እ። ምን ልል ነበር አያ? ኧረ አወን ልበለው። "የታስራችሁ #የተሰውታችሁ እንይ" ምኞት። "በሞኝ ክንድ ዘንዶ ይለካበታል።"
እ። ምን ልል ነበር አያ? ኧረ አወን ልበለው። "የታስራችሁ #የተሰውታችሁ እንይ" ምኞት። "በሞኝ ክንድ ዘንዶ ይለካበታል።" "እግዚአብሄር እዮብን ልቡ ከኃጢያት፤ እንደነፃች ባየው ጊዜ፤ በብዙ ክብር ተቀበለው።" (መቃብያን ም ፰ ቁ ፪) ምዕራፍ ፲፱። ጤና ይስጥልኝ ክብርት ኢትዮጵያ እናት አገሬ፤ ጤና ይስጥልኝ እምዬ ሲዊዝሻ ርህርህተ - አገር፤ ጤና ይስጥልኝ ኮሽ አይሏ ደጓ፤ እየኖርኩብሽ እማልጠግብሽ ቢንተርቱር ከተማ (Winti) ጤና ይስጥልኝ አዱኛወቼ ቤተ - ሥርጉትሻ እንዴት አድራችሁ? እንደምንስ አረፈዳችሁልኝ? "በአገራዊ" የምክክር ኮሜሽን ቅሬታ ያላቸው ተቋማት፤ የተከፋ ተሳታፊወች "ጉባኤውን ረግጣችሁ ውጡ፤ ምን ትጠብቃላችሁ፤ ሞትም እስራትም ቢመጣ ተጋፈጡት፤ የሚል ጨካኝ ሃሳብ አዳመጥኩኝ። "ያልተነካ ግልግል ያውቃል" እንዳልል ሃሳብ አራማጁ በዘመነ - ህወሃት፤ በዘመነ - ብልፄው ታስሮ የተንገላታ፤ የተሰደደም ነው። በተለይ የአማራ ተወያዮች "በነውረኛ ቃል ዘለፋ፤ በክፋ ዓይን መገረፍ፤ በተሳትፎ ላይ ዕድል መነፈግ፤ ግልምጫ፤ ማሳደድ ተካሂዶብናል" ብለው ቅሬታቸውን ለምክክር ኮሚሽኑ አቅርበው አድማጭ ማጣታቸው ነው "ጥለው ይውጡ ምን ይሠራሉ? ይውጡ እና የሚመጣውን ይጋፈጡ" የሚል ሃሳብ ተሰጣቸው። ወጣትነት ትዕግሥትን የሚፈትን ስለሚሆን ይሆናል። ወጥተው የት ይሂዱ እነኝህ ቅሬታ አቅራቢወች? ሰማዩም ምድሩም እኮ #በብልፄው መንግሥት ሥር ነው። ምንድን ነው ወጥተው የሚያተርፋት? ማንስ አላቸው???? መቼም ከ፵ ሚሊዮን ህዝብ በላይ ስደት ሊያስብ ይቻል ይሆን ሎጅኩ? ልሰደድ ቢልስ ይችላልን??? የአማራ ተሳታፊወች ጉባ...