ልጥፎች

#ዋ! የዬኔታ ልቅና #ራስ #ዋሸራ! ሆይ! ሆይ!

  #ዋ ! የዬኔታ ልቅና #ራስ #ዋሸራ ! ሆይ! ሆይ!   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   "ዋሸራ (ደብረ ምዕራፍ ዋሸራ ማርያም) በኢትዮጵያ፣ አማራ ክልል ጎንጅ ቆለላ ወረዳ (ምዕራብ ጎጃም) የሚገኝ ታሪካዊና መንፈሳዊ ቦታ ነው። ከአዲስ አበባ 426 ኪሎ ሜትር እና ከባሕር ዳር 82 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ስፍራ፣ በርካታ ሊቃውንት የተገኙበት የቅኔ መገኛ ማዕከል በመባል ይታወቃል።ቁም ነገሮች፡የቅኔ አምባ፡ ከዋሸራ የወጡ የቅኔ ሊቃውንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታላላቅ ገዳማትና አድባራት በማስተማር ቅኔን አስፋፍተዋል።የቅኔ ዩኒቨርሲቲ፡ የቅኔ ጥበብን ለማሳደግ "የቅኔ ዩኒቨርሲቲ" ማዕረግ የተሰጠው ሲሆን፣ ታላላቅ የበዓላት በዓላት ለምሳሌ የአስተርእዮ ማርያም በዓል እጅግ በደማቅ ሁኔታ በቦታው ይከበራል።"   #ብሎት መሆኑን አውቃለሁኝ። በዓለም ውስጥ ላለነው፣ ለኢትዮጵያ የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች። ግን እንዲህ ህሊናን የሚያፈርስ ክስተት ሲኖር ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ ጠርቶ ቤተ - እግዚአብሄራችን ጋሻ፣ ጦሯ፣ ድሮኗ፣ ኒኩለሯ፣ ባሩዷ፣ ትጥቅ እና ስንቋ #ጸሎት ነው። ፆም ነው። ሱባኤ ነው። ስግደት ነው። ምህላ ነው። ልመና ነው።    እግዚአብሄርን የተረገምንበትን ከልቶ ምህረት ይልክ ዘንድ ተንበርክኮ #ድሆ መለመን አያሽላንም። ይህን ማታዊ ዜና እንዲያስታግሰው፣ እንዲያቆረው ለሁሉ ጌታ አማኑኤል በዕንባ መጠየቅ ይገባ ይመስለኛል። አልቦሽነት ነገን፣ ማግሥትን አልቦሽን #ስለሚቀልበው ።   የወል ሱባኤ ጥቅሙ የአንዱ ባይደመጥ ከብዙኃን የእኔ ቢጤ ኃጣን አንድ #ዕዮባዊ አይጠፋም እና የወል ሱባዬ መያዝ የተገባ ይመስለኛል። እኔ ቅዱ...

#ገዳይ ሃሳብ በአካልም ይሁን በመንፈስ #በታኝ ነው።

  #ገዳይ ሃሳብ በአካልም ይሁን በመንፈስ #በታኝ ነው።   "እግዚአብሄር ቃየልን ወንድምህ አቤል ወዴት አለ አለው፤ ቃየልም በልቡ ትዕቢት የወንድሜ የአቤል ጠባቂ ነኝ አለ። አቤል ንጹሕ ሰውን ሆነ ቃየል ግን ደግ ሰው ወንድሙን አቤልን በመግደል ኃጢያተኛ ሆነ።" (መጸሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ም ፳፰ ቁ ፬ - ፭)   #ምዕራፍ ፲፱።   እንዴት አደራችሁ ማህበረ - ቅንነት።    እኔ አቶ ሽመልስ አብዲሳን ኢትዮጵያዊ #ጎልጉል እላቸዋለሁኝ። ግልጽ እና ቀጥተኛ ሃሳባቸውን ማጋራታቸው መልካም ነገር ነው። አይደለም በአገር ደረጃ በቤተሰብ እንኳን ይህን መሰል ግልጽ እና ቀጥተኝነት ጠቃሚ ጉዳይ ነው። ትዕቢታዊ ሁነታቸው ግን ይጎፈንነኛል። መታበይ ወንዝ አያሻግርም፤ ሥልጣንንም አያጸናም።    4ሺ ኢትዮጵውያንን በጋራ አሰባስቦ ያለው አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ረጅም ጊዜ የወሰደበትን ተልዕኮ ለመቋጨት ስምንት በኽረ አጀንዳወችን የያዘ የመወያያ አቅጣጫ አመልካች ሰነዱን ሰሞኑን አስተዋውቋል። የተሳታፊ ቁጥር እየጨመረ ስለመሆኑም እያደየጥኩ ነው። " ኑ በራችን ክፍት ሆኖ ይጠብቃችኋል" የሚል ዕድምታ እንዳለም አንብቤያለሁኝ።   የሆነ ሆኖ ከዚህ ጋር በተያያዘ ብልፄው እንደ ፓርቲ ለምክክር ኮሚሽኑ አቀረበ የተባለው ሰነድ ደግሞ በአቻነት ወጥቷል። ከውስጥ የተገኜ መረጃ ይሉታል ዘመነኛ ተጽዕኖ ፈጣሪወች ወይንም የዩቱብ ባለቤቶች።    እንደምን የሚስጢር በር ለእነሱ ቧ ብሎ እንደሚከፈት፤ ለሌሎቻችን ደግሞ ክርችምችም እንደሚል በይገባኝም። የክት እና የዘወትር፤ የቤት እና የእዳሪ ልጅነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ልሙድ ነው።   የኦሮምያ ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ አገራዊ ምክክሩን ተከትሎ፤...

#የ106 ደቂቃወች የምጥ ግልግል #በኒወርክ።

  #የ106 ደቂቃወች የምጥ ግልግል #በኒወርክ ።   "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱።)   #ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ። ክብረቶቼ የእኔ አዱኛወቼ፤ የአገሬ ልጆች የእቴጌ ድንቡልቡል የልብ ህሊናወች፤ የእግር ኳስ አፍቃሪወች፤ አትኩራታውያን ሁሉ ምሽቱ፤ አዳሩ፤ ረፋዳው እንዴት ይዟችኋል?    ስለ - ተፈጥሯዊነት፤ ስለ - ጥበብ፤ ስለ - ሰው ልጅ ሐሤት የአሰጣጥ ሥርዓትየሚመስጣችሁ ወገኖቼ፤ በማስተዋል የአርቱ ቤተኛ ለመሆን የመስጠት አቅም ያላችሁ ውዶቼ እግር ኳስ ለእኔ 13ኛው #ፕላኔት ነው። ተክለ - ሁነቱን እዩት ማዕድ ነው። ክብ ነው። እቅፍቅፍ ጥግትግት - ውህድህድ - ያለ የዓለም ማህበረሰብን የሚናፍቅ ሐዋርያ፤ ትንቢተኛም።   እግር ኳስ በፍቅር ተፈጥሮ የጰጰሰ፤ በተፈጥሯዊነት ነብይነትን የተጎናጸፈ ልዩ ስጦታ ነው። ግሎባላይዜሽን - ሲታሰብ፤ ደንበር አልቦሽ እኛዊነት ሲታሰብ፤ አብሮነት - ሲታጭ፤ ህብራዊነት - ሲታለም፤ ዕንባ - ሳቅ - ሲቃ - የጋብቻ አጋጣሚ፤ ቤተሰባዊነት፤ ማህበራዊነት፤ ታዳሚነት - አድማጭነት ሲታለሙ ፌክ ያልሆነ የውስጥ ለውስጥ አገናኝ ነው። ድልድይ ነው የላቀው የእግር ኳስ ቅኔዊ - ጥበቡ፤ ዘለግ ሲል ዊዝደሙ።   በኳስ ውስጥ መሰጠትን፤ ማተኮርን፤ ማስተዋልን፤ የጋራ እና የግል ኃላፊነትን፤ ፖስተኝነትን፤ ቅብዓን፤ ህግን፤ ጥሪን፤ የድንጋጌ አፈፃጸም ሂደትን፤ የትውልድ አገነባብ ሜቶሎጂን፤ ትውልዳዊ ድርሻን፤ ታሪክን - ትውፊትን - አደራን - ስልጣኔን - መኖርን - መታመንን - ሞራልን - ዲስፕሊንን - ድንበር አልቦሽነትን - እድገትን - ስኬትን - መደመጥን - ቅንነትን - ማግስ...