እናትም አባትም ሆነው ላሳደጉ አባት አቶ ይርጋለም ይህ #ጥቁር ዜና #ማት ነው።
እናትም አባትም ሆነው ላሳደጉ አባት አቶ ይርጋለም ይህ #ጥቁር ዜና #ማት ነው። "የእግዚአብሄር ቸርነቱ ብዙ ነው እያልክ፤ በኃጢያት ላይ ኃጢያት አትሥራ።" (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፭) #ምዕራፍ ፲፱። #የተባጀበት የወል አስጨናቂ የሰርክ መርዶ። የሞዴል ሩት ይርጋለም እህት (ወ/ሮ ወት) ቅዱሳን ይርጋለም በሥጋ መለዬትን ዘሃበሻ ላይ ዜናውን ሰማሁኝ። የሁለቱ እህታማቾች #እናታቸውም ፤ #አባታቸውም አቶ ይርጋለም እንደምን ሆነው ይሆን? ልጃቸው ሞዴል ሩት ቃለ- ምልልስ ስታደርግ ዕድምታውን የተረዳሁት ልጆቻቸውን እያሳደጉ ፈቅደው #በምናኔ የኖሩ፤ በሥጋ ለተለዮዋቸው የትዳር አጋራቸው ፍጹም ታማኝ፤ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት የሚሰማቸው ልዩ አባት መሆናቸውን ተረድቼ ነበር። በጣም ቁጥብ። እንደ እነዚህ ዓይነት ተብዕቶች ቁጥብ ናቸው። በዘመናት መሃል ነው የሚገኙት። ይህን መሰል ሰብዕና #የተለመደ አይደለም። ትዳር በህይወት እያለ የክት እና የዘወትር የሚያሻቸው ባሉበት ዓለም፤ ትዳር በሥጋ ሲለይ ለዛውም በወጣትነት በዚህን ያህል ጽናት ዕድሜ ሙሉ #በተዕቅቦ መኖር መመረቅ ነው። እንዲህ እራሳቸውን ሰጥተው፤ መኖራቸውን ለፍጹም ታማኝነት እና ለባለቤታቸው አደራ ጠባቂ በመሆን ያሳደጓት ልጃቸው ስትታፈን፤ #ስትታገት ጭንቁን እንሰበው። ለወላጅ ምጥ ነው። የተባለውን ገንዘብ ማቅረብ ስላልቻሉ ይመስለኛል እንሆ እንደዛ በብቸኝነት ያሳደጓትን ልጃቸውን ያጡት። እግዚአብሄር #ያጽነወት ። አሜን። ብርታቱን ይስጠወት። አሜን። ለማን ብለው በዓለም እየኖሩ መነኑ? ለልጆቸወት አይደለምን? አዝናለሁኝ። ሞዴል ሩት ይርጋለም ይህን መሰል ሃዘን...