውጫ የፈጸመው ሞልቶ የተረፈው ግፍ ሱፍ አስለብሶ በሽልማት፤ በሽርሽሽር፤ በሰርግ መልስ እና ቅልቅል ድለቃ ትወና ዓይን አይችለው የለ ሚዲያ ግልምት እስኪለን ድረስ አየን። ማፈሪያነት፤ ጸረ ሰውነት ባለ ክብር ሆኖ ሲጎማሸር የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለሰብአዊነት፤ ለተፈጥሯዊነት ያለው የህሊና አቅምን ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ...

#የ2018ዓ.ም የምርጫ መቅድመ ሙግት ካዳመጥኩት - ትዝብቴ።

ምስል
  #የ2018ዓ .ም የምርጫ መቅድመ ሙግት ካዳመጥኩት - ትዝብቴ።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።"   #ምዕራፍ ፲፰።    «የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጀመሪያው የክርክር መድረክ»  https://www.youtube.com/watch?v=DG6SHFL76_0   ሊንኩን በጥዋቱ ሼር አድርጌዋለሁኝ። በተጨማሪም መቅድመ ውይይት ስለሆነ ልፅፍበት ፈለግሁኝ። በቅድሚያ የሴቶች ተሳትፎ ለፆታ ተዋፆ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሴቶችን የፖለቲካ ግንዛቤ አቅም ጋር አቻ ሆኖ ሲገኝ ተስፋ ሰጪ ነው። እኔ ለሴቶች ተሳትፎ ልዩ ስስት አለኝ። ሴት ስለሆን ብቻ መድረክ ይሰጠን አይደለም። እእ። አቅም ያላቸው ሴቶች ተመጣጣኝ የፖለቲካ ውክልና ሊሰጣቸው ይገባል ነው የእኔ የትግል ማዕከል። በዘርፋ የፖለቲካ ሊቃናት ሴቶች ከእነሱ #ድፍረት ማነስ ካልሆነ በዘመነ አብይዝም ያለው ሁነት የሚያበረታታ ነው። ብዙ የፖለቲካ ሴት ሊቃናት ወደፊት መጥተዋል። ይህ የውሳኔ አቅም በአወንታዊነት የማየው ነው።    ሌሎችም ተፎካካሪወች ይህን አትራፊ እና ቀና መንገድ በመከተላቸው አመሰግናቸዋለሁኝ።    1) #የመወዳደሪያ ዓርማ።   1.1) የስንዴ ነዶ ባለፈው በስፋት ስለገለጽኩት አልመለስበትም። ነዶ (የጨርቅ ነዶ፤ የእሳር እህል ነዶ፤ የመቃጠል ዓዋጅ፤ የብስጭት መግለጫ) ቃሉ ለማስታወስ ያህል አሻሚ ትርጉም ያለው ስለመሆኑ አጠይቄ ብቻ አልፈዋለሁኝ። (የብልጽግና የምርጫ መወዳደሪያ መለያ ነው የስንዴ ነዶ።)   1.2) ሚዛን። ከገጠር እስከ ከተማ የሁሉንም ትርታ የሚገዛ ነው። (የኢዜማ የምርጫ መወዳደሪያ መለያ ነው ሚዛን።) 1.3) የእጅ ባትሪ። የግል የሆነ፤ ማንም የማያዘ...