#ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ #ሐዋርያ ነው - ለእኔ። አዶናይወዲላን።
#ስፖርት የፍቅር ተፈጥሮ #ሐዋርያ ነው - ለእኔ። አዶናይወዲላን። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፱። ክፋ ሃሳብ በእጅጉ እየፈተናት በምትገኜው እቴጌ ዓለማችን ስፖርት ነፍስ ሆኖ፤ ነፍስ ሰጥቶ፤ ፍቅር ሆኖ፤ ፍቅር ሰጥቶ ይሞግተዋል ክፋ ሃሳብን። ከስፖርት ውስጥ አንዱ እግር ኳስ ነው። ዕውነተኛው የፍቅር ተፈጥሮ የሚገኘውም #ከእናት እና #ከስፖርት #ማልያ ነው ብዬ አስባለሁኝ። ለዚህ ነው አዘውትሬ ልብ ሳይሆን እናት ትሁን የፍቅር ተፈጥሮ የምለው። በዓለማችን ክፋ ሃሳብን ሞግቶ የሚያሸንፍ፤ ዕለታዊ ተግባሩ የፍቅር ተፈጥሮ የሆነ የማስተማሪያ፤ የሚዲያ፤ ዓለም ዓቀፍ ተቋም ባይኖርም የስፖርት ማልያ ግን ይህን ኃላፊነት ለመወጣት አዘውትሮ ይጥራል። የዓለም የሳቅ ጊዜ የዕውነተኛው አለ፤ ወይንም ተገኜ ከተባለ ከስፖርት ፍቅር እና ከእናት የሚፈልቀው ወይንም የሚመነጨው #ንጽህና ስለመሆኑ አምናለሁኝ። እግር ኳስ ፍጹም ልዩ ነው። #የሐሤት ተልዕኮ የተሰጠው። የዓለምን ሙሉ አደብ በፍቅር የሚገዛ። እኔ እግር ኳስ እወዳለሁኝ። ለረጅም ጊዜ በአምደኝነት በተሳተፍኩባቸው ፔጆች፤ በራሴም ሚዲያ ዘገባውን እሰራለሁኝ። ማዬት በማልችልበት ጊዜ ከስደት ወደ ስደት ሂጄ የአውሮፓን እና የዓለም ዋንጫን እከታተል ነበር። በፍቅር፤ በጉጉት ከውስጤ ደስ ብሎኝ የምመለከተው የመኖር አርት ቢኖር #እግር ኳስ ነው። የዓለምን አርቲቡርቲ፤ የዓለምን ኳኳቴ፤ የዓለምን የክፋ ሃሳብ ፈተናን ረሳ አድርጋችሁ ወደ ዕውነተኛው የመፈጠራችን ሚስጢር፤ ወደ ንጽህናችን የሚወስደን ጎዳና ቢኖር ለእኔ እግር ኳስ ነው። የእግር ኳስ ፍቅር #አያረጅም ። የእግር ኳስ ፍቅር...