#ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። #ፍቅር ሲያልቅም ትዕግሥት ይሰደዳል።
#ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። #ፍቅር ሲያልቅም ትዕግሥት ይሰደዳል። "ዳዊትም ሰው ከንቱን ይመስላል፤ ዘመኑም እን ጥላ ያልፋል፤ እያለ ስለእሱ ተናገረ።" (መጽሐፈ መቃብያን ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፳፫) #ምዕራፍ ፲፱። ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል፤ ፍቅር ሲያልቅም ትዕግሥት ይሰደዳል። በህወሃት መሸኛ ዘመን እጠቀምበት የነበረ አገላለጽ ነው። የሆነ ሆኖ አብን የሚሊዮኖች ድምጽ ሆኖ ወጥቶ፤ ያን ኃላፊነት እና ግዴታውን የተወጣበት መንገድ ግን ተስፋ ሰጪ አልነበረም። ሥልጣንን በሚመለከት አንድ የፖለቲካ ድርጅት የሚታገልበት በኽረ ጉዳይ ስለሆነ ለጋሱ ብልፄ ያቀረበለትን ገጸበረከት ይሁንታ ሰጥቶ መቀበሉ ለእኔ የሚጎረብጥ አልነበረም። ግን መነሻውን ከመድረሻው ለማዋህድ የተከተለው መስመር ግን ለአማራ ይሁን ለኢትዮጵያኒዝም የተስፋ ሂደት #እክል ነበር። ለብልፄ ብሎ አላስፈላጊ ቅራኔ ሁሉ ይገባ ነበር። ሁልጊዜ ከህውሃት ("ትህነግ") ጋር የነበረው አቲካራ አላስፈላጊ ነበር። አንድም የአማራ ጥያቄን የማስመለስ አቅምም አልነበረውም። በሌላ በኩል እሱ ያመነበትን መንገድ የሚከተሉ አማራወችን የማግኜት ዕድሉም ስስ ነበር። ስለሆነም ብልፄው የአማራ ህዝብን አራጦ ለመግዛት ዕድሉን አብን የማመቻቸት ዕድል ለብልፄ ማጉረስ አልቻለም። የተወሰኑ የአብን አመራሮች ህይወትን የማሻሻል ነገር እንደ ትርፍ ካየው ይሁንለት። የሆነ ሆኖ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ለጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ #የበኽር ልጃቸው ነው። ለትውልድ እንዲሆን አድርገው በሚገባ አደራጅተውታል። እኔም እከታተላቸው የነበረው ከዛ አንፃር ነበር። ልዩ ጊዜ ያሳለፋበት በኢትዮጵያኒዝም መንፈስም ያ የማይገኝ ጊዜ ይመስለኛ...