ልጥፎች

#አብይዝም እና ሥነ - መንግሥታዊ #ፕሮቶኮል።

ምስል
  #አብይዝም እና ሥነ - መንግሥታዊ #ፕሮቶኮል ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።"       #ምዕራፍ ፲፰።   ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ናት ማለቱ ብቻ በቂ አይደለም።    ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ለፕሮቶኮል ሥርዓት የሚመቹ #መሪ አይመስሉኝም። በፕሮቶኮላዊ ዲስፕሊን ሥር ለመንቀሳቀስም የሚፈቅዱ አይመስለኝም። ይህን ለ፱ኛ ዓመት ዋዜማ ላይ ከሚገኘው የመንግሥታቸው አፈፃጸም ሂደት ግብረ መልስ ያገኜሁት መረጃ ነው።   ቀድሞ ነገር በአብይዝም #ፕሮቶኮል ሙያ እንደሆነ አብይዝም ይቀበለዋል ብዬ አላምንም። ለአፍሪካው ስብሰባ መሪወች አቀባበል ሲደረግላቸው አንዲት ሴት አይቻለሁኝ። ይህ በተቋም ደረጃ ይሁን አይሁን አላውቅም። ወይንም የአፍሪካው ህብረት አዘጋጅቶ ይሁን አላውቅም።   የሆነ ሆኖ አንድን አገር እንደ መንግሥት #ሊያቆመው ፤ #ሊያጸናው ፤ ሊያስከብረው ከሚችሉ በኽረ ጉዳዮች መካከል #ሥርዓት ወሳኝ ጉዳይ ይመስለኛል። በአብይዝም ዘመን የፕሮቶኮል ሹም የሚባልም ሰምቼ አላውቅም። በደርግ ጊዜ የኮነሬል መንግሥቱ የፕሮቶኮል አገልግሎት የሚሰጡ ደልደል ያሉ ፍጹም ታማኝ ሴት እንደነበሩ አስታውሳለሁ። ይህ በተዋረድ በክ/አገር፤ በአውራጃ እና በወረዳ በጽህፈት ቤት አገልግሎት ሥር ይመራ ነበር።    አቀማመጥ #በሲነሪቲ ነው። ዝንፍ የለም። አለባበስም በስብሰባ #ደማቅ ሰማያዊ ካኪ፤ በመደበኛ ሥራ ካኪ ቀለም እና ድብ ያለ ድባ ነገር ይለበሳል። እኔ አመጸኛ ነገር ነበርኩኝ። ቅዳሜ እና እሁድም፤ ዓውድ ዓመታትም ሥራ ላይ ስለነበርን በእነኝህ ቀናት ካኪ አለብስም ነበር። የተለዬ ልብስ ለብሼ ነበር ቢሮ እምገባው። ትርፍ ሰዓቴ ስለሆነ።   እራሱ ካኪውን በፋሽን ዲዛ...

የኢትዮጵያ Mastermind ለመሆን የተሰለፋ አገራት እና የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መጥኖ የመነሳት መቅኖ አስፈላጊነት።

ምስል
  የኢትዮጵያ Mastermind ለመሆን የተሰለፋ አገራት እና የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መጥኖ የመነሳት መቅኖ አስፈላጊነት።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰   ብዙ በጣም ብዙ ሁነቶች በኢትዮጵያ ሰሞኑን ተስተናግዷል። በላይ በላይ ፋታ አልቦሽ ሁነቶችን ሳይ በ2010 እኢአ ስደት ላይ የነበሩ ኢትዮጵውያን፤ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አገሮች ሁሉ ወደ ኢትዮጵያ ይጓዙ ነበር። ፖለቲካው ገና #ችግኙ ከፈልነት ሳያልፍ የገነገኑ ሁነቶችን እንደምን ማኔጅ ማድረግ እንደሚቻል እራሱን የቻለ አካልም ሳይኖር የነበረው ዲል ያለ ሁነት ይገርመኝ ነበር። ጎንደሮች ባለቅኔ ናቸው። ይህን መሰል ሁነት ሲገጥም "ራስ ሳይጠና ጉተና" ይሉታል።   ሰሞኑን ያዬሁትም አብይዝም የ፯ ዓመታት ልምድ ቢኖረውም፤ በጎኑ ማን አለ እራሱን የቻለ ተብሎ ሲታሰብ አንድ ሁለት ሊኖሩ ቢችሉም ብዙው የአብይዝም ቀጥተኛ መንፈስ ጥገኛ ነው። ከንቲባ ጽህፈት ቤትን፤ ጠቅላይ ሚር ቢሮን፤ ውጭ ጉዳይ ሚኒስተርን ለናሙና ማንሳት እችላለሁኝ።   አብዛኛው የሁለመና ሁነት የአብይዝም መንፈስ ጥገኛ ነው። ይህ ደግሞ አደጋው ብዙ ነው። እንጂ፤ እንጂማ በዚህ ወላፈን ውስጥ የማይቀርበትን አንዱን ኢቬንት ከውን፤ ለሌላው በቂ ጊዜ ሰጥቶ፤ አስታግሶ ፤ ሳይጠዳደፋ፤ ትንፋሽም ሰብስቦ ማስተናገድ ይገባ ነበር። -------------- የገረመኝ ደግሞ፤ በዛ ሁነት ሰንብተው ጠቅላይ ሚኒስተሩ ትናንት ወለጋ ነበሩ፤ በ100 ቀናት ውስጥ ዶር ለማ መገርሳን እና እሳቸው የተሞገቱበት ደንቢደሎም በጉብኝቱ ተካታ ተመልክቻለሁኝ። ያን ጊዜ ጽፌበትም ነበር ስለ ነገረ ደንቢደሎ፤ ሊዮዋቸው እንኳን ፈቃደኞች አልነበሩም። አኩርፈው ነበር የተቀበሏቸው።    ብቻ፤ አወን ብቻ...

#ፖለቲካ #ብልህነት #ይጠማዋል። እንደ መከወኛ።

ምስል
  ቅንነት የህሊና #ቀበቶ ቢሆን፤ አቅልም ቢፈቀድለት ስል በትህትና ቤተ- ሥርጉትሻ ታዳሚወችን እጠይቃለሁኝ።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፰     የበደሉ መነሻ እና መድረሻ በጥልቀት ሊጠና የሚገባው ነው። ባለፋት ፰ ዓመታት የሆኑት ነገሮች ሁሉ በተለይ እንደ እኔ ከሁሉም ነገር እራሱን አግልሎ ግን የአገሩን፤ የአህጉሩን፤ የዓለምን ሁኔታ የሚከታተል ሰብዕ አደብ ገዝቶ፤ በጥሞና ሆኖ የቀውስ ወጀብ መነሻውን ይሁን መድረሻውን ሊመረምር ይገባል። አቅም የወንዝ ዳር #አሽዋ አይደለምና።    በገፍ ሌት እና አቅም መግበን፤ ልዩ ልዩ ስለ ሰብ ግድ የሚላቸውን ተቋማትን አስተባብረን፤ የተከበሩ የዓለም ሊቃናትን በር አንኳኩተን፤ ደፍረን #መስክረንም መንበር ላይ ካስቀመጥን በኋላ፤ በዓለም መድረክ እናት አገር ኢትዮጵያ እንደባይታዋር ሆና " #ኢትዮጵያ #አጀንዳዬ አይደለችም" የሚልን መርዶ ነው እኔ ያዳመጥኩት። ሰውነቴ ነበር የተንቀጠቀጠው። ለእኔ ከኢትዮጵያ በላይ አጋይስትዓለሙ ሥላሴ ቅድስት እናቴ ድንግል ማርያም እና ቅዱሳን ፃድቃን እና ሰማዕታት ነው ያሉት።    የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ እንደ ነውር ይታይ በነበረበት ጊዜ ተማግደንበታል። ዛሬ ከሚዲያ ላይ፤ በየፖለቲካው ፎረም ያለው #መቧደኑም ፤ ወጨፎውም ማንን እንደሚገርፍ በጥሞና እየተካተትልኩት ነው። ቢያንስ እቆምለታለሁ ለሚባለው ማህበረሰብ #አንዱን ጥሎ ሌላውን አንጠልጥሎ ሊሆን አይገባም ነበር። እንመራለን ካሉ። እኛማ አማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰው ሁለገብ በደል በአመክንይ ስንሞግት፤ ስለአፋሧ እናትም፤ ስለ ጌዲዋ እናትም፤ ስለተጋሩ እናትም፤ ስለኦሮሞ እናትም፤ ስለ አማሮ እናትም ወዘተ እንደምንታገለው ነበር የታ...