#አብይዝም እና ሥነ - መንግሥታዊ #ፕሮቶኮል።
#አብይዝም እና ሥነ - መንግሥታዊ #ፕሮቶኮል ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" #ምዕራፍ ፲፰። ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ናት ማለቱ ብቻ በቂ አይደለም። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ለፕሮቶኮል ሥርዓት የሚመቹ #መሪ አይመስሉኝም። በፕሮቶኮላዊ ዲስፕሊን ሥር ለመንቀሳቀስም የሚፈቅዱ አይመስለኝም። ይህን ለ፱ኛ ዓመት ዋዜማ ላይ ከሚገኘው የመንግሥታቸው አፈፃጸም ሂደት ግብረ መልስ ያገኜሁት መረጃ ነው። ቀድሞ ነገር በአብይዝም #ፕሮቶኮል ሙያ እንደሆነ አብይዝም ይቀበለዋል ብዬ አላምንም። ለአፍሪካው ስብሰባ መሪወች አቀባበል ሲደረግላቸው አንዲት ሴት አይቻለሁኝ። ይህ በተቋም ደረጃ ይሁን አይሁን አላውቅም። ወይንም የአፍሪካው ህብረት አዘጋጅቶ ይሁን አላውቅም። የሆነ ሆኖ አንድን አገር እንደ መንግሥት #ሊያቆመው ፤ #ሊያጸናው ፤ ሊያስከብረው ከሚችሉ በኽረ ጉዳዮች መካከል #ሥርዓት ወሳኝ ጉዳይ ይመስለኛል። በአብይዝም ዘመን የፕሮቶኮል ሹም የሚባልም ሰምቼ አላውቅም። በደርግ ጊዜ የኮነሬል መንግሥቱ የፕሮቶኮል አገልግሎት የሚሰጡ ደልደል ያሉ ፍጹም ታማኝ ሴት እንደነበሩ አስታውሳለሁ። ይህ በተዋረድ በክ/አገር፤ በአውራጃ እና በወረዳ በጽህፈት ቤት አገልግሎት ሥር ይመራ ነበር። አቀማመጥ #በሲነሪቲ ነው። ዝንፍ የለም። አለባበስም በስብሰባ #ደማቅ ሰማያዊ ካኪ፤ በመደበኛ ሥራ ካኪ ቀለም እና ድብ ያለ ድባ ነገር ይለበሳል። እኔ አመጸኛ ነገር ነበርኩኝ። ቅዳሜ እና እሁድም፤ ዓውድ ዓመታትም ሥራ ላይ ስለነበርን በእነኝህ ቀናት ካኪ አለብስም ነበር። የተለዬ ልብስ ለብሼ ነበር ቢሮ እምገባው። ትርፍ ሰዓቴ ስለሆነ። እራሱ ካኪውን በፋሽን ዲዛ...