ልጥፎች

#ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። #ፍቅር ሲያልቅም ትዕግሥት ይሰደዳል።

ምስል
  #ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። #ፍቅር ሲያልቅም ትዕግሥት ይሰደዳል።   "ዳዊትም ሰው ከንቱን ይመስላል፤ ዘመኑም እን ጥላ ያልፋል፤ እያለ ስለእሱ ተናገረ።" (መጽሐፈ መቃብያን ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፳፫)   #ምዕራፍ ፲፱።   ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል፤ ፍቅር ሲያልቅም ትዕግሥት ይሰደዳል። በህወሃት መሸኛ ዘመን እጠቀምበት የነበረ አገላለጽ ነው። የሆነ ሆኖ አብን የሚሊዮኖች ድምጽ ሆኖ ወጥቶ፤ ያን ኃላፊነት እና ግዴታውን የተወጣበት መንገድ ግን ተስፋ ሰጪ አልነበረም። ሥልጣንን በሚመለከት አንድ የፖለቲካ ድርጅት የሚታገልበት በኽረ ጉዳይ ስለሆነ ለጋሱ ብልፄ ያቀረበለትን ገጸበረከት ይሁንታ ሰጥቶ መቀበሉ ለእኔ የሚጎረብጥ አልነበረም።    ግን መነሻውን ከመድረሻው ለማዋህድ የተከተለው መስመር ግን ለአማራ ይሁን ለኢትዮጵያኒዝም የተስፋ ሂደት #እክል ነበር። ለብልፄ ብሎ አላስፈላጊ ቅራኔ ሁሉ ይገባ ነበር። ሁልጊዜ ከህውሃት ("ትህነግ") ጋር የነበረው አቲካራ አላስፈላጊ ነበር።    አንድም የአማራ ጥያቄን የማስመለስ አቅምም አልነበረውም። በሌላ በኩል እሱ ያመነበትን መንገድ የሚከተሉ አማራወችን የማግኜት ዕድሉም ስስ ነበር። ስለሆነም ብልፄው የአማራ ህዝብን አራጦ ለመግዛት ዕድሉን አብን የማመቻቸት ዕድል ለብልፄ ማጉረስ አልቻለም። የተወሰኑ የአብን አመራሮች ህይወትን የማሻሻል ነገር እንደ ትርፍ ካየው ይሁንለት።    የሆነ ሆኖ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ለጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ #የበኽር ልጃቸው ነው። ለትውልድ እንዲሆን አድርገው በሚገባ አደራጅተውታል። እኔም እከታተላቸው የነበረው ከዛ አንፃር ነበር። ልዩ ጊዜ ያሳለፋበት በኢትዮጵያኒዝም መንፈስም ያ የማይገኝ ጊዜ ይመስለኛ...

"ላም እረኛ ቢቆጣ ምሳው ራቱ ይሆናል።"

ምስል
  "ላም እረኛ ቢቆጣ ምሳው ራቱ ይሆናል።"   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       አንድ ቀን ለቀረው የምክክር ኮሚሽን ጉባኤ የትኛውም ተቋም፤ የትኛውም ድርጅት፤ የትኛውም ቡድን የምክክር ኮሚሽኑን ስብሰባ #ጥሎ ቢወጣ የሚያመጣው #ለውጥ ምንም የለም።   ይልቁንም በራስ ላይ ድርብ #ሰንሰለት ከማምጣት በስተቀር እርምጃው አትራፊ አይደለም።   ከተገኙ ላይቀር #በንቃት #መሳተፍ ፤ የማይመቹ ጉዳዮችን መሞገት፤ ቅሬታን በተደራጀ ሁኔታ መግለጽ።    የራስ ደህንነትን መጠበቅ። ከትርፍ ንግግር መቆጠብ ይገባል።   በተረፈ #በተጠናቀቀ ሁኔታ ላይ #ጥሎ መውጣት አትራፊ ውሳኔ አይደለም። ከራስ ጉዳት በስተቀር #ለብፄ #የሚያጎድልበት ነገር #አንዳችም የለም።    ውዶቹ ደህና እደሩልኝ። አሜን። ሥርጉትሻ 18/08/026. ውብ የእንቅልፍ ጊዜ እመኛለሁኝ። See less

"ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኽ።" "ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ወጭት ጥዶ ማልቀስ።"

ምስል
  "ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኽ።" "ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ወጭት ጥዶ ማልቀስ።"   "አገራዊ" ምክክር ኮሚሽኑን ሳስብ ሟቹ ተስፋዬ ገብረአብ ታሪክን እንዳይደግመው እሰጋለሁኝ። የሆነ #ልብወለድ ታሪክ በአዲስ እንደ ቡርቃ ዝምታ ኮሚሽኑ ይፃፍ ይሆን እላለሁኝ። ኢትዮጵያን #ተቀላች ፣ #ተጠማኝ ፣ #ጥገኛ ፣ #ምርኮኛ የሚያደርግ የታሪክ ዝገት በራስ አገር ልጅ እንዳይፈጠር ያሰጋኛል። አዲስ አበባ "ክልል ትሁን፣ አዲስ አበባ ራስ ገዝ" ትሁን ከውድድር ውጪ የሆነበት ሁኔታን ከውስጤ ሳስበው።)     #ምዕራፍ ፲፱።   1) #የአብን እና የብልፄው ፍቺ በአገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአቅም ኩነት ላይ። 2) " #የአገራዊ " ምክክር ኮሚሽን አብን ስላቀረበው ቅሬታ የሰጠው ማስተባበያ።   3) " #የአገራዊ " ምክክር ኮሚሽኑ የመብት ልክን ያጋለጠው የአቶ ያሬድ ኃ/ማርያም መረጃ (የህግ ባለሙያ እና የሰባዕዊ መብት ተሟጋች።) BBC የኮሚሽኑን ማስተባበያውን ይዞ ወጥቷል፣ የአቶ ያሬድን መረጃ እና የአብን #ደፋር መግለጫ ከፌስቡካቸው ያገኜሁት ነው።   "ልብህን በምግባር አቅና፣ መከራውንም ታገስ፣ አትጠራጠር በመከራውም ብትጠራጠር አትጠራጠር።" (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፪ ቀጥር ፩)   አቅምን መጥኖ ማስተዳደር ይገባል። የኦሮሞ ብልጽግና ፍላጎቶን በግልጽ ሲያሳውቅ ነው የኖረው። ያን አድምጦ አቅምን በቅጡ መያዝ፣ የአቅም መግቦቱንም ማመጣጠን ይጠበቅ ነበር።   ሌላው ወሳኝ ጉዳይ ለመደገፍ ይሁን ለመቃወም እንዲሁም እንደ እኔ #ለመሞገት የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ አጥንቶ መነሳት ይገባል። ዴሞግራፊን እኔ #አሉታዊ እና #አወንታዊ ብዬ በሁ...