ልጥፎች

እናትም አባትም ሆነው ላሳደጉ አባት አቶ ይርጋለም ይህ #ጥቁር ዜና #ማት ነው።

ምስል
  እናትም አባትም ሆነው ላሳደጉ አባት አቶ ይርጋለም ይህ #ጥቁር ዜና #ማት ነው።   "የእግዚአብሄር ቸርነቱ ብዙ ነው እያልክ፤ በኃጢያት ላይ ኃጢያት አትሥራ።" (መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፭)   #ምዕራፍ ፲፱።         #የተባጀበት የወል አስጨናቂ የሰርክ መርዶ።   የሞዴል ሩት ይርጋለም እህት (ወ/ሮ ወት) ቅዱሳን ይርጋለም በሥጋ መለዬትን ዘሃበሻ ላይ ዜናውን ሰማሁኝ። የሁለቱ እህታማቾች #እናታቸውም ፤ #አባታቸውም አቶ ይርጋለም እንደምን ሆነው ይሆን? ልጃቸው ሞዴል ሩት ቃለ- ምልልስ ስታደርግ ዕድምታውን የተረዳሁት ልጆቻቸውን እያሳደጉ ፈቅደው #በምናኔ የኖሩ፤ በሥጋ ለተለዮዋቸው የትዳር አጋራቸው ፍጹም ታማኝ፤ ኃላፊነት እና ተጠያቂነት የሚሰማቸው ልዩ አባት መሆናቸውን ተረድቼ ነበር። በጣም ቁጥብ። እንደ እነዚህ ዓይነት ተብዕቶች ቁጥብ ናቸው። በዘመናት መሃል ነው የሚገኙት።   ይህን መሰል ሰብዕና #የተለመደ አይደለም። ትዳር በህይወት እያለ የክት እና የዘወትር የሚያሻቸው ባሉበት ዓለም፤ ትዳር በሥጋ ሲለይ ለዛውም በወጣትነት በዚህን ያህል ጽናት ዕድሜ ሙሉ #በተዕቅቦ መኖር መመረቅ ነው።    እንዲህ እራሳቸውን ሰጥተው፤ መኖራቸውን ለፍጹም ታማኝነት እና ለባለቤታቸው አደራ ጠባቂ በመሆን ያሳደጓት ልጃቸው ስትታፈን፤ #ስትታገት ጭንቁን እንሰበው። ለወላጅ ምጥ ነው። የተባለውን ገንዘብ ማቅረብ ስላልቻሉ ይመስለኛል እንሆ እንደዛ በብቸኝነት ያሳደጓትን ልጃቸውን ያጡት። እግዚአብሄር #ያጽነወት ። አሜን። ብርታቱን ይስጠወት። አሜን። ለማን ብለው በዓለም እየኖሩ መነኑ? ለልጆቸወት አይደለምን? አዝናለሁኝ።   ሞዴል ሩት ይርጋለም ይህን መሰል ሃዘን...

#ዋ! የዬኔታ ልቅና #ራስ #ዋሸራ! ሆይ! ሆይ!

  #ዋ ! የዬኔታ ልቅና #ራስ #ዋሸራ ! ሆይ! ሆይ!   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፱።   "ዋሸራ (ደብረ ምዕራፍ ዋሸራ ማርያም) በኢትዮጵያ፣ አማራ ክልል ጎንጅ ቆለላ ወረዳ (ምዕራብ ጎጃም) የሚገኝ ታሪካዊና መንፈሳዊ ቦታ ነው። ከአዲስ አበባ 426 ኪሎ ሜትር እና ከባሕር ዳር 82 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው ይህ ስፍራ፣ በርካታ ሊቃውንት የተገኙበት የቅኔ መገኛ ማዕከል በመባል ይታወቃል።ቁም ነገሮች፡የቅኔ አምባ፡ ከዋሸራ የወጡ የቅኔ ሊቃውንት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ታላላቅ ገዳማትና አድባራት በማስተማር ቅኔን አስፋፍተዋል።የቅኔ ዩኒቨርሲቲ፡ የቅኔ ጥበብን ለማሳደግ "የቅኔ ዩኒቨርሲቲ" ማዕረግ የተሰጠው ሲሆን፣ ታላላቅ የበዓላት በዓላት ለምሳሌ የአስተርእዮ ማርያም በዓል እጅግ በደማቅ ሁኔታ በቦታው ይከበራል።"   #ብሎት መሆኑን አውቃለሁኝ። በዓለም ውስጥ ላለነው፣ ለኢትዮጵያ የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች። ግን እንዲህ ህሊናን የሚያፈርስ ክስተት ሲኖር ቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ጉባኤ ጠርቶ ቤተ - እግዚአብሄራችን ጋሻ፣ ጦሯ፣ ድሮኗ፣ ኒኩለሯ፣ ባሩዷ፣ ትጥቅ እና ስንቋ #ጸሎት ነው። ፆም ነው። ሱባኤ ነው። ስግደት ነው። ምህላ ነው። ልመና ነው።    እግዚአብሄርን የተረገምንበትን ከልቶ ምህረት ይልክ ዘንድ ተንበርክኮ #ድሆ መለመን አያሽላንም። ይህን ማታዊ ዜና እንዲያስታግሰው፣ እንዲያቆረው ለሁሉ ጌታ አማኑኤል በዕንባ መጠየቅ ይገባ ይመስለኛል። አልቦሽነት ነገን፣ ማግሥትን አልቦሽን #ስለሚቀልበው ።   የወል ሱባኤ ጥቅሙ የአንዱ ባይደመጥ ከብዙኃን የእኔ ቢጤ ኃጣን አንድ #ዕዮባዊ አይጠፋም እና የወል ሱባዬ መያዝ የተገባ ይመስለኛል። እኔ ቅዱ...

#ገዳይ ሃሳብ በአካልም ይሁን በመንፈስ #በታኝ ነው።

  #ገዳይ ሃሳብ በአካልም ይሁን በመንፈስ #በታኝ ነው።   "እግዚአብሄር ቃየልን ወንድምህ አቤል ወዴት አለ አለው፤ ቃየልም በልቡ ትዕቢት የወንድሜ የአቤል ጠባቂ ነኝ አለ። አቤል ንጹሕ ሰውን ሆነ ቃየል ግን ደግ ሰው ወንድሙን አቤልን በመግደል ኃጢያተኛ ሆነ።" (መጸሐፈ መቃብያን ቀዳማዊ ም ፳፰ ቁ ፬ - ፭)   #ምዕራፍ ፲፱።   እንዴት አደራችሁ ማህበረ - ቅንነት።    እኔ አቶ ሽመልስ አብዲሳን ኢትዮጵያዊ #ጎልጉል እላቸዋለሁኝ። ግልጽ እና ቀጥተኛ ሃሳባቸውን ማጋራታቸው መልካም ነገር ነው። አይደለም በአገር ደረጃ በቤተሰብ እንኳን ይህን መሰል ግልጽ እና ቀጥተኝነት ጠቃሚ ጉዳይ ነው። ትዕቢታዊ ሁነታቸው ግን ይጎፈንነኛል። መታበይ ወንዝ አያሻግርም፤ ሥልጣንንም አያጸናም።    4ሺ ኢትዮጵውያንን በጋራ አሰባስቦ ያለው አገራዊ የምክክር ኮሚሽን ረጅም ጊዜ የወሰደበትን ተልዕኮ ለመቋጨት ስምንት በኽረ አጀንዳወችን የያዘ የመወያያ አቅጣጫ አመልካች ሰነዱን ሰሞኑን አስተዋውቋል። የተሳታፊ ቁጥር እየጨመረ ስለመሆኑም እያደየጥኩ ነው። " ኑ በራችን ክፍት ሆኖ ይጠብቃችኋል" የሚል ዕድምታ እንዳለም አንብቤያለሁኝ።   የሆነ ሆኖ ከዚህ ጋር በተያያዘ ብልፄው እንደ ፓርቲ ለምክክር ኮሚሽኑ አቀረበ የተባለው ሰነድ ደግሞ በአቻነት ወጥቷል። ከውስጥ የተገኜ መረጃ ይሉታል ዘመነኛ ተጽዕኖ ፈጣሪወች ወይንም የዩቱብ ባለቤቶች።    እንደምን የሚስጢር በር ለእነሱ ቧ ብሎ እንደሚከፈት፤ ለሌሎቻችን ደግሞ ክርችምችም እንደሚል በይገባኝም። የክት እና የዘወትር፤ የቤት እና የእዳሪ ልጅነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ልሙድ ነው።   የኦሮምያ ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ አገራዊ ምክክሩን ተከትሎ፤...