ልጥፎች

#መቼ ይሆን - #የሰላም #መቼቱ #በጦቢት?

  • #መቼ ይሆን - #የሰላም #መቼቱ #በጦቢት ?   ጦቢት እንዴት አደርሽ?    እንዴትስ አረፈድሽ? መቼ ነው ቀጠሮሽ #የወኽታ ቀንሽ? ናፈቀኝ ማዕልትሽ የሰላም እንብርትሽ።   "ሃሌ ሉያ። እግዚአብሄርን የሚፈራ፥ ትዕዛዙንም እጅግ የሚወድ ሰው ምስጉን ነው።" (መዝሙር ፻፲፩ ቁጥር ፩)   እባክህን አማኑኤል ሆይ! የሰጠህንን #የውስጥህን #ሰላምህን በህሊናችን #ዘርተህ #አብቅል ! አብቅለህም #አስብልልን ። አሜን። ጭንቀትን፤ ስጋትን ከምድራችን አጥፋልን። #መጨካከን አቁርልን። አሜን።   በነጋ ጠባ ጥቁር ዜና፤ በየለቱ መርዶ፤ በየማዕልቱ ዕንባ መፈጠርን ተፃሮ በቆመ ክፋ ሃሳብ የአንድ እትብት ልጆች እንዲህ መሆን ያሳዝናል።   #ንጋት ሆይ! የተስፋ #ወጋገን ሆይ! አቤቱ #የሳቅ - ዘመን ሆይ! መቼ #ትመጣላችሁ ????? ማህበረ ሰብአዊነት እንዴት አደራችሁልኝ።    ሥርጉትሻ 13/08/026. #የሚናፍቅስ #ሰላም #ብቻ ።    https://www.bbc.com/amharic/articles/c4gx835q9gwo «በመተከል ዞን ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ» 12 ነሐሴ 2026 የንባብ ጊዜ: 3 ደቂቃ «በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ።   ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ማክሰኞ ነሐሴ 6/ 2018 ዓ. ም. ጠዋት 12 ሰዓት ላይ በዞኑ ዋና ከተማ ግልገል በለስ በሚገኙ ቤተ ክርስቲያናት እና መናኸሪያ ላይ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።   ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የአካባቢው ነዋሪ "ሕይ...

#ዘመነ #ሰማዕትነት በየለቱ #በየባዕቱ። #በዚህ መሰል ሂደት መሬትም --- ታዝናለች። አየሩ --- ያዝናል። ተፈጥሮ --- ያዝናል። ዘመንም --- ያለቅሳል። ፈጣሪም ይከፋል።

  #ዘመነ #ሰማዕትነት በየለቱ #በየባዕቱ ።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   የምህረት፤ የይቅርታ፤ #የይቅርባይነት ልቦና ፈጣሪ ለሁላችንም ይስጠን። አሜን።    #ምዕራፍ ፲፱።   ሰማዕታት በዘመኑ በርካቶች ናቸው። ጥቂቶችን ብቻ ነው ያቀርብኩኝ። ሁሎችም ምንም #ከፖለቲካ ጋር ግንኙነት ዬሌላቸው #ባተሌወች ነበሩ።   ሁሎችም እናት አላቸው። ስለ ኢትዮጵያ እናቶች ይጨንቀኛል። ሴቷ ካረሳሁት ዕጸገነት የምትባል፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሠራተኛ #ሙሽራም የነበረች ነበረች።    ታዳጊ ወጣቱ ወላጆቹን እየሠራ የሚረዳ ነበር። በዚህ ዕድሜው የቤተሰብ #ኃላፊነት የወሰደ ትጉህ ነበር።   እስር ቤት ውስጥም #ሰማዕትነት የተቀበሉ የባንክ ሠራተኛም አሉበት። በአማራ ፖለቲካ ይመስለኛል ታሥረው የነበሩት።   ፈውስ፤ መፍትሄ፤ መዳን፤ ርህርህና፤ ዕውቀት ሁሉም ነገር እንዳልነበረ የሆነበት የሃኪሞች ጉዳይ የኢትዮጵያ የተስፋዋ #ውጋት የሆነ ገጠመኝ ነበር፤ የሁሎችም ሰማዕትነት በአማራ ክልል የተከወነ ነው።    "ህወሃት በፖለቲካ የበላይነት" በሚመራበት የአማራ ክልል ይህን መሰል #ጥቃት የሚጠበቅ ነው።   በሱር ኮንስትራክሽን በማዕከላዊ ጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ 80ሺህ ተፈናቃይ እስከ ስሜን ፓርክ ቃጠሎ ድረስ የተከወኑት አሰቃቂ፤ ሰላም ነሽ ጉዳዮች ባለቤቱን በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም #የተቀየጠ ስለሆነ።    ለነገሩ አቤቱ ህወሃት ናፍቀህናል #ና እባክህ #ናልን መባሉን እያዳመጥን ነው።    የሆነ ሆኖ በሁሉም ሂደት የሰው ልጅ እንዲህ በየለቱ ተስፋውን ማጣቱ እጅግ …… እጅግ ያሳዝናል። ዕድሜው እንዲህ መቀጨቱ። ...

አዲስዬ #የእግዚአብሄር እጅ ያለባት ከተማ ናት። አዲስና #ምሩቅ መንፈስም ናት።

ምስል
  አዲስዬ #የእግዚአብሄር እጅ ያለባት ከተማ ናት። አዲስና #ምሩቅ መንፈስም ናት።   "ጎለመስኩ አረጀሁም፤ ፃድቅ ሲጣል፤ ዘሩም እህል ሲለምን አላዬሁም።" (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፴፯ ቁጥር ፳፭።)   https://www.youtube.com/watch?v=Bjs7wTqjs8E «በአዲስአበባ ጉዳይ አስደንጋጭ ጉድ ተሰማ! | የአዲስአበባ እጣፈንታ ተወሰነ? | ወይ አዲስአበባ! አፋጀቻቸው!| Ethiopia»   #ምዕራፍ ፲፱።   ሊንኩን መለጠፌ የተረጋጋ ውይይት ስለሆነ ነው። ቁጣ የለውም። ብስጭት የለውም። ገረጭራጫ መንፈስ የለውም። የእቴጌ #ጣዩቱ ከተማ መነሻዋ፤ ታዳጊነቷ፤ ወጣትነቷ፤ ጎልማሳነቷ፤ አዛውንትነቷን ገለጣው ይተነትናል ውይይቱ።    ለምን እሷን የመሰለ ከተማ መፍጠር አልተቻለም ሲል ትንተናው ይጠይቃል። ከተፈላጊነቷ #ዝቅ የማድረግ ፕሮጀክት ሊኖር እንደሚችል ኢትዮጵያዊው ጉግል አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገልጠው ነበር። የሸገር ሲቲ እኮ ከዛ ጋር የተያያዘ ይመስለኛል። አዲሱ የአውሮፕላን ማረፊያ ጥንስስም ለዛ ይመስላል። ግን አሁንም ጉምጅቱ ተጧጡፏል።    ግን ኦህዴድ ድሬን፤ ደብረዘይትን፤ ናዝሬትን፤ ጅማን የከፋን፤ ሚዛን ተፈሪንም፤ ኢሊባቡር መቱን፤ ባሌ ጎባን፤ ወለጋ ነቀምትን፤ አርሲ አሰላን፤ ሻሸመኔን ጠቅልሎ ተሰጥቶት ግን የአዲስ አበባ #አቻ ለመፍጠር ምን ተሳነው?።   ስንት ዓመት? ከ30 ዓመት በላይ። ጅማ እማ በሚያሳዝን ሁኔታ እንደ ነበር ሰምቻለሁኝ። ድሬም እንዲሁ። ከእጅ የገቡ የቀድሞ ስንት የክ/ ሃገራት ከተማ ለኦህዴድ ተሰጠው??? ግን ምንም …… በተሠራ ነገር ላይ ብቻ #የእኔን ገነባበት። በዚህ መፈተን ይቻላል።    በሌላ በኩል አይደለም ከአዲ...

#ጸጸትን ስለማስተናገድ።

  #ጸጸትን ስለማስተናገድ።    "የእግዚአብሄር ቃል ሁሉ ትፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፴ ቁጥር ፭)   #ምዕራፍ ፲፱።   የሰው ልጅ በሚያምንበት መስመር መሳተፍ መብት ነው። የሰው ልጅ #በማያምንበት መስመርም ቢሆን ጊዜው // ዘመኑ ካስገደደው መኖርን ለመምራት በሚያደርገው ተጋድሎ ውስጥ ስለመሆኑ አስተውሎ ሊመረምረው ይገባል።   130 ሚሊዮን ህዝብ ከአገሩ ውጭ የት ይሰደድ? ልሰደድ ቢልስ ይችላል ወይ? ይህንን ጽንሰ ሃሳብ በዘመነ ህወሃትም እጽፈው ነበር። የሚቻል ነገር ከገጠመ በህሊና ዳኝነት መወሰን ጥሩ ነው። #በማይቻል ሁኔታ ግን የአንዷን ቀን የለት ጉርስ መሸፈን ጋዳ ሆኖ፤ ተመችቶት በተቀመጠ ድሎተኛ ጫና በራስ ላይ ሌላ ፈተና ማከል አያስፈልግም። ህይወት ጥምልምል ነው። ያ በቂ ነው - ፈተናው።   ስለሆነም ወጣቶች ዕድል፤ ዘመን፤ ሁኔታ የሚፈቅድላችሁን ማድረግ ይገባችኋል። በዘመነ ህወሃት የውጭ የትምህርት ዕድል ያገኜ ወጣት አልሄድም፤ ሥርዓቱን ስለማልወደው አላለም። በዕድሉ ተጠቅሞ ለቤተሰቡም ተስፋ መሆን የቻለው ዕድሉን #ባለማፍሰሱ ነው።   በ6ኛው ይሁን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ መሳተፍ፤ እጩ ሆኖ ለመቅረብ መፍቀድ፤ በድምጽ ሂደቱ ለመሳተፍ በአገኛችሁት ዕድል ሁሉ መሳተፋችሁ ወጣቶች ሆይ! #አይጸጽታችሁ ። በኢትዮጵያ ውስጥ እየኖራችሁ መኖራችሁም እራሱ ፖለቲካ ነውና በሁነታዋ ሁሉ በንቃት መሳተፍ የተገባ ነው። ዕድሉ ከተገኜ።   በሌላ በኩልም በአገራዊ ምክክሩም መሳተፍ መልካም ነገር ነው። በተሳትፎው ውስጥ ትልቁ ቁምነገር በዕድሉ ከክፋ ሃሳብ ጋር አለመገናኘት ግን ይገባል። መሳተፍ ጸጸት #አይደለም ።   ታላቅ ተመክሮ፤ ጥሩ ሰወች ጋ...

አዲስ አበባ #ቅዱስ መንፈስ ናት። ብልህነት ዊዝደም ነው። ብልጥነት ግን ለእኔ እንቅጩን ስናገር #ማጭበርበር ነው።

ምስል
  ብልህነት ዊዝደም ነው። ብልጥነት ግን ለእኔ እንቅጩን ስናገር #ማጭበርበር ነው።   የምርጫ ተርሙስ ከ6ኛው አገራዊ ምርጫ ይጀምራልን???? ሁለት የምርጫ ተርም ወደ ሦስት ማህበረ እንደ ልቡ ካላስደረጉት። የምርጫ ተርሙስ ከሁለት ወደ ሶስት ይሸጋገራልን? ከ7ኛው ምርጫስ ይጀምራልን? በዞግ ፖለቲካ ፕሬዚዳንታዊነት??? በቋንቋ "ፌድራሊዝም" እንደ አሜሪካ ዲሞክራሲ?   "ንጉሥ በፍርድ አገሩን ያጸናል፤ መማለጃ የሚወድ ግን ያፈርሰዋል።" መጽሐፈ ምሳሌ (ተግሳጽ ) (ምዕራፍ ፳፰ ቁጥር ፬)   #በፓርላማ ምርጫ ፕሬዚዳንታዊ???? እንዴት ሊሆን ይችላል?   በቃ ኢትዮጵያ የተፈጠረችው የአንድን ዞግ ፍላጎት፤ ምኞት መሻት ብቻ ልታስፈጽም ነውን? ሌላው ጥያቄዬ ደግሞ መንግሥታዊ አደረጃጀትን ፓርቲያዊ ዲስፕሊን ውስጥ ተዘፈቀን?    ግን ክብረቶቼ እንዴት ናችሁልኝ?    እኔ ሁሉንም ነገር መጀመሪያ ላይ በቅንነት ስለማይ ይህ የፕሬዚዳንታዊ መሻት #በስምንተኛው አገራዊ ምርጫ በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ አቶ ሀ፤ አቶ ለ፤ አቶ መ ሴት አይታሰብም ይወዳደሩ እና ያን ጊዜ ፕሬዚዳንታዊ መሆን ይቻላል የሚል ዕሳቤ ነበረኝ።   እንዲህ በአቋራጭ እንደ አየር ላይ ትምህርት ዶክተሬትነት በፍጹም አላሰብኩም። አንድ እንፍራንዝ ከምትባል ትንሽዬ ከተማ የምርጫ ጣቢያ፤ ወይንም አርሲ ከሚገኝ ዲክሲስ ከሚባል የምርጫ ጣቢያ የተመረጠ አቶ ሀ አቶ ለ አቶ መ የአገር ፕሬዚዳንት ልክ እንደ አሜሪካኖች ዲሞክራት፤ ሪፓብሊካን ወይንም ኢንዲፔንደት ልሆን ብሎ ማሰብ ብዙ የገዘፋ የመንግሥት አደረጃጀት መርሆችን የሚሰባብር፤ የሚያቆሳስል፤ የሚገርፍ መከራ ይሆናል።    ብዙ የገዢው ፓርቲ የብልፄው ዝንባሌው የመ...