ልጥፎች

#ምርጫው ቢራዘምስ? መሪው የምርጫ ምልክት #ነዶ ምርጫው ታስቀጥል ይሆን? ብታራዝመው አይሻልህምን?

  መሪው የምርጫ ምልክት #ነዶ ምርጫው ታስቀጥል ይሆን? ብታራዝመው አይሻልህምን?    ግን ቆረጠ #ብልፄው 7ኛ አገራዊ ምርጫውን ለመፈጸም?   አገራዊው፤ አህጉራዊው እና ሉላዊው ሁነት ሲታሰብ ምርጫን መፈጸም ወይንስ ማረዝም የቱ ይቀል ይሆን?   ማራዘም ላይ ተጫኝ ሁለገብ ችግሮች አይለዋል። ገና ሳይጀመር ሞት አለ። ራስ ጋይንት ላይ አሳዛኝ ሁኔታ ነው ያለው። ሞቱ ከምርጫ ጋር ተያይዞ ነው።   ማስጠንቀቂያውም እንዲሁ ነው። በከፋኝ ዱር ቤቴ ባሉ ታጣቂወች በኩል #ዋ ! ብትመርጥ// እጩ ሆነህ ብትመረጥ፤ በብልፄው በኩል ዋ! #ባትመርጥ ባትሳተፍ /// እጩ ሆነህ ባትቀርብም ህዝባችን ወከባ ላይ ነው። ጭንቅ ላይ።    #ምርጫው ቢራዘምስ?   #ግን ጉዳዩን ለመንፈቅ ወይ ለ፩ ዓመት ምርጫው #ቢራዘምስ ? አልኩኝ እኔው። ርጋታ የለም። የተረባበሼ መንፈስ ነው ያለው። ውጥረቱ የመንፈስ አና ብሏል። ከኑሮ ውድነቱ፤ ከሰላም እጦቱ ጋር ምርጫ + ጫን ተደል ጭንቀት ተሸክሞ ምጥ ላይ ነው????    በነገራችን ላይ ዴሞክራሲን ባለመለሙ፤ ሰላማቸው በተረጋጋ አገሮች እኮ ምርጫ ልብ ያንጠለጥላል፤ ዘናም ያደርጋል፤ ፋክክሩ ሲጦፍ ትዕይንት ነው።    "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   እኔ ምርጫ መብት ነው ብዬ አምናለሁኝ። መምረጥም /// መመረጥም የመብት ቅኔ ናቸው። ዕድሉ ባያፈስ የሚመለከታችው ሁሉ ቢሳተፋ፤ ሁሉም ቢሳተፋ ጥሩ ነው።   #ግን አጤ ሆርሙዝ ሁለገብ ተጨማሪ ራህብን አውጇል፤ የቤርሙዳ ትርያንግል ያህል እዬከበደ ነው። ከስምምነት ቢደረስ እንኳን የተረጋጋ ሁነት ለመፍጠር ዘለግ ያሉ ወራቶች ያስፈልጉታል እዬተባለ ነው። የኃይል አሰላለፍም ብወ...

#እናታዊነት ታላቁ የህላዊነት ህቅታ፤ ኖታዊ አንከር፤ #የትውልድም እዮራዊ ብራ!

  #እናታዊነት ታላቁ የህላዊነት ህቅታ፤ ኖታዊ አንከር፤ #የትውልድም እዮራዊ ብራ!   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፈጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   እናትነት የርህርህና፤ የደግነት፤ የፍቅር ኃላፊነትን ጠንቅቆ የመወጣት እዮራዊ አቅምን፤ ክህሎትን፤ ብቃትን፤ ልቅናን በልዕልና የሚያመሳክር፤ የሚያነብ፤ የሚተረጉም እና የሚያመሳጥር ፍፁም የሆነ ጸጋ ነው።   #እናት መጠሪያ ናት። #ዕውነትም ።   እናትን በትክክል ሊገልጹ የማይችሉ ቃላት፤ ሐረጋት፤ ሥንኛት፤ ቅኔያት ሁሉ ሊገልፆዋት አለመቻላቸው ይገርመኛል። ይደንቀኛልም። የሰው ልጅ መቻልን የሰጠው በቻለው ልክ ስለመሆኑ የሚያመሳጥርልንም እናትነትን በሚስጢሩ ልክ ሊሸከም የሚችል አቅም የፊደል ገበታ አለመኖሩ ነው። ታዋቂው የራሺያ ጸሐፊ ፑሽኪን ማስተር ፒሱ " #እናት " የሚለው መጸሐፋ እንዲሆን ያደረገው በእሱ ልክ ለመግለጽ አቻ ከዛ በፊት ያልነበረ መሆኑ ይመስለኛል።    ያም ሁኖ ከዛም በፊት ይሁን ከዛም በኋላ መጸሐፍት፤ ፊልሞች፤ ተውኔቱች በዓለም በእናት ዙሪያ ተሰርተዋል። ጥያቄው የእናትን እናታዊ እዮራዊ ጸጋ መተርጎም ችሏል ወይ ነው ቁምነገሩ። ዕውነት ለመናገር እኔ ድሮ ……… ድሮ ዜማወች፤ መጸሐፍት ስለእናት የገለፆዋት ይመስለኝ ነበር። እናቴን የበሞቴ ልዕልቴን፤ የእሽታ ንግስቴን፤ የናፍቆት እመቤቴን እቭዬ ሆዴን በሥጋ ካጣሁ በኋላ ግን እናት ተመስጥራ የምትገኝበት ቀመር መኖራችን ትንፋሹን፤ ህቅታውን አስቀጣይ ሌላ ተጨማሪ ሚስጢር ሆኖ ነው ያገኜሁት። #እትብታዊ ፍልስፍናዬ ለ፬ ዓመታት እራሴን የሞገትኩበት።   እናት እና ስደት በእናት ህልውና ብቻ የታነጸ ነው። እናት ጋር መራራ ስንብት ሲሆን ቀጥ ይሆናል። ቃ ይመጣል። ዳ ያሸንፋል። ውበ...

#ጊዜን የማድመጥ አቅም፣ ሊደመጥ ይገባል።

ምስል
  #ጊዜን የማድመጥ አቅም፣ ሊደመጥ ይገባል።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፥ ሰው ግን አያስተውለውም።"   #ክፍል ፲፱።   https://www.youtube.com/watch?v=8NoAvavswVk ኢትዮጵያ ቦታዋ አሁን ያለችበት አይደለም | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ETV | EBC | EBCDOTSTREAM https://www.youtube.com/watch?v=sN2roWE6dAs ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰጡት ማብራሪያ   ሼር ባደረኩት ሊንክ ያዳመጥኩት ሲሆን፣ በጉዳይ ላይ ሦስት ጉልህ አመክንዮችን አስተውያለሁኝ። እና ሂደቱን በአራተኛ ደረጃ ላነሳ እሻለሁኝ።   1) ስለ ፕሮፌሰር ዶር. ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስተሩ የተነሳው በጎ ጉዳይ ነው። ገፊ ኃይሉ፣ ስለምን ጎልቶ እንደ ተነገረ ዛሬ ላይ ለእኔ ግልጽ ነው። ባለፈው በሰፊው ጽፌበታለሁ።   2) ስለ የጥበብ ቤተኞች የተሰጠው ማብራሪያ ነበር። "ዓዋቂወች ግን ……… " ጉዳዩን ባለቤቶቹ ይሂዱበት። እኔ በዚህ አገላለጽ የምሻውን ብቻ እገልፃለሁኝ።   3) ስለ " #የሠፈር ' ዕሳቤ በተነሳው ጉዳይ ምልከታዬን አቀርባለሁ።   4) የፕረዘንቴሽኑ #ቶን ፣ ጀስቸር እንዲሁ ብቃኜው ብያለሁኝ።   #አንከር ጉዳዮቼ።   ቁጥር 1) ስለ ፕሮፌሰር ከዚህ ቀደም ስለፃፍኩበት ሊንኩን አስቀምጣለሁኝ። ከእኔ ዕሳቤ ጋር አቻ የሆነ ዕይታ መራመዱን ወይንም አለመራመዱን የእናንተ ህሊና ይመዝነው ዘንድ እተወዋለሁኝ።   ቁጥር 2)    የጥበብ ቤተኞችን የህሊና አቅም ጎልቶ፣ የማህበራዊ ኑሮ ዘይቤያቸው ላይ ስስነት ተወስቷል። እራሳቸው ባለቤቶቹ ስላሉ እሱን ለእነሱ እሰጣለሁኝ። ተመቸ...