ልጥፎች

#ጊዜን የማድመጥ አቅም፣ ሊደመጥ ይገባል።

ምስል
  #ጊዜን የማድመጥ አቅም፣ ሊደመጥ ይገባል።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፥ ሰው ግን አያስተውለውም።"   #ክፍል ፲፱።   https://www.youtube.com/watch?v=8NoAvavswVk ኢትዮጵያ ቦታዋ አሁን ያለችበት አይደለም | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ETV | EBC | EBCDOTSTREAM https://www.youtube.com/watch?v=sN2roWE6dAs ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሰጡት ማብራሪያ   ሼር ባደረኩት ሊንክ ያዳመጥኩት ሲሆን፣ በጉዳይ ላይ ሦስት ጉልህ አመክንዮችን አስተውያለሁኝ። እና ሂደቱን በአራተኛ ደረጃ ላነሳ እሻለሁኝ።   1) ስለ ፕሮፌሰር ዶር. ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስተሩ የተነሳው በጎ ጉዳይ ነው። ገፊ ኃይሉ፣ ስለምን ጎልቶ እንደ ተነገረ ዛሬ ላይ ለእኔ ግልጽ ነው። ባለፈው በሰፊው ጽፌበታለሁ።   2) ስለ የጥበብ ቤተኞች የተሰጠው ማብራሪያ ነበር። "ዓዋቂወች ግን ……… " ጉዳዩን ባለቤቶቹ ይሂዱበት። እኔ በዚህ አገላለጽ የምሻውን ብቻ እገልፃለሁኝ።   3) ስለ " #የሠፈር ' ዕሳቤ በተነሳው ጉዳይ ምልከታዬን አቀርባለሁ።   4) የፕረዘንቴሽኑ #ቶን ፣ ጀስቸር እንዲሁ ብቃኜው ብያለሁኝ።   #አንከር ጉዳዮቼ።   ቁጥር 1) ስለ ፕሮፌሰር ከዚህ ቀደም ስለፃፍኩበት ሊንኩን አስቀምጣለሁኝ። ከእኔ ዕሳቤ ጋር አቻ የሆነ ዕይታ መራመዱን ወይንም አለመራመዱን የእናንተ ህሊና ይመዝነው ዘንድ እተወዋለሁኝ።   ቁጥር 2)    የጥበብ ቤተኞችን የህሊና አቅም ጎልቶ፣ የማህበራዊ ኑሮ ዘይቤያቸው ላይ ስስነት ተወስቷል። እራሳቸው ባለቤቶቹ ስላሉ እሱን ለእነሱ እሰጣለሁኝ። ተመቸ...

#ፕሮቶኮሉ እንደ ኢትዮጵያዊ አልተመቸኝም።

  #ፕሮቶኮሉ እንደ ኢትዮጵያዊ አልተመቸኝም።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   “PM Abiy Appointed AU Champion for AI and Digital Health.” https://www.ena.et/web/eng/w/eng_8705845 https://www.youtube.com/watch?v=S0YCAlonH8c «ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአፍሪካ የAI እና ዲጂታል ጤና መሪ ሆነው ተመረጡ | PM Abiy Ahmed AU Champion |”   #የሹመቱ ፕሮቶኮሉ በፍጹም አልተመቸኝም። ኢትዮጵያ መመረጧ መልካም ነገር ነው። በዘርፋም ጥረት እንደ አለ እከታተላለሁኝ። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድም በዲጅታል ደህንነት ላይ የሠሩ፤ ሙያውም ያላቸው ናቸው። ከፍ ያለም ዝንባሌ እንደ ነበራችው ቀደም ባለው ጊዜ አስተውል ነበር። እዚህ ደረጃ ሳይደርሱ እከታተል ነበር።    በተለይ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስተር ሳሉ። አንድ ብሄራዊ ውይይት አዘጋጅተው ነበር። " #ከእርምጃ ወደ ሩጫ" የሚል ሞቶ የነበረው። ይህን ዕርስ ወስደው ስለ አባይ ግድብ ውይይት ሲደረግም ያዬሁ ይመስለኛል። ባለቤቱ እሳቸው ናቸው እና በትምህርተ - ጥቅስ ማስገባት ይገባል። ሥንኙን መጠቀም የሚሹ ግለሰቦች ይሁኑ ሚዲያወች። እንዲህእንዲህ ዓይነት ሞቶ ዶክተር አብይ ይወዳሉ። "ከጎዳና ወደ ፓርላማም ብለውን" ነበር። ሂደቱ እራሱን የቻለ ፈተና ገጥሞታል።   የሆነ ሆኖ በዛ " ከእርምጃ ወደ ሩጫ" በጉባኤውም፤ ከዛም በኋላ በአገኙት የሚዲያ አጋጣሚ ሁሉ በዲጅታሉ ዘርፍ ዓለም ጥሎን እንዳይሄድ የቀረንበትን አስተካክለን አብረን መጓዝ የሚያስችል እርምጃ መውሰድ ካልቻልን፤ መጪው ጊዜ አብሮ ለመራመድ ይቸግረናል...

#ማስተዋል። ዘለግ ያለ ዕይታ ስለ ባለቅኔው ቴዲ አፍሮ።

ምስል
  • #ማስተዋል ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፱።   #አሜን ።   እንዴት አድረን? እንደምንስ አረፈድን? ማስተዋል ተሰጥቶናል በጌታችን መዳህኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በአላህ፤ ያን እንጠቀምበት ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን። አሜን።    "እዮሪካ" አልበምን። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉውን ለመጀመሪያ ጊዜ ሙሉ ቀን መድቤ አዳምጨዋለሁኝ። ሥንኞችን እየመላለስኩ አንብቤያቸዋለሁኝ። ሥራው ሐዋርያ ነው። ለሁላችንም ራዲዮሎጂ ነው። የምሥራቹ ደግሞ የኢትዮጵያ የሥነ - ጹሁፍ አቅም ከፍ አድርጎታል። ቋንቋወች ዘምነዋል። የቅንብር ሥልጣኔ በጉልህ ታውጆበታል። የህዝብ ፍቅር እናቀና ተሳትፎ ዘመንን አናግሯል። እያንዳንዳችን መርምሯል። የዳኜ ብቁ አቅም ነው።   #ትውስታ በምልሰት። ተያያዥ ጉዳዮች ዘለግ ብለው ይነሳሉ።    እኔ ሙዚቃ አድማጭ አይደለሁም። በልጅነት ጊዜዬ በአጋጣሚ ራዲዮ አቨይ አባቴ ያደምጥ ስለነበር ከዛ ጊዜ ወስጄ ያዳመጥኳቸው ከ10 አይበልጡም። እኔ እምሳበው በሥነ - ግጥሙ ይዘት ነው። ዛሬም በሙሉ ዕድሜዬ ይኽው ነኝ። ቤተሰቦቼ አብሶ ክብርት እናቴ ትወዳለች። ከእኛ ቤት በመደበኛ ሙዚቃ ይደመጣል። ቤተሰቡም ሙሉ ነፃነት አለው። እናቴ የአርቲስት ይሁኔ በላይ አድናቂ ናት። እኔ ደግሞ የመጸሐፍት ቀበኛ ሆኜ ነው ያደግኩት።   የሆነ ሆኖ ሚዲያወቼ በተፈጥሮ ዜማ ነው የምሰራቸው። በጸጋዬ ራዲዮ ሦስት ዓመት ቢሞላው ነው፤ ሙዚቃወቻችንም ይደመጡ ብዬ የፈቀድኩት። ይህም ሆኖ ኖቱ፤ ቅኝቱ፤ ቅላፄው፤ የላይኛው፤ የታችኛው የሚባለውን ጥበብ አላውቀውም።   ፍሬ ሃሳቡ የገባኝ፤ ስክርቢቱን ማግኜት ከቻልኩ በራዲዮ ዝግጅቴ አጫውተዋለሁ። ባመዛኙ በመሳሪያ ...