ልጥፎች

ከኦገስት 28, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አላዛሯን ኢትዮጵያ የእኔ የማለት።

ምስል
የመቻቻል እጬጌዊቷ፤ ሉላዊቷ እናት ጠ/ ሚር አንጌላ ሜርክል  ለኢትዮጵያ! „አቤቱ አሳቦችህ በእኔ ዘንድ እንደምን እጅግ የተከበሩ ናቸው! ቁጥራቸውም እንደ ምን በዛ! ብቆጥራቸው ከአሽዋ ይልቅ ይባዛሉ፤ ተነሳሁም፤ እኔም ገና ከአንተ ጋር ነኝ።“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፴፰ ቁጥር ፲፯ እስከ ፲፰  ከሥርጉተ©ሥላሴ  28.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·         የልብ አድርስ ዜና። ውዶቼ የማከብራችሁ ትንሽ የልብ አድርስ ዜና አለችኝ። ያው የጹሑፌ ታዳሚዎች እንደምታውቁት እኔ በጀርመኗ መራሂተ መንግሥት በጠ/ ሚር  አንጌላ ሜርክል ልዩ የሆነ ተመስጦ አለኝ።  የ21ኛውም ምዕተ ዓመትም የሉላዊ የመቻቻል እናት ናቸውና። ሶርያ ያን ጊዜ እንደዛ በሁለገብ ችግር ስትናጥ፤ ስደተኛ እንደ ጎርፍ አውሮፓን ሲያጥለቀልቅ በነበረበት ወቅት ከስደቱ ግዝፈት አንፃር ሁኔታው ለአውሮፓው ህብረት ከአቅም በላይ ሆኖ ነበር። በዛ ላይ የሽብርተኝነት አደጋው ደግሞ መጠነ ሰፊ ነበር። ብዙም ተከታታይ አደጋ ነበር በፈረንሳይ እና በቤልጄየም። በሌሎች አውሮፓ አገሮችም ስጋቱ ይህ ነው አይባልም ነበር።  ስለሆነም የአውሮፓ ህብረት አገሮች የሚችሉትን ሁሉ አድርገው፤ ሸክሙ ሲባዛ በበቃኝ ፊታቸውን ሲያዞሩ እንሂ የዓለማችን ድንቅ ጽድቅ ግን ሁሉንም ነገር ተቋቁመው ያን የመከራ ጊዜ ተጋፈጡ። የርህርህና ጉልላቷ ዶር አንጌላ ሜርክል በሚመሩት በፓርቲያቸው በCDU አባላት፤ በደጋፊዎቻቸው፤ በአጋር እህት ድርጅቶች ሳይቅር ተዘርዝሮ የማያልቅ ፈተና ውስጥ ነበሩ። ተጨማሪ አዲስ የናዚ መንፈስ አራማጅ ፓርቲ አስከ መፈጠር የተደረሰበት ጉዳይ የስደተኛው መጠን ያለፈ ብዛት እና የነበረውም የህግ ጥሰት ቀወስ አስፈሪነት ነበር። ሴት ል

ቧልተኛው አቶ በረከት ስምዖን ...

ምስል
የአቶ በረከት ስምዖን ቧልት። „አኔ በስውር በተሰራሁ ጊዜ፤ አካሌም በምድር ታች በተሠራ ጊዜ፤ አጥንቶቼም  ከአንተ አልተሰወሩም።“ ከሥርጉተ©ሥላሴ 28.08.2018 ከኮሽ አይሏ ሲዊዝ።                                የአማራ ልጅ የተስፋ ትምህርት ቤት።                                 ይሄ ነው ድል የሚባለው የእነ ሳጅን በረከት የሰሞናቱ ምሾ። ይገርም ነው ነገሩ። አሁን ኢትዮጵያ ነበረች እያሉ ነውን እነ ሳጅን በረከት የሚፎካክሩት? እሚገርም ታሪክ እኮ ነው እዬተጠመደ ያለው። አሁን ያለው የብአዴን አመራር ለኢትዮጵያ ህልውና ያሰጋልም ነው የሚሉት አቶ በረከት ስምዖን?እኛ የመራንበት ዘመን ንጥር ነው እያሉን ነው? ይገርም እስከ ወዲያኛው። ይህን መሰል ቧልት ከቻሉስ ስለምን አቶ በረከት ስምዖን የኮሜዲ ማሰልጠኛ አይከፍቱም? የውነት ይሻላቸው ነበር።  እንግዲህ ምርኩዞቹን ሁሉ እንደማይቀጥሉ አልሻም ማለቱን ሰሞኑን ብአዴን ልብ ሰጥቶት ውሳኔ አሳልፏል። እርግጥ ነው ብአዴን ፌድራል ላይ ውክል አድርጎ የሚልካቸው አካሎቹ ያው ተዘው ቤተ ወያኔ ሃርነት ትግራይን ነው፤ ከአንድ ምንጭ፤ ትግራይም ተውክላለች የራሷን ልጆች፤ ድምጽም አላት እኩል 9ኙም 45ም፤ ብአዴን ደግሞ ተጋሩን ባህርዳርም በዳብል ያስኬድለታል።  የባህርዳሩ ቢሮው የወያኔ ሃርነት ትግራይ ለተጋሩ ሽፋን በመስጠት፤ አማራ በማህሉ አፈር ላይ እንደ ተረገጠ የእንብርክክ ይሄዳል። ነፍስ ያለው ሰው ስለዚህ የግፍ ዘመን እና የሚስጢር ቅብረት የ እኔ አለማለት መቼም በድንነት ነው።  የሆነ ሆኖ ብአዴን ለኢትዮጵያ ተስፋም ቀጣይነትም አስጊ ነው ማለታቸው ብአዴን አማራነትን አጥብቋል ከሆነ መቼም ተመሰገን ነው። ይሄ በፆም በጸሎትም

የሳጅን በረከት የምክር አገልግሎት በአፍንጫዬ ይውጣ። ...

ምስል
ግልግሉ መቼ ነው?  „ጠፈርን በህዋው ላይ አጸናት፤ ሰማይንም ማዬት በጸሐይ ብርሃን ነው።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፵፫ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  28.08.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።   ግልግሉ መቼ ነው? ·          መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=i8xI-WBrTMY Ethiopia: ሰይፉ ፋንታሁን ከአቶ በረከት ስምዓን ጋር ያደረገው ቆይታ ውዶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁን። ዛሬ ነፋሻማ አዬር አለ ተዚህ ከጋዳማዊቷ ውቢት ቆንጂት ሲዊዝሻ። ስለሆነም ዞር ዞር ብዬ ተመለስኩኝ። ደስ ይላል ሁለመናው። ሳጅን በረከት ስምዖን በርካታ ዲስኩሮችን እያሰሙን ነው። ባለፈው ሰሞናት ዶር አብይ አህመድ ድምጻቸው ጥፍት ባለበት ወቅት ከጠ/ ሚር ቢሮ የወጣ መግለጫ ይሁን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕከት ይህስ ጹሁፍ የሳጅን በረከትን ነው ጠረኑ ብዬ ነበር። እኔ የዶር አብይ አህመድን የጸሁፍ ጣዕም፤ የቃላት ይዘት እና ምቱን ስላጠናሁት ያ ጹሁፍ ሊገጥም ስላልቻለ ነበር እንደዛ ያልኩት። መልክዕቱ የጠ/ ሚሩ ነው ተብሎ ነበር የቀረበው፤ ነገር ግን መንፈሱ ደግሞ የሳጅን በረከት ነበር። በሰሞናቱ የሳጅን በረከት ስምዖን ቃለ ምልላሳቸውም ከጠ/ ሚር አብይ አህመድ ጋር በቅርበት እንደሚገናኙና የማመከር ተግባራቸውም እንደ ቀጠለ ተነግሮናል። ያው ነው በግል የቤት ሥራ እንደሚሰጣቸው እና የቀጥታ የስልክ ግንኙነትም እንዳለ አዳምጠናል። መቼ ነው ከሴራው ቸረቸራ ሀርድ ዌር አላዛሯ ኢትዮጵያ መቼ ነው የምትገላገለው አሰኝቶኛል።  እኔ እንደ ሌሎች ሰዎች አይደለሁም በይቅርታ እና በመቻቻል መንፈስ ጽኑ እምነት አለኝ። ሰው ባይፈቅደውም ጥሩ ሆነ መገኘት አትራፊ ስለመሆኑ አውቃለሁኝ። ጥ