ልጥፎች

#የ106 ደቂቃወች የምጥ ግልግል #በኒወርክ።

  #የ106 ደቂቃወች የምጥ ግልግል #በኒወርክ ።   "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱።)   #ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ። ክብረቶቼ የእኔ አዱኛወቼ፤ የአገሬ ልጆች የእቴጌ ድንቡልቡል የልብ ህሊናወች፤ የእግር ኳስ አፍቃሪወች፤ አትኩራታውያን ሁሉ ምሽቱ፤ አዳሩ፤ ረፋዳው እንዴት ይዟችኋል?    ስለ - ተፈጥሯዊነት፤ ስለ - ጥበብ፤ ስለ - ሰው ልጅ ሐሤት የአሰጣጥ ሥርዓትየሚመስጣችሁ ወገኖቼ፤ በማስተዋል የአርቱ ቤተኛ ለመሆን የመስጠት አቅም ያላችሁ ውዶቼ እግር ኳስ ለእኔ 13ኛው #ፕላኔት ነው። ተክለ - ሁነቱን እዩት ማዕድ ነው። ክብ ነው። እቅፍቅፍ ጥግትግት - ውህድህድ - ያለ የዓለም ማህበረሰብን የሚናፍቅ ሐዋርያ፤ ትንቢተኛም።   እግር ኳስ በፍቅር ተፈጥሮ የጰጰሰ፤ በተፈጥሯዊነት ነብይነትን የተጎናጸፈ ልዩ ስጦታ ነው። ግሎባላይዜሽን - ሲታሰብ፤ ደንበር አልቦሽ እኛዊነት ሲታሰብ፤ አብሮነት - ሲታጭ፤ ህብራዊነት - ሲታለም፤ ዕንባ - ሳቅ - ሲቃ - የጋብቻ አጋጣሚ፤ ቤተሰባዊነት፤ ማህበራዊነት፤ ታዳሚነት - አድማጭነት ሲታለሙ ፌክ ያልሆነ የውስጥ ለውስጥ አገናኝ ነው። ድልድይ ነው የላቀው የእግር ኳስ ቅኔዊ - ጥበቡ፤ ዘለግ ሲል ዊዝደሙ።   በኳስ ውስጥ መሰጠትን፤ ማተኮርን፤ ማስተዋልን፤ የጋራ እና የግል ኃላፊነትን፤ ፖስተኝነትን፤ ቅብዓን፤ ህግን፤ ጥሪን፤ የድንጋጌ አፈፃጸም ሂደትን፤ የትውልድ አገነባብ ሜቶሎጂን፤ ትውልዳዊ ድርሻን፤ ታሪክን - ትውፊትን - አደራን - ስልጣኔን - መኖርን - መታመንን - ሞራልን - ዲስፕሊንን - ድንበር አልቦሽነትን - እድገትን - ስኬትን - መደመጥን - ቅንነትን - ማግስ...

10 ጎል ከመረብ ጋር #የተጋባበት የደረጃ ጨዋታ።

  10 ጎል ከመረብ ጋር #የተጋባበት የደረጃ ጨዋታ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   የመጀመሪያው ግማሽ ጨዋታ በእንግሊዝ 4 ፈረንሳይ ምንም በሆነ ውጤት ፈረንሳዮች ምን ነካቸው የሚል የቤት ሥራ ለተመልካች #ሸልመው ግራ ቀኙ ተጫዋቾች ወደ እረፍት አመሩ።   ከእረፍት መልስ ፈረንሳዮች ተጠናክረው ገብተው ሦስት ጎል አስገቡ። እንግሊዞች #የቅጣት ምት አገኙ እና ከ4 ወደ 5 ከፍ አሉ። ፈረንሳዮች የማጥቃት እንቅስቃሴያቸውን ቀጥለው አንድ በመጨመር ወደ 4 አደጉ። ይህን ጊዜ ጨዋታው ሊራዘም ይችላል የሚል ተስፋ ቢጤም ነበር። ነገር ግን እንግሊዞች 1 አክለው 6 እንዳሉ ጨዋታው #ተጠናቀቀ ።   በደረጃ ጨዋታ ይህን ያህል ጎል በጣም ብዙ ነው። የእንግሊዞች በአርጀንቲና መሸነፍ፣ የፈረንሳይ ደረጃውን ስፔኖች መውሰድ #የመድከም ፣ #የመዛል ሊሆን ይችላል።   በዚህ ጨዋታ #ማፔ ሁለት ጎል አስገብቷል። ቢጠነክር ዛሬ ተጨማሪ ጎሎችንም መጨመር ይችል ነበር። #የወርቅ ጫማዋ ብትቀናው ምኞቴ ነው።   #የወርቅ ቀለበትም ተዘጋጅቷል አሉ። እኔ አይደለም ያልኩት። ቢቢሲ ነው። ነገ ለፍፃሜ አርጀንቲና እና ስፔን ይጋጠማሉ። የነገ ሰው ይበለን። አሜን። ጨዋታው በመደበኛ ጊዜ ነው የተጠናቀቀው። #ደክሟቸዋል #ይረፋ ። የእንግሊዞች የደረጃ ሽልማት እዬተሰጠ ነው። #ሦስተኛ ደረጃ ይዘው።   ጨዋታውን ይህ ዓይነት ነበር ለማለት አልቻልኩም። ደንብ እና ህግ ስለሆነ ብቻ የከወኑት ነው የሚመስለው። #የማይቀርበት ስለሆነ።   ሥርጉተ©ሥላሴ። Sergute©Selassie. 19/07/026

ለኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር #ህሊናው ሊሆን የሚገባው #ኦርጋኒክ ሰብዕና ያለው አቶ ኦባንግ ሜቶ ነበር።

  ለኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር #ህሊናው ሊሆን የሚገባው #ኦርጋኒክ ሰብዕና ያለው አቶ ኦባንግ ሜቶ ነበር።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   ኦባንግሻ #ለፈላስፊት ኢትዮጵያ #ኦርጋኒክ ማንነት፣ #ልኩ ኦርጋኒክ ሰብዕናው የሚመጥን ነበር። ሁልጊዜ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት እነቃለሁ። እንደ ነቃሁ የሚያስቀጥል ሃሳብ አዕምሮዬ ካመነጨ ይህንኑ አዲስ ሃሳብ እያጠናሁ ይነጋል።   ዛሬ ሌሊት ኦባንግሻን አሰብኩት #ዘለግ አድርጌ። ሁልጊዜም አስብለታለሁኝ። ምክክሩ ከወደ ጋንቤላ አዲስ "ምክክር" የሚባል ቤቢ አግኝቷል። ስሙም " #ምክክር " ነው። ይደግልን። አሜን።    ከንቲባ ወሮ አዳነች አበቤ የአራስ ወጉን ሲያደርሱ አይቻለሁ። ይህ መልካም ነገር ነው። መልካም ነገርን የማነወር ሰብዕና የለኝም። እንዲለመልም መመኜት እንጂ።    ለነገሩ አንዷ አክስቴ #መልካም ሰው፣ ሌላዋ #ደግ ሰው ይሉኝ ነበር። ጸጥ ያልኩ፣ ያለኝን ሁሉ የምሰጥ የልጅነት ጊዜ ነበረኝ። አዲስ ለተገኜው የጋንቤላው ልዩ ህፃን የተደረገው እንክብካቤ #ማለፊያ ነው። የዓለምን የሚዲያ አውታር ያጨናነቀው የስፔኑ ያማል ታናሽ ወንድም ነው። ብርቅ ድንቅ ደጋፊነቱ ልዩ አትኩሮት ስቧል። ሁለቱንም ዓለም አደነቀ።   ልዩ የሰብአዊነት አቅም የኢትዮጵያ #አንከር አቶ ኦባንግ ሜቶስ? ለአዲሱ ቤቢ ክብር፣ እንክብካቤ ጥሩ ነገር ነው። የትናንቱ የኢትዮጵያ ባለውለታ መኖሩን እንኳን ለማወቅ አለመቻላችን ያሳስባል።   ኦባንግሻን የበላ ጅብ አልጮኽ አለ። አይደለም ኢትዮጵያ #አህጉራችን ሊወክል የሚችል #አብነታዊ ሰብዕና ያለው። አምኖ፣ አገሩ ገብቶ፣ ንጹህ #መታመን ከድቶት እንዲህ ዝግትግት ባለ መረጃ አልቦ...

ግን የት ደረሰ?

  "ኑ አገራችሁን ግቡ።" ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ። "ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን።" ግን የት ደረሰ?   "ቀን የሚያመጣውን ምን እንደሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፯ ቁጥር ፩)   #ምዕራፍ ፲፱።   "ኑ አገራችሁን ግቡ። #ስንኖር ኢትዮጵያዊ፤ #ስንሞት ኢትዮጵያ" በምልሰት የሚጠይቅ አገላለጽ ነው። ብለህ ነበር፤ ያልከው ሆኖን፤ ምን አሳካህ፤ ምንስ አጎደልክ የሚል የህሊና ሙግት ጋር እራስን #ያገጣጥማል ።   ስንኙ - ያማልላል። ውስጥን - ይደላል። ግን ገቢር ላይ ተፈትኖ የወደቀ ጽንሰ ሐሳብ ነው። በውስጡ የሌለ ጭብጥ ዕውንነቱ ከመፈጠሩ በፊት #ክስመቱን ስለሚያውጅ።   ቀድሞ ነገር ኢትዮጵያ #የማን ናት? ኢትዮጵያን #የሚያዝባትስ ማነው? ለኢትዮጵያዊነት ዜግነት ሰጩ፤ #ነሹስ ማን ነው? #ኢትዮጵያዊነት በገብያ ንግድስ ይተዳደራልን?   የገዘፋ ጥያቄወችን በዚህ ዙሪያ በብዙ ማንሳት ይቻላል። መላሽ ካገኙ። እንደ እኔ እምነት ኢትዮጵያዊነት በገብያ ህግ ሊተደደር አይችልም። ኢትዮጵያም የኢትዮጵውያን ናት። ኢትዮጵያን የሚያዛት፤ መታዘዝ ካለባት ህዝቧ ብቻ እንጂ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ወይንም፤ አንድ ዞግ ሊሆን አይችልም።    ለኢትዮጵያ ዜግነት ሰጩም ነሹም፤ ውጡ ግቡም ብሎ የመበየን የአንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪ ሥልጣን በፍጹም አይደለም። ሊሆንም አይችልም።    በማንነት ጉዳይ የሚሰጠው ብይን የግንዛቤ እጥረት ወይንም አቃሎ የማየት፤ ወይንም የውስጥ ቀውስን ለማስታገስ ካልሆነ በስተቀር የማንነት ጉዳይ አገር፤ አህጉር፤ ሉላዊ በሆነ መንፈስ ስናዬው ለሰው ልጅ የተሰጠው የነፃነት መንበር፣ ላዕላይ የሆነ የክብሩ መገለጫ፣...