ልጥፎች

#ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ #ሐዋርያ ነው - ለእኔ። አዶናይወዲላን።

ምስል
      #ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ #ሐዋርያ ነው - ለእኔ። አዶናይወዲላን።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   ክፋ ሃሳብ በእጅጉ እየፈተናት በምትገኜው እቴጌ ዓለማችን ስፖርት ነፍስ ሆኖ፤ ነፍስ ሰጥቶ፤ ፍቅር ሆኖ፤ ፍቅር ሰጥቶ ይሞግተዋል ክፋ ሃሳብን። ከስፖርት ውስጥ አንዱ እግር ኳስ ነው። ዕውነተኛው የፍቅር ተፈጥሮ የሚገኘውም #ከእናት እና #ከስፖርት #ማልያ ነው ብዬ አስባለሁኝ። ለዚህ ነው አዘውትሬ ልብ ሳይሆን እናት ትሁን የፍቅር ተፈጥሮ የምለው።   በዓለማችን ክፋ ሃሳብን ሞግቶ የሚያሸንፍ፤ ዕለታዊ ተግባሩ የፍቅር ተፈጥሮ የሆነ የማስተማሪያ፤ የሚዲያ፤ ዓለም ዓቀፍ ተቋም ባይኖርም የስፖርት ማልያ ግን ይህን ኃላፊነት ለመወጣት አዘውትሮ ይጥራል።   የዓለም የሳቅ ጊዜ የዕውነተኛው አለ፤ ወይንም ተገኜ ከተባለ ከስፖርት ፍቅር እና ከእናት የሚፈልቀው ወይንም የሚመነጨው #ንጽህና ስለመሆኑ አምናለሁኝ። እግር ኳስ ፍጹም ልዩ ነው። #የሐሤት ተልዕኮ የተሰጠው። የዓለምን ሙሉ አደብ በፍቅር የሚገዛ።   እኔ እግር ኳስ እወዳለሁኝ። ለረጅም ጊዜ በአምደኝነት በተሳተፍኩባቸው ፔጆች፤ በራሴም ሚዲያ ዘገባውን እሰራለሁኝ። ማዬት በማልችልበት ጊዜ ከስደት ወደ ስደት ሂጄ የአውሮፓን እና የዓለም ዋንጫን እከታተል ነበር። በፍቅር፤ በጉጉት ከውስጤ ደስ ብሎኝ የምመለከተው የመኖር አርት ቢኖር #እግር ኳስ ነው።   የዓለምን አርቲቡርቲ፤ የዓለምን ኳኳቴ፤ የዓለምን የክፋ ሃሳብ ፈተናን ረሳ አድርጋችሁ ወደ ዕውነተኛው የመፈጠራችን ሚስጢር፤ ወደ ንጽህናችን የሚወስደን ጎዳና ቢኖር ለእኔ እግር ኳስ ነው።   የእግር ኳስ ፍቅር #አያረጅም ። የእግር ኳስ ፍቅር...

#የአገር መሪን የሥልጣን ጊዜ ስለመገደብ የእኔ ዕይታ። "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ።"

  #የአገር መሪን የሥልጣን ጊዜ ስለመገደብ የእኔ ዕይታ።    "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ።"   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   ብዙ ተቃዋሚወች ይሁኑ ተፎካካሪወች ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን አቅልሎ የማዬት የወል ባህሪ አይባቸዋለሁ። ልምድ እንደሌላቸውም ሲናገሩ አድምጫለሁኝ።    በቂ ልምድ አላቸው። ሚሊተሪ ላይ ሠርተዋል፤ በተመድ ፕሮጀክት ተሳትፈዋል፤ ከኢንሳ መስራችነትም አሉበት በዛው ተቋም መሪነቱም ታክሎ ልምድ ይገበይበታል፤ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂን በሚር ደረጃ መርተዋል፤ የኢህአዴግ የፓርላማ አባል ነበሩ፤ በኦሮሚያ የተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ሠርተዋል። ይህ በቂ ነው።    የኢትዮጵያ መሪ ከሆኑ በኋላ እሳቸው የሚያምኑበትን መስመር ተግተው ነው የሚሠሩት። ቢሮክራሲው ላይ የሉበትም መስክ ላይ፤ ፕሮጀክት ተኮር ጉዳዮችን ይወጥናሉ፤ ይፈጽማሉም። ዳሽ የሆነው ሰብአዊነት ላይ ነው የማጽናናት፤ አይዟችሁ የማለት፤ በተከፋት ቀዬ በህዝባቸው ውስጥ ተገኝተው ጥግ የመሆን አቅም አለመኖር። እስር ላይ ያለው የማይገፋ ተራራ። ሌላው ዳሽ የሆነው የቢሮ አስተዳደራዊ ሥራም ነው። በተጨማሪም የሌሎችን መከፋት #አቅለው ማዬታቸው፤ ለመፍትሄው አለመትጋታቸው ዳሽ ነው።    ጠቅላይ ሚር መለስ ዜናዊ የትኛው ተቋም ላይ ሠርተዋል? ከጫካ ህይወት ቤተ- መንግሥት። በቃ! ዕውነቱ ይሄ ነው። ያለውን #ዕውነት #ማስከፋት አያስፈልግም። ከዚህም ሌላ መሪነት ፈቃደ እግዚአብሄር፤ ቅብዓ ስለመኖሩም ማመን ያስፈልጋል።    የሆነ ሆኖ አገራዊ ምክክሩ ለምን እንዳስፈለገ፤ ከዛ በፊት ለሙከራ አቋቁመው ያፈረሷቸው ኮሚሽኖች ሁሉ በመደዴ ታስበው የተከ...

በነገረ ሐራ መሬት የነገ #ስጋቴን ብገልጽስ? #ነገን ሰላማዊ ተከታይ ስለማድረግ።

  በነገረ ሐራ መሬት የነገ #ስጋቴን ብገልጽስ?   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ።   በብልጽግና መንግሥት የተፈቀደለት ሽምቅ ተዋጊ ኃይል በአፋር እንዳለ ሳድምጥ ቆይቻለሁኝ። ለሽምቅ ኃይሉ የፖለቲካ ክንፍ እንደተደራጀለትም ይገባኝ ነበር። ግን የእኔን የመረዳት መጠን መሬት ላይ ካለው የራሱ አካል ማረጋገጫ እስኪሰጥበት ድረስ ጸጥ ብዬ መጠበቅ ነበረብኝ።   ሰሞኑን በአርተስ የዜና ዕውጃ ከስምረት ፖለቲካል ፓርቲ በተገኜ መረጃ መሰረት የኃራው ታጣቂ ሸማቂ ኃይል ክንፋ እንደሆነ ዜናው ያትታል። እኔም አውቄው ስለነበር አላስደነገጠኝም። እንዲህ ገልፆ መናገር መልካም ነገር ነው።   #ጥቃትን መቅደም እና መቀደም።   በጣም ከሚያሳዝኑኝ የዓለም ማህበረሰብ ውስጥ ሊባኖናውያን አንዱ ናቸው። ሊባነን መንግሥት አላቸው። መንግሥታቸው ግን ለህልውናቸው ቀጣይነት የደህንነት ዋስትና የመስጠት አቅም የለውም።   አቅሙ ያለው ከመንግሥት ውጭ የሆነው #ሂዝቦላ ነው። የሂዝቦላ የፖለቲካ ክንፍ የሊባኖስ ማዕከላዊ መንግሥት ሳይሆን አገረ #ኢራን ናት። የኢዝቦላ ተቋማት ሁሉ በሊባኖሳውያን ውስጥነት ታዳሚወች ናቸው። ወጩ የሚሸፈንለት በኢራን መንግሥት ነው። የሂዝቡላ የፖለቲካ ያው ሃይማኖታዊ ነው፤ የታጣቂ ኃይል መሪ የኢራን መንግሥት ፖለቲካ ነው።   ሂዝቦላ ለሚወስደው እርምጃ ዋጋ የሚከፍለው ደግሞ መከረኛው የሊባኖስ ህዝብ ነው። ይህ ወጣ ገብ ሁነት የተፈጠረው ከጥንስሱ የሊባኖስ መንግስት የራሱን የፖለቲካ፤ የሚሊተሪ ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ባለመቻሉ ነው። የዘገዬ እና ፍዝ አቋም ያለውም ነው። አሁን የሊባኖስ ንጹኃን የሚከፍሉት ዋጋ ተመን ሊወጣለት የማይችል ነው። ከሊባኖ...