ከማጣጣል ሂደቶችን በስክነት መከታተል ይበጃል - የአባ #ጠቅልልን የነገረ አጤ ሂደት - በማስተዋል። • የአቅም #ግኝት #ፍለጋው የሚያስተምረው ድርጁ ተመክሮ ስላለው።
ከማጣጣል ሂደቶችን በስክነት መከታተል ይበጃል - የአባ #ጠቅልልን የነገረ አጤ ሂደት - በማስተዋል። • የአቅም #ግኝት #ፍለጋው የሚያስተምረው ድርጁ ተመክሮ ስላለው። "የእግዚአብሄር ተራራ የለመለመ ተራራ ነው። የጸኑ ተራራወች ለምን ይነሳሉ? የእግዚአብሄር ይህን ተራራ ያድርበት ዘንድ ወደደው፤ በዕውነት እግዚአብሄር ለዘላለም ያድርበታል።" (መዝሙረ ዳዊት ፷፯ ከ ቁ ፲፭ - ፲፮።) #ምዕራፍ ፲፱። ሰሞኑን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ፤ ከተወዳጁ ተጓዥ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም ጋር ውይይት ነበራቸው። የውይይቱ ፍሬ ነገር ሳይሆን #ገፊ ምክንያቱ ምንድን ነው የሚለውን ሳስበው ሰነበትኩኝ። የሆቴል ሥራ #ብራንዱ የጀግና አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገ/ ሥላሴ ነው። የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ በኽረ ፕሮጀክታቸው ሆቴል መሥራት ነው። ሌላው የጠቅላዩ የጫካ ፕሮጀክት ትኩረታቸው ነው። ሰፊውን ጊዜ የሚሰጡት። የደን ልማት ፕሮጀክትም አላቸው። የአባይ ግድብ አሻራ #ሁለት ሰብዕና ጎልተው ይወጡበት ነበር። የቀድሞው ጠቅላይ ሚር አቶ መለስ ዜናዊ እና ኢንጂነር ስመኜው በቀለ። በፕሮጀክቱ ግንባታ ልክ ሰብዕናቸውም ተገንብቶበታል። የፕሮጀክቱ በአዲስ መሃንዲስ ተጠናቋል። በአባይ ግድብ ዙሪያ አጀንዳ ከኖረ የቀደሙት ሥሞች በማህበራዊ ሚዲያ ጎልተው ይወጣሉ። ይህ ባይፈቀድለትም ግን እየሆነ ያለ ዕውነት ነው። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ላጠናቀቁት ፕሮጀክት ፊድባኩ የሚነግረን መነሻ መሰረት የጣሉትን አክብሮ ይነሳል። ይህ ማለት በአባይ ግድብ ዙሪያ የነበረውን ቀደምት ዕውነት የህዝብ ህሊና ሴብ እንዳደረገው አስተውላለሁኝ። በነገራችን ላይ ስለ ጎርጎራ ፕሮጀክት ደርግ የሰራበት መዝ...