ልጥፎች

የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነትን በቀዝዝቃ ጦርነት እናስረክብ ነው፤ የኮሚሽኑ ልዩ ኮሚቴ ፍላጎት።

ምስል
  የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነትን በቀዝዝቃ ጦርነት እናስረክብ ነው፤ የኮሚሽኑ ልዩ ኮሚቴ ፍላጎት።   "ከንቱ፤ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።"       ጠቅላላ የኢትዮጵያ ተቋማት፤ አህጉራዊ ይሁን ሉላዊ የሥልጣን ቦታወች በገፍ ለማን እየታደለ እንዳለ ይታወቃል።    ይህም ይሁን ተብሎ ኢትዮጵያዊነት መንበረ - እርካቡን፤ ማዕዱን አስረክቡን "አንገት የተሰራው አዙሮ ለማየት ነው" ብሂልን ይድጠዋል።    በዚህ ስሌት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተር በኦሮምያ አስተዳደር #ሥር ይወድቃል። ማናቸውም ብሄራዊ፤ አህጉራዊ፤ ዓለም ዓቀፋዊ ጉባኤወችም በኦሮምያ አስተዳደር ስር ይወድቃሉ። የተንጠራራ ፍላጎት ነው ያለው።    መግራትም፤ መቆንጠጥም አልተቻለም። ብልፄው እራሱን ፈቅዶ #እየናደ ይገኛል። ውስጥን በዝምታ ማሸፈት ጠንቁ ለራሱ ነው ለብልፄው አገራዊ ነኝ እያለ ሲደሰኩር ባጅቶ ዞጋዊ መሆኑን እራሱ እየመሰከረ ነው። ዲስፕሊኑ ሲጣስ ጸጥ ረጭ ብሏል።   አንድ የፖለቲካ ድርጅት ዲስፕሊኑን መቆጣጠር ከተሳነው አናርኪዝም ይነግሳል። አናርኪዝም #አንጃ ይፈጥራ። አንጃው ፍርሻ ነው። በኢሠፓ ውስጥ አንጃ ተፈጥሮ ሁለት ዓመት አልቆየም ኢሠፓ መራራ ስንብት ያደረገው። ወፋ ጥሩ አይደለም።    ኦሮምያ አስተዳደር መንፈሱ ኦነግ #ወረስ ነው። ኦነግ ደግሞ ህልሙም ፍላጎቱም ከኢትዮጵያ #መነጠል ነው። ይህን ለማስፈጸም ነው "አገራዊ" በሚል የተቋቋመው ኮሚሽን እያስፈጸመ የሚገኘው።   " #ዋስትና " ከበሪንግ ነው። ወይንም ቅርፊት። አገር ተሰጥቶህ፤ ኖቤል ተሸልመህበት፤ ብሪክስ ላይ ቤተኛ ሆነህ ዋስትና ትጠይቃለህን???   ዋስትና በአንድ ሉዓላዊ መንግሥት ...

#አድሎ እና #አግላይነት ይቁም! "ከልጅልጅ ቢለዩ ዓመትም አይቆዩ።" ኮሚሽኑ የክት እና የእዳሪ ልጅ አለው። #የቀዝቃዛው ጦርነት ሂደት ቀጥሏል።

ምስል
  #አድሎ እና #አግላይነት ይቁም! "ከልጅልጅ ቢለዩ ዓመትም አይቆዩ።" ኮሚሽኑ የክት እና የእዳሪ ልጅ አለው። #የቀዝቃዛው ጦርነት ሂደት ቀጥሏል።   "ከክፋ ሸሽ፤ መልካሙን አድርግ፤ ለዘላዕለም ትኖራለህ።" (መዝሙር ፴፮ ቁጥር ፳፯)       ለምክክር ኮሚሽኑ የቤት ልጅ አቆላማጭ፤ አባባይ ልዩ ኮሚቴ አቋቋመመ።   የማይገባኝ የማህበረ ኦነግ ቤተኞች ኢትዮጵያዊነትን የሚያገሉበት፣ እነሱን ከኢትዮጵያዊነት መንፈስ አውጥተው የመንፈስ ውጊያ በየዘመኑ የሚያደርጉበት፣ እኛን ገፍተው ዶክትሬናቸው እኔ - እኔ - እኔ - የእኔ - የእኔ - የሚሉበት ጉዳይ ነው። እኛ እኮ በውስጣቸው ፈጽመን የለንም። ኧረ እኛ አማራነት አለ በዘር ሐረጋችን ሌሎችን ወገኖቻችን ቢያንስ የእኛ የማይሉበት ምክንያት አይገባኝም።   #የሆነ ሆኖ ………   "በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ኮሚሽኑን የሚያግዝ አዲስ ኮሚቴ ተዋቀረ " ሪፖርተር።" ይህ ጉዳይ በቅጡ ምላሽ ካላገኜ ከፋኝ ላሉት ታጣቂወች ንጥረ አመክንዮ ይሆናል። አቅማቸውን ይጨምራል። ተስፋቸውን #ያደረጃል ። የተበተነ መንፈስንም ይሰበስባል። በተለይ ሳይለንት ማጆሪቲውን የማቅረብ ሁነት ይፈጥራል።    አሰላ የአርሲ ፎለቄ ዋና ከተማ፤ በደምብ ነው የማውቃት። ጅማ ተወዳጁ የከፋ ክ/ አገር ዋና ከተማ፤ መቱ የደጋጎቹ የኢሊባቡር ዋና ከተማ፤ ነቀመት ተናፋቂው የወለጋ ዋና ከተማ፤ ድሬ እናታዊ የሁለመና ደማቅ ከተማ፤ ደብረዘይት ውዷ እታጌዋ ከተማ፤ ሻሸመኔ የህብራዊነት አብነት ከተማ፤   ናዝሬት ብቋዋ የደህንነታችን ዋስትና ከተማን አንድም ሳቢነት፤ አጓጊነት ሳያክል ጠቅልሎ የያዘው የአቶ አባዱላው #ኦህዴድ ፤ በጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ ...

#ሽኝት ሆድ ያረባብሻል። ይገባልም።

ምስል
  #ሽኝት ሆድ ያረባብሻል። ይገባልም።   ገዳይዚም ተመስጥሮ ሳይሆን ተገልጦ ነው የተጀመረው። መሪወቹ ነግረውናል እኮ። ስለዚህም ከገዳይዝም ከተፈጥሮው የሚመነጩ አስደንጋጭ ክስተቶች የግድ ይሆናሉ።    "እኔ ሰምቻለሁ፤ ልቤም ደነገጠብኝ፤ ከድምጹ የተነሳ ከንፈሮቼ ተንቀጠቀጡ፤ መንቀጥቀጥ ወደ አጥንቶቼ ገባ በስፍራዬ ሁኜ ተናወጥሁ፤ በሚያስጨንቁን ህዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ፤ የመከራን ቀን ዝም ብዬ እጠብቃለሁኝ።" (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፮።)         መነሻዬ ከዋዜማ ራዲዮ አቶ ዳንኤል በቀለ ሼር ያደረጉት ቁምነገር ነው።   #ሽኝት ።   የፈለገ ነገር ይደርደር፤ የፈለገ ነገር ይቀመር፤ የፈለገ ነገር ይሽሞንሞን፤ የፈለገ ነገር ግጥግጥ ላይ ይሁን የአዲስ አበባ ሁነት እንዲህ በጎሼ፤ በአጎረፈ፤ በአጎፈረ ሁኔታ እልል ተብሎ አሸኛኜቱ ሊጸድቅ አይገባም። አንበሳው አብዲሳ አጋ፤ አርበኛ አብርኃም ደቦጭ፤ አርበኛ ሞገስ አስጎደም፤ አርበኛ ዘርዓይ ደረስ፤ ሰማዕቱ ብጹውወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ "ኃይለማርያም ማሞ የጦሩ ገበሬ፤ ፈረሱን እንደ ሰው አስታጠቀው ሱሪ" እንዲህ በለብ ለብ፤ በግብር ይውጣ ሁነቱ ስክነት አንሶት ብይን ሊሰጥበት አይገባም።    በባዶ እግር ቤቱን ትዳሩን ትቶ፤ ሞፈር ተፈቶ የፈሰሰው ደም እና አጥንት፤ ሰማዕትነት አጥንት ወጥቶ ሊጠቀጠቅ አይገባም።   ይቺ አገር የኩባ፤ የራሽያ፤ የየመን፤ የአርመኖች መንፈስ የተገበረላት የዘጠኙ ቅዱሳን የመንፈስ ማረፊያ፤ የነብዬ መሐመድ የነብይነት ልክ የተገለጠባት ጠይም ዕንቁ ናት።   በአንድ ዞግ ባህል እና ትውፊት፤ ፍላጎት እና ግብ ልትመራ አይገባም። ህብራዊ - ሥናዊ፤ ቅባዕዊ ጸጋዋ ይፈገፈጋ...