ልጥፎች

#የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ የመሪወች ጉባኤ ሊጠራ ይገባል።

  #የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ የመሪወች ጉባኤ ሊጠራ ይገባል።   #የሰብ #የተፈጥሮ #የፈጣሪ #ጥላቻ አህጉራችን አፍሪካንም እየናጣት ነው።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፈጠርልኝ።" አሜን።     https://www.bbc.com/amharic/articles/c17ypvpze1po በደቡብ አፍሪካ ስደተኞች እንዲወጡ የተቀመጠው ቀነ ገደብ መቃረቡን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዜጎች እንዲጠነቀቁ አሳሰበ   የሚችሉ የዓለም ዜጎች በወላፈኑ ከመቀቀል #ዞር ቢሉ እና ጊዜውን ቢያሳልፋ ጥሩ ነው። #ጭካኔ #የጥላቻ ውጤት ነው። #ጥላቻ ጭካኔን #ሲያሰርጥ #ርህርህና ይሰደዳል። ለአፍሪካ አሳዛኝ ገጠመኝ ነው። ይህ ንቅናቄ የተደራጀ እና መሪም ያለው ነው። ለዓለምም የሚያስተምረው #ግራጫማነት ነው።   ውስጤ ያዝናል። ማዘን ብቻ ሳይሆን #ይጨንቀኛልም ። ግን የአፍሪካ #ህብረት ምን ይላል? ሸበላ ጊዜ።   ሥርጉትሻ 26/06/026. ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው። See less

ብልፄው የደግነቱ ልክ ለፓርላማ የክብር አባልነት #በቻሪቲ። #በምደባ አገር ምድሩን አንበሸበሸ። ኢትዮጵያም የአማራ ህዝብም ሚስ ያደረጓቸው ጨዋ፤ ጭምት፤ አስተዋይ ሰብዕና።

ምስል
  ኢትዮጵያም የአማራ ህዝብም ሚስ ያደረጓቸው ጨዋ፤ ጭምት፤ አስተዋይ ሰብዕና። ብልፄው የደግነቱ ልክ ለፓርላማ የክብር አባልነት #በቻሪቲ ። #በምደባ አገር ምድሩን አንበሸበሸ።   #አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።    https://www.youtube.com/watch?v=I_7EVUEbSqE   በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ውጤት ያልቀናቸው ዶክተር አበባው ደሳለው ውጤቱ ያልጠበቁት መሆኑን ተናግረዋል | Abebaw Desalew | Ethiopia Inisder   ብልፄው ለውስጦቹ የፓርላማ ወንበር #ቻሪቲ በ7ኛው ምርጫ ገፋ አድርጎ አንበሽብሿቸዋል። መጠራቅቁ ከተቻለ። ወጥ ሃሳብ። ወጥ ፍላጎት። የሁሉ እሽታ እና ይሁንታ በገፍ ……… የማያጓጓ የማይስብ ይሆናል። በድርጅታዊ ሥራ ሞጋች ተሁኖ ሊወጣ ይችል ይሆናል። ያለፍጥረቱ ያለልኩ የተሰፋ እጀ ጠበባ ወይንም ጥብቆ ይሆናል። እራስን የሚያጸናው የራስ ጥረት ብቻ ነው። በሙሉ ጥገኝነት እና ጥገና እራስን ለማግኜትም፤ ሆነ ለመሆን ጋዳ ይሆናል።   #ዕፍታ ።   ለሰከነ፤ ምራቁን ለዋጠ፤ ጥድፊያን ሃራም ለሚል ሰብዕና የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፎርማት የሚመች አይመስለኝም። ምክንያቱም ሴራ ገብ፤ ኢጎ - ገብ ስለሆነ። የ6ኛው አገራዊ ምርጫ ተካሂዷል። ተጫኝ ሁነቶች የተደራጄ ቀውስ ግብዓቶች የፍርሃት፤ የስጋት፤ የጭንቀት ጫና ነበር። ከዘንድሮ ግን የተሻለ የነበረ ይመስለኛል። የ7ኛው አገራዊ ምርጫ #ምደባ ነው።    ብልፄው ሁሉንም ተቆጣጥሮ በሥሩ ያስተዳደረበት እና ቦታወችን አቅዶ የደለደለበት ሁኔታ ነው የታየው። ውጤት ለመንገር መዝግየቱም ለዚያ ነው። ፌስታውን ተመልክቻለሁኝ። ይህ አይጠቅምም። እራስን መሸንገል ስለሚሆን። ዕውነ...

ህይወት ያለው ሁሉ #ይተነፍሳል። ይህን መዝጋት ከሰጪው ከፈጣሪ ጋር #መጣላት ነው።

ህይወት ያለው ሁሉ #ይተነፍሳል ። ይህን መዝጋት ከሰጪው ከፈጣሪ ጋር #መጣላት ነው።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"    #ምዕራፍ ፲፱።   #እሺ ! አይዋ ብልፄው እንዴት ሰነበትክ?    ፌስታውስ እንዴት እያደረገህ ነው?   ብልፄውሻ ደስታው እንዴት እያደረገህ ነው? ጥምር ደስታ 100%: ፓርላማህን ጠቅልለህ ቁብ አልክበት። አባ #ጠቅልልነት በተዘዋዋሪ። ከዚህ እዚህማ ሞናርኪያዊ ለምን አታደርገውም ሥርዓትህን? የምሬ ነው። ተረብ አይደለም።   የሚገርመኝ ደግሞ በለስ ይቀናኃል ፮ኛው ምርጫ ኮረናና ጦርነት፤ ፯ኛው የሆርሙዝ ሰርጥ ፈተና ለአንተ ኮረቻ ድልዳል ሆነውልኃል። በዚህ ውስጥ ስጋት - ጭንቀት - #ይመርጥኃል ። ሌላዋ ዲል ያለ ደስታ በነገረ ህወሃት ላይ ደግሞ አገኜህ፤ ቀንቶኃል።   ነገረ ህወሃትን የመቋቋም አቅምህ ግን #አቅቶህ ነበር። ሁለቱንም የምርጫ ሥርዓት ባን ሆኖበኃል። ኮሪደር ሎጂ ብሎ ነገር እዛ እንዳታስብ አድርጎህ ነበር። ትውር ለማለትም፤ ለማዘዝም ጋራ ነበር።    #የሆነስ ሆኖ #አይዋ ብልፄው ……   ግን አንድ ትሁታዊ ጥያቄ አለኝ። ስንት #እስር ቤት ለመስራት አቅደሃል? ምን ያህል የኮሪደር ልማት በቅሊንጦ፤ በገላን፤ በዝዋይ ለመሥራት ተልመኃል? የአዲስ አበባው የቢላ እስር ቤቶችህ ያው በአዲስዬ #የመናፈሻ ፕሮጀክት ቅምሻ ቢጤ አላቸው ብዬ ነው። ጠበለ ጣዲቁ ይደርሳቸዋል እንደማለት።    ብልፄው ቆይ እስቲ! ግን አንተ ማሰር - ማፈን - #አይሰለችህም ? በቃ! መደበኛ የእስር ሂደት ሥራህ ሆቴል የመሥራቱ ያህል ከቀለለህ ቅልጥፍና ጋር #በአቻነት እያስኬድከው ነው። በድሬ አንድ እጩ ተወዳዳሪ ዶር #ሃኪም ማ...

#የኮፒራይቱ የይገባኛል ፉክክሩ ተጧጡፏል። ዕልፍኘ - #ትራንፒዝም እንዳሻ የሚወጣበት የሚገባበት አይደለም።

ምስል
  #የኮፒራይቱ የይገባኛል ፉክክሩ ተጧጡፏል። ዕልፍኘ - #ትራንፒዝም እንዳሻ የሚወጣበት የሚገባበት አይደለም።   «ለቁጣ የዘገየ ፍቅሩም የበዛ ነው።» ( መዝሙር ፻፫፤ ፰)   #ምዕራፍ ፲፰።   «አሜሪካ በህወሓት መሪዎች እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ማዕቀብ ጣለች» ዘገባው የቢቢሲ ነበር።    መቼም ለማህበረ ህውኃት አካልን ሳይሆን መንፈስን #መቅኖ አልቦሽ የሚያደርግ ውሳኔ ነው። ሰሟናቱ የነሃሴ ዝናብ ጨቀጨቅ ሳይመጣ የህወሃትን የተንጠራራ መሻት እሳት ውስጥ የገባ #ፕላስቲክ የሚያደርግም ነው። #ኩፍትርትር ።   የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ ፖለቲከኞች ዕውቅና ይሰጡት ዘንድ ትሁታዊ ማሳሰቢያ የምሰጠውም ለዚህ ነው። በዘመነ ኢሠፓ የዘመኑ የፖለቲካ ባህሬ አንድ ሳብጀክት ነበር። አቅምህን ማቀድ፤ ወደ ተግባር ለመቀዬር #ቀያሹ የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ መረዳት ሲቻል ነው።   ይህ ዘመን ቋሚ ባህሬ #ስለሌለው ተለዋዋጩን ባህሬውን በመከታተል እራስን ማጣጣም Update ማድረግን ግድ ይሆናል። ዲታ ተሆነ፤ ደኃ። በሌላ በኩል #ትራንፒዝምን ማንበብ፤ መተርጎም እና ማመሳጠርም ከባድ ነው። የዘመኑን ባህሬ አውቆ ለመሰናዳት #አቃች ሁነቶች አሉበት። ግን ዝንባሌውን በስሱ መገመት ይቻላል። ከፖለቲካዊ አቅም ይልቅ #ቢዝነሳዊ ባህሪው፤ አትራፊ ቅያሶች ለዘመኑ የፖለቲካ ባህሬ መሃንዲስ እንደሆኑ ማስተዋል ይቻላል።   አንድ ምሳሌ ባነሳ …… ፋርስን ስታስቡ በዚህን ያህል አቅም ዓውራ ሆና ለመውጣት ዳጥማ ዳገቱን ተቋቁማ እዚህ ትደርሳለች ብሎ መገመት አይቻልም ነበር። አሁን እኮ የአህጉርነት አቅም ብቻ ሳይሆን ድምጽን በድምጽ የመሻር መብት ካላቸው አገሮች ጋር #መሳ ለመሳ የሚያቆም ሁነት ላይ ነ...