#ትህትናችሁ ዘወትር ቁሞ ለሚያስተምረኝ ቅኖቼ ሁሉ።
#ትህትናችሁ ዘወትር ቁሞ ለሚያስተምረኝ ቅኖቼ ሁሉ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። የምትናፍቁኝ፤ የምሳሳላችሁ፤ አዘውትሬ የማስባችሁ፤ ክብሮቼ የአገሬ ልጆች እንዴት አድራችሁ፤ አርፍዳችሁ፤ ዋላችሁልኝ? እኔ እግዚአብሄር ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። የምርም ደህና ነኝ። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በዓጤ ፌስቡክ ዕይታዬን #በምራፍ ከፋፍዬ ሥሰራ ቆይቻለሁኝ። እስከ አሁን ፲፰ ምዕራፎችን ሠራሁኝ። ሳጠናቅ አዲስ ምዕራፍ ከመጀመሬ በፊት ጥሞና እወስዳለሁኝ። ምዕረፍ ፲፰ ረጃጅም የወግ ገበታወችን ያቀርብኩበት ምዕራፍ ነበር። በብሎጌ ላይም ሰፊ አንባቢ አግኝቷል። ጹሁፎቹ በብዙ ሁኔታወች ያልተደጋገሙ፤ አትኩሮቱም በተለዬ የእኔ ምርጫ የሆኑትን ብቻ በመለየት አቅም ተመግበዋል። ምዕራፎቼ ሚዲያው ሁሉ ከሚረባረብበት አጀንዳ #ወጣ ያሉ ሃሳቦች የቀረበበት ነበር። አስፈላጊ ሲሆን ሁሉም እንደ አጀንዳ ያዬው ግን #ሲርገበገብ ሳይሆን ሲሰክን ለመዳሰስ ሞክሬያለሁኝ። ይህ ፔጅ አክሰሱ ላላቸው ታዳጊ ወጣቶች ከሁሉም የአያያዝ፤ የአመራር፤ የአነጋገር፤ የአፃፃፍ ኢትዮጵያዊ ሥርዓታዊ ሂደት ይማሩበት ዘንድ በፍጹም ጥንቃቄ ለመሥራት ሞክሬያለሁኝ። ከዚህ ፔጅ ያልተገቡ ፆታዊ ጉዳዮች፤ ቃሎች ኖረው ግን ከደረጃ የሚያወርድ የአፃፃፍ ዘይቤወችን፤ ከፎቶ ላይ የሚፃፋ #ነውረኛ ሁነቶችን፤ ኢትዮጵያ መለያዋ ከሆነው አክብሮ ከመፃፍ፤ ከመሞገት አንፃርም #አንቱታን በማስቀጠል፤ ሙሉ ስድስት ዓመት በትጋት ስለሰራሁበት ፔጃችን በዲስፕሊን የታነጹ የሁሉም ፖለቲካዊ ዕይታወች፤ የሁሉም ዕምነት ዶግማና ቀኖናወች አክብሮ ሲያስተናግድ ቆይቷል። በዚ...