ልጥፎች

ከኦገስት 27, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ጦርነት ትርፉ ሁለመናን ማሳጣት ነው።

ምስል
ዎህ! በተመጠነ ሁኔታ! „ኖን። መንገዳችን እንመርምርና እንፈትን።    ወደ እግዚአብሄር እንመለስ።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፵ ከሥርጉተ©ሥላሴ 27.08.2018 ትውልዳዊ ድርሻ እንደ ወርቅ የሚፈተንበት አዲስ የተጋድሎ ዘመን።   ምርኩዝ። https://www.youtube.com/watch?v=CrjLmBMoEUc Ethiopia: አብዲ ኢሌ በአዲስ አበባ ከተደበቀበት በይፋ በቁጥጥር ስር ዋለ ·        የወ ግ ገባታ። ከድካም የሚያሳርፍ ፈቃደ እግዚአብሄር ነው። የቅድመ ዓለም የማዕከለ ዓለም የድህረ ዓለም ንጉሥ ክርስቶስ በቃችሁ ሲል እንዲህ ቸር ወሬ ያሰደምጣል። የኢትዮ ሱማሌ ነገር የተከደነ የጭንቅ አውዴ ነበር። ምክንያቱም ልጅ እያለሁ ነበር የኢትዮጵያ እና የታላቋ ሱማሌ ህልምን እውን ለማድረግ ሲያድ ባሬ ጦርነት የከፈተብን። ያን ጊዜ ቀበሌ ላይ የእናቴ ተሳትፎ እጅግ የሚገርም ነበር። ከት/ቤት ስመለስ ቁልፍ ለማምጣት ወደ ቀበሌ ስሄድ የኢትዮጵያ እናቶች ትጋት እጅግ ድንቅ ነበር። አቤት እንዴት ደስ ይል እንደነበር የነፃነት መሻት ዓውደ ዝማሜው ...  በመደዳ ምጣድ ተጥዶ ገብስ ሲቆላ፤ በመደዳ ሙቀጫ ተዘጋጅቶ ሲሾኮሾክ፤ በመደዳ ገብስ ተዘርግፎ ሲበጠር፤ ሲለቀም ታምር ነበር። ሌሎችም መሰናዶዎች ጎን ለጎን ሲከወኑ ... እናቶቻችን እኛን ወደ ት/ ቤት ሸኝተው እቃቸውን ይዘው በጥዋቱ ልክ እንደ መደበኛ ሥራ ወደ ቀበሌ ይገሰግሱ ነበር። ወንዶችም ገብሱን ከመኪና በማውረድ፤ ለሥራ በሚያመች መልኩ ከባባድ እቃዎቸን በማቀራረብ፤ በማደራጀት፤ በ እንጨት ፈለጣ፤ ውሃ በማቅረብ... ወዘተ ይሳተፉ ነበር። ትውናው አገር ማለት ምን ማለት እንደሆን ታላቅ ተቋም ነበር። የ

ማለዳ።

ምስል
አዱኛማ መቅድም። „ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታምኝነትህ ብዙ ነው።“ ሰቆቃው ኤርምያስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፳፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ 27.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። መነሻዬ ሊንክ። https://www.youtube.com/watch?v=cCGAqPKdPc8 ጠ / ሚኒስትር ዶ / ር አብይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች ልጆች ድጋፍ በተደረገበት ወቅት ያደረጉት ንግግር   መነሻውን ያወቀ መደረሻውን ያሳካል። መቅድሙን ከመዝለቂያው ልብ ላይ የተካነ ግቡን ያሳካል። ሩቅ በማስብ ውስጥ ማግስት አለ። በማግስት ውስጥ ቀጣይነት አለ። በቀጣይነት ውስጥ ትውልድ አለ። በትውልድ ውስጥ አገር አለ። በአገር ወስጥ መኖር አለ። በመኖር ውስጥ አኗኗሪ ነፍስ አለ። የአኗኗሪ ነፍስ የቀደመ - የተሰላ -  የተደራጀ - የተቀናጀ  - ቅናዊ - ቸራዊ እቅዳዊ ትልም ነው የማግሥት መዳረሻ። ከዚህ የተነሳ ትልም የፈለገ የፈተና ዓይነት ይከመርበት ይወጣዋል። ስለምን? ነገን ማሰብ ነው እና የዛሬ አኗኗሪ የነገ ተወዲያም ንጥረ ነገር ዋስተና ልእለ ጉልላት - እርስትም። በማያልቅ የሃሳብ ውጣ ውረድ እና ጉግስ ውስጥ የከተመ ብልህ ሁልጊዜም አያልቅበትም። ፏፏቴ! የማያልቅበት ደግሞ ነገን ለማደራጀት መሳሪያው በእጁ ነው ያለው። ለመሳሪያው ውል ደግሞ ያሰቡትን ለማሳካት ቆርጦ መነሳትን ይጠይቃል። ኢትዮጵያን ቁም ነገር ያደረገ መሪ በገቢረ ክህሎቱ ክህንቱ ያጸደዬ ነውና። በመኖር አኗኗር እና በአኗኗር መኖር መካከል ውስጥነት ካለ፤ ውስጥን ከውስጥ በማገናኘት ሃዲድ ለመዘርጋት ተፈላጊው ንጥረ ነገር እኛዊነትን በልባዊት በማጋባት፤ ማዕዳዊ ቤተኝነትን መፍጠር ነው። እኛዊነት በልባዊነት ሲጋባ ደግሞ የማግስት ተስፋ እድዮዊ

ለክፉ ነገርስ ችርስ መታመም ነው።

ምስል
ነገር ማጋጨቱን ብናቆምስ? „ሰው ሳይወድቅ በፊት ልቡ ከፍ ክፍ ይላል፤ ትህትናም ክብረትን ትቅማለች።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ 26.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·          ነገረኝነት በረከተ። መዋጋት እና ማዋጋት እለታዊ አጀንዳችን ሆነ። በዚህ በጠ/ ሚር አብይ አህመድ ከጋዜጠኞች ጋር የነበረው የመጠይቅ እና የወይይት ክ/ ጊዜም ይህን ስመለከት አዘንኩኝ። ምን አለ ስለ ኢትዮጵያ - ኢትዮጵያዊ አጀንዳ ቢኖረን። ምን አለ በዚህ መሰል ብሄራዊ ጉባኤ እንኳን ቀና ቀናውን ብናስብ። ምን አለ ስለ ወደፊቱ ተስፋችን ምን ብንደርግ እንዴትስ ተደጋግፈን ይህን ያገኘነውን ዕድል ከፍ ወደ አለ ደረጃ እንዴት እናሸጋግር የሚል ትኩረት ቢኖረን። የሚገርመኝ በአንዲህ ዓይንት ቴሌቪዥናዊ ውይይት ላይ ልጆችን እርግፍ አድርገን እንረሳቸዋለን። በጹሁፍ ላይ፤ በድህረ ገፆች ውይይት ሙግት ላይ የዛሬ ልጆች ብዙም ግድ አያሰጣቸውም አክሰሱን ቢኖራቸውም። ትልልቆችም ቢሆኑ ማድመጡን እንጂ ማንበቡን አይወዱትም፤ ጥቂት ሰው ነው ማንበብ የሚሻው። ነገር ግን በቴሌቪዥን ከሆነ ያዳምጡታል። የሆነ ሆኖ እኔስ እላለሁኝ በዬትኛውም ሁኔታ እና በዬትኛውም አጋጣሚ የቴሌቪዥን መግለጫዎች፤ የራዲዮን ውይይቶች፤ የቃለ ምልልስ ሂደቶች ሁሉ ልጆችም ሊያደምጡት እንደሚችሉ እያሰብን ቢሆን እመርጣለሁኝ። ልጓም ልናበጅለት ይገባልም ለአንደበታቸውን እላለሁኝ። ልጆች ዛሬ ሁሉም አጋጣሚ ስላላቸው ሁሉንም ነገር ለመወሰድ ጭንቅላታቸው ባዶ ሌጣ ወረቀት ማለት ነው። ጥቁርም ሲጻፍበት ጥቁር፤ ነጭም ሲጻፍበት ነጭ። የሚገርመው ነገር ከዛ ሁሉ ጠያቂ አንድም ሰው፤ አንድም ነፍስ ስለ ትውልድ የሞራል ቀረጻ አንዳችም ጥያቄ