#የ2018ዓ.ም የምርጫ መቅድመ ሙግት ካዳመጥኩት - ትዝብቴ።
#የ2018ዓ .ም የምርጫ መቅድመ ሙግት ካዳመጥኩት - ትዝብቴ። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።" #ምዕራፍ ፲፰። «የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመጀመሪያው የክርክር መድረክ» https://www.youtube.com/watch?v=DG6SHFL76_0 ሊንኩን በጥዋቱ ሼር አድርጌዋለሁኝ። በተጨማሪም መቅድመ ውይይት ስለሆነ ልፅፍበት ፈለግሁኝ። በቅድሚያ የሴቶች ተሳትፎ ለፆታ ተዋፆ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሴቶችን የፖለቲካ ግንዛቤ አቅም ጋር አቻ ሆኖ ሲገኝ ተስፋ ሰጪ ነው። እኔ ለሴቶች ተሳትፎ ልዩ ስስት አለኝ። ሴት ስለሆን ብቻ መድረክ ይሰጠን አይደለም። እእ። አቅም ያላቸው ሴቶች ተመጣጣኝ የፖለቲካ ውክልና ሊሰጣቸው ይገባል ነው የእኔ የትግል ማዕከል። በዘርፋ የፖለቲካ ሊቃናት ሴቶች ከእነሱ #ድፍረት ማነስ ካልሆነ በዘመነ አብይዝም ያለው ሁነት የሚያበረታታ ነው። ብዙ የፖለቲካ ሴት ሊቃናት ወደፊት መጥተዋል። ይህ የውሳኔ አቅም በአወንታዊነት የማየው ነው። ሌሎችም ተፎካካሪወች ይህን አትራፊ እና ቀና መንገድ በመከተላቸው አመሰግናቸዋለሁኝ። 1) #የመወዳደሪያ ዓርማ። 1.1) የስንዴ ነዶ ባለፈው በስፋት ስለገለጽኩት አልመለስበትም። ነዶ (የጨርቅ ነዶ፤ የእሳር እህል ነዶ፤ የመቃጠል ዓዋጅ፤ የብስጭት መግለጫ) ቃሉ ለማስታወስ ያህል አሻሚ ትርጉም ያለው ስለመሆኑ አጠይቄ ብቻ አልፈዋለሁኝ። (የብልጽግና የምርጫ መወዳደሪያ መለያ ነው የስንዴ ነዶ።) 1.2) ሚዛን። ከገጠር እስከ ከተማ የሁሉንም ትርታ የሚገዛ ነው። (የኢዜማ የምርጫ መወዳደሪያ መለያ ነው ሚዛን።) 1.3) የእጅ ባትሪ። የግል የሆነ፤ ማንም የማያዘ...