ልጥፎች

ከዚህ በኋላስ? "በዋግ ኽምራ ዞን ታጣቂዎች ሁለት ወረዳዎችን በመቆጣጠራቸው በርካታ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው ተነገረ" BBC.".

  "በዋግ ኽምራ ዞን ታጣቂዎች ሁለት ወረዳዎችን በመቆጣጠራቸው በርካታ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው ተነገረ" BBC.   https://www.bbc.com/amharic/articles/cjeg35z91ywo 10 ሰኔ 2026 የንባብ ጊዜ: 5 ደቂቃ   "በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን 'የአገው ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ' (አዴን) ታጣቂዎች አበርገሌ እና ፃግብጂ ወረዳዎችን "ሙሉ ለሙሉ" መቆጣጠራቸውን እና ማኅበረሰቡ በስጋት ሸሽቶ መፈናቀሉን የአካባቢው አስተዳደር እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።   ከሁለት ዓመት በፊት ከመንግሥት ጋር የሰላም ስምምነት ፈርመው የነበሩት የአገው ታጣቂዎች ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምረው ሁለት ወረዳዎችን እንደተቆጣጠሩ አምስት የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዞኑ ፀጥታ መምሪያ ተናግረዋል።   የአዴን ኃላፊዎች ወረዳዎቹን እንደተቆጣጠሩ ለቢበሲ አረጋግጠው፤ ነዋሪዎች ግን አልተፈናቀሉም በማለት አስተባብለዋል። በአበርገሌ ወረዳ ሚያዚያ 12/2018 ዓ.ም. በአካባቢው ሚሊሻዎች እና በታጣቂዎች መካከል "በከባድ መሣሪያ" የታገዘ ግጭት ከተቀሰቀሰ በኋላ የአዴን ኃይሎች በከፊል ተቆጣጥረውት የነበረውን ወረዳ ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠራቸው ተነግሯል።   ቀኑን ሙሉ ውሏል በተባለው ውጊያ የአዴን ኃይሎች ከ"ህውሓት ታጣቂዎች" ጋር "ተቀናጅተው" እንደተሳተፉ ነዋሪዎች እና የዞኑ አስተዳደር ለቢቢሲ አመልክተዋል።   የአዴን የሚዲያ እና ኮምዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ ካሴ ከህውሓት ኃይሎች ጋር ተጣምረው መዋጋታቸውን አስተባብለው፤ "አመራሮቻችንን አፍነው ለመውሰድ ሲሞክሩ" ግጭቱ ተቀስቅሷል በማለት "ተገፍተን ነው [ወደ ግጭት] የገባነው" ...

"የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ BBC."

ምስል
  "የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ BBC." https://www.bbc.com/amharic/articles/cn94gp15zx7o   ከ 5 ሰአት በፊት የንባብ ጊዜ: 3 ደቂቃ   "በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።   ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።   በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።   ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።   ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።   ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።   ''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።   ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው ...

«ስዊትዘርላንድ የሕዝብ ቁጥሯ ከ10 ሚሊዮን እንዳይበልጥ በቀረበው ዕቅድ ላይ ድምጽ ልትሰጥ ነው» BBC.

  «ስዊትዘርላንድ የሕዝብ ቁጥሯ ከ 10 ሚሊዮን እንዳይበልጥ በቀረበው ዕቅድ ላይ ድምጽ ልትሰጥ ነው» BBC. https://www.bbc.com/amharic/articles/c6216ggwxryo   ከ 5 ሰአት በፊት የንባብ ጊዜ : 3 ደቂቃ "አንድ አገር የሕዝብ ቁጥሩ እንዳያድግ ቁጥሮችን ማስቀመጥ እና መወሰን ይቻላል ?" "ይህንን ለመመለስ ስዊትዘርላንድ የአገሪቱን ሕዝብ ቁጥር ከ 10 ሚሊዮን እንዳይበለጥ የቀረበው ዕቅድ ላይ እሁድ ድምጽ ትሰጣለች። ዕቅዱን ቀኝ ዘመሙ የስዊስ ሕዝብ ፓርቲ ( ኤስቪፒ ) ደግፎታል። ፓርቲው ዕቅዱ በመኖሪያ ቤት፣ በሕዝብ አገልግሎቶች እንዲሁም በአካባቢ ላይ ያለውን ጫና ይቀንሳል " የዘላቂነት " ጥያቄ ነው ሲል ደግፎታል። ወደ ስዊትዘርላንድ የሚመጡ ስደተኞችን ቁጥር የመቀነስ ዓላማ ያለው ይህ የፓርቲው ሃሳብ ሕዝቡን እና አንዳንድ ተቋማትን ለሁለት ጎራ ከፍሏቸዋል። የስዊስ መንግሥት እንዲሁም ሁሉም ትልልቅ ፓርቲዎች፣ የንግድ ድርጅት ኃላፊዎች እና የንግድ ማኅበራት በበኩላቸው " ቀውስን የሚጋብዝ " ዕቅድ ነው ሲሉ ተቃውመውታል። ሆቴሎች እና ሆስፒታሎችን የመሳሰሉ አገልግሎት መስጫ ተቋማት አስፈላጊ የሆነ የሰው ኃይል እጥረት እንዲገጥማቸው ያደርጋል ሲሉ ተከራክረዋል። አክለውም አገሪቱ ከአውሮፓ ኅበረት ጋር ያላትን ግንኙነት አደጋ ላይ እንደሚጥለው እና ከኅብረቱ መውጣት ደግሞ በዚህ አደጋ በሞላበት ዓለም ስዊዘርላንድን እንድትገለል እንደሚያደርግ አስረ...

#ሰውኛ #ሥልጣኔ ይናፍቀኛል።

ምስል
  #ሰውኛ #ሥልጣኔ ይናፍቀኛል።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ምዕራፍ ፲፱።   ሽው የሚለኝ ሰውኛ = ሥልጣኔ፤ የሚናፍቀኝ ተፈጥሮኛ = ሥልጣኔ፤ የሚያጓጓኝ = ይቅርታ እና ምህረት፤ የሚርበኝ = ቅንነት እና ርህርህና፤ የሚጠማኝ #ትቅቅፍ ።   የሚያሳሳኝ በብሩህ ዓይን መተያዬት። አንባጓሮ፤ ግጭት፤ ጦርነት ግለት፤ ጭቆና ስልችትችት ብሎኛል። የምር ሰው ሆነን መፈጠራችን ገሃድ ነው። ሰው ሆነን መኖርን ያሰለጠንበት ጎዳናም ዕጹብ ነው። ያቃተን ግን በተፈጠርንበት የሰውኛ ቃና እና #ቅኔ መቆም አለመቻላችን ነው።   ምንም -- የሚያጠላላ፤ -- የሚያቃቅር፤ ፊት የሚያዞር --- እኛ ያልሰራነው ሸር የለም፤ ምንም እኛ ያልታደምነበት የሴራ ማግ እና ድር የለም፤ ምንም እኛ የሌለንበት የምቀኝነት ኔት የለም።   ምንም እኛ ያላሰለጠነው የጥፋት #ጥላቻ የለም። ምንም የሰው ልጅ ማህበርተኛ ያልሆነበት በቀል የለም። ምንም የሰው ልጅ የሌለበት ማሸበር፤ ማስፈራራት፤ ማሳቀቅ፤ ማስደንገጥ የለም።   ከተፈጥሮ አደጋ በመለስ ያሉ የሰው ልጅ እልቂቶች፤ የሰው ልጅ ፍልሰት፤ የሰው ልጅ የሃዘን ዕንባ፤ የሰው ልጅ ጭቆና፤ የሰው ልጅ መገለል የለም። ከተፈጥሮ ችግር ባሻገር ያሉ ሰቅጣጭ ግድያወች፤ ዘረፋወች፤ ውድመቶች ሁሉ የሰው ልጅ እንደ ዳንቴል በእጁ የሠራቸው፤ እንደ ጨርቃ ጨርቅ የሸመናቸው ናቸው።   አንድ ቀን ቀርቶ በአንድ ሰከንድ ውስጥ ስንት የክፋ ሃሳብ ጎርፍ እንደሚያጥለቀልቀን እሰቡት። ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ መተግበሪያ ቱል ነው ብዬ አምናለሁኝ።   እንደ እኔማ የፍቅር ተፈጥሮ ከእናት እና ከስፖርት ማልያ ብቻ ይገኛል የሚል ጽኑ እምነት አለኝ። በናፍቆት፤ በጉጉ...