ልጥፎች

"ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኽ።" "ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ወጭት ጥዶ ማልቀስ።"

ምስል
  "ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኽ።" "ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ወጭት ጥዶ ማልቀስ።"   "አገራዊ" ምክክር ኮሚሽኑን ሳስብ ሟቹ ተስፋዬ ገብረአብ ታሪክን እንዳይደግመው እሰጋለሁኝ። የሆነ #ልብወለድ ታሪክ በአዲስ እንደ ቡርቃ ዝምታ ኮሚሽኑ ይፃፍ ይሆን እላለሁኝ። ኢትዮጵያን #ተቀላች ፣ #ተጠማኝ ፣ #ጥገኛ ፣ #ምርኮኛ የሚያደርግ የታሪክ ዝገት በራስ አገር ልጅ እንዳይፈጠር ያሰጋኛል። አዲስ አበባ "ክልል ትሁን፣ አዲስ አበባ ራስ ገዝ" ትሁን ከውድድር ውጪ የሆነበት ሁኔታን ከውስጤ ሳስበው።)     #ምዕራፍ ፲፱።   1) #የአብን እና የብልፄው ፍቺ በአገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአቅም ኩነት ላይ። 2) " #የአገራዊ " ምክክር ኮሚሽን አብን ስላቀረበው ቅሬታ የሰጠው ማስተባበያ።   3) " #የአገራዊ " ምክክር ኮሚሽኑ የመብት ልክን ያጋለጠው የአቶ ያሬድ ኃ/ማርያም መረጃ (የህግ ባለሙያ እና የሰባዕዊ መብት ተሟጋች።) BBC የኮሚሽኑን ማስተባበያውን ይዞ ወጥቷል፣ የአቶ ያሬድን መረጃ እና የአብን #ደፋር መግለጫ ከፌስቡካቸው ያገኜሁት ነው።   "ልብህን በምግባር አቅና፣ መከራውንም ታገስ፣ አትጠራጠር በመከራውም ብትጠራጠር አትጠራጠር።" (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፪ ቀጥር ፩)   አቅምን መጥኖ ማስተዳደር ይገባል። የኦሮሞ ብልጽግና ፍላጎቶን በግልጽ ሲያሳውቅ ነው የኖረው። ያን አድምጦ አቅምን በቅጡ መያዝ፣ የአቅም መግቦቱንም ማመጣጠን ይጠበቅ ነበር።   ሌላው ወሳኝ ጉዳይ ለመደገፍ ይሁን ለመቃወም እንዲሁም እንደ እኔ #ለመሞገት የዘመኑን የፖለቲካ ባህሬ አጥንቶ መነሳት ይገባል። ዴሞግራፊን እኔ #አሉታዊ እና #አወንታዊ ብዬ በሁ...

እኔ ሥርጉተ©ሥላሴ ብልፄውን ስለምሞግት የደፂን ህወሃት ልደግፍ #አልችልም። ፈፅሞ! መቼውንም! ለምንግዜም!

  እኔ ሥርጉተ©ሥላሴ ብልፄውን ስለምሞግት የደፂን ህወሃት ልደግፍ #አልችልም ። ፈፅሞ! መቼውንም! ለምንግዜም!   "እግዚአብሄርን መፍራት ክብር ነው፤ የሚያስመካ ተድላም፤ ደስታም ነው፤ ተድላ ደስታ ይሰጣል፤ ደስም ያሰኛል፤ በሕይወት የሚኖሩበትን ዘመን ያበዛል።"   #ምዕራፍ ፲፱።   #ጠብታ ።   ህወሃት የሚለው የዞግ የፖለቲካ ድርጅት ስለተከፋፈለ፤ አንደኛውን ክንፍ #የደፂ ህወሃት ወይንም #ደፂዝም ማለት ይገባል።    አሁን ባለው ፖለቲካዊ ጭብጥ በቀደመው ሥም መጥራት የተገባ አይመስለኝም። ህወሃት ሆነው ግን የህወሃትን አሁናዊ #ትወና ሊጋሩ የማይፈልጉ ወገኖች ስላሉ።   ወጣትነቴን አላውቀውም። ስለእኔ አስቤ አላውቅም። እኔን "የእኔ" አጀንዳ አድርጌም አላውቅም። በማገኛት አጋጣሚ ሙሉ መንፈሴን ከእኔ ውጭ ላሉ ሰብዕናወች አስባለሁ፤ እጨነቃለሁ፤ የምችለውን አደርጋለሁኝ።   ዘመኔን ቅርጥም አድርጎ የበላው ደግሞ አውራው ህወሃት እና #ጨካኙ ጉዞው ነበር። ብዙ በጣም ብዙ አቅሜን ያለ ገደብ በጸረ - ህወሃት ትግል ሰጥቻለሁኝ።   በቤተሰብ ይሁን በማህበራዊ ጉዳይም "ለእኔ" የሚል ሁነት ቀድሞብኝ አያውቅም። ስለሆነም የድምጽ አልባወቹ የኢትዮጵያ እናቶች #ዕንባ መሪዬ፤ መስመሬ መርሆዬ ነው።   ፈጣሪ እረድቶን በራሱ በአምላካችን ጥበብ ፈቅዶ ህወሃት እራሱን ከመንበረ መንግሥቱ ሸኜ። ይህ ትንግርት፤ ታምር ስለነበረ ከዚህ በኋላ በህወሃት ላይ የሚነሱ ወቀሳወች መበርከት የለባቸውም ባይም ነበርኩኝ።   ህወሃት የአማራ ክልል እና አፋርን እስከ ወረረባት ቅጽበት ድረስ፤ የኢትዮጵያ ዜጎችን ቁስለት ከዓለም ዓቀፍ ሚዲያ የማገኘውን መረጃ #በእኩልነት ዘገብኩኝ።   ...