ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 30, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የነገረ ግብጽን እና ሱዳን ጉዳይ በሚመለከት ኢትዮጵያ እግዚአብሄር #ከፈጠረው #ቅንነት እና #ደግነት በላይ ናት።

ምስል
  የነገረ ግብጽን እና ሱዳን ጉዳይ በሚመለከት ኢትዮጵያ እግዚአብሄር #ከፈጠረው #ቅንነት እና #ደግነት በላይ ናት።   አቤቱ አምላኬ ሆይ! "በቸርነትህም ምራኝ።"       ዕውነት ለመናገር አገረ ግብጽን በሚመለከት የኢትዮጵያ መንግሥታት ሁሉ በባዛ #ቅንነት ፤ በገዘፈ #ትዕግስት መጠኑን ባለፈ #የመቻል አቅም ነው ኢትዮጵያ የገጠማትን፤ የሚገጥማትን ችግር ሁሉ ያስተናገደችው። እንዲያውም ሥልጣን ላይ የነበሩ፤ አሁንም ያሉ የፖለቲካ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ኢሊቶች ለተፎካካሪያቸው ሆነ ለተቃዋሚ የፖለቲካ #ዕሳቤወች ሆነ #ተቋማት በዚህ ያህል ቅንነት፤ በዚህን ያህል ትዕግስት፤ በዚህ የመቻል አቅም #ጥያቄወቻቸውን ለማስተናገድ እንደምን እንዳልቻሉ፤ እንደማይችሉም ግርም ይለኛል። የሃሳብ ልዩነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ለሞት፤ ለእስራት፤ ለመገለል፤ ለመሰወር ይዳርጋል።   ዕውነት ለመናገር ለግብጽ ኢትዮጵያ #የእናት ያህል ነው ጥያቄወቿን ሁሉ ስታስተናግድ የኖረችው። የአባይ ግድብ ከሃሳቡ እስከ ፍፃሜው እጅግ በሚደንቅ፤ በሚያስደም ብልህነት ነው ኢትዮጵያ የከወነችው።    ይልቅ ኢትዮጵያ ማድረግ ያለባት የገለልተኛ አገራትን ባለሙያወች በህይወት እያሉ በክብር ጋብዛ #መሸለም እንዲሁም የምስክርነት ተመክሧቸውን ቃለ - ምልልስ በማድረግን በፍጥነት ልትከውን ይገባታል ባይ ነኝ።   አጤ አባይን በሚመለከት ያን የመሰለ #የህሊና በሳል ቅድመ ዝግጅት እና #ስኩን ክንዋኔም በዶክመንተሪ በፍጥነት ዘገባው ሊሠራ ይገባዋል ባይ ነኝ። ለዕውነት #ፈጣን መሆን ያስፈልጋል። ውሸት ሲደራረብ ዕውነት ይመስላል እና። በዘንድሮው የተመድ ጉባኤም ሆነ ከዛ በፊት በማደምጣቸው ጉዳዮች በግብጽ በኩል ኢትዮጵያ #ተጫኝ...

ነፍሱ ከሥጋው የተለዬ፤ ሰላማዊ እረፍቱን የተነሳ የሰው ልጅ #አስከሬን ለፖለቲካ መደራደሪያ #የሚሰቃይበት ዘመን ያሳዝናል። «ትራምፕ እና ኔታንያሁ በጋዛ የሰላም ዕቅድ ላይ ተስማሙ» ዘገባው የBBC ነው። «የመካከለኛው ምሥራቅ እና የአውሮፓ መሪዎች የጋዛን የሰላም ዕቅድ እንደሚደግፉ ገለጹ»

ምስል
      ነፍሱ ከሥጋው የተለዬ፤ ሰላማዊ እረፍቱን የተነሳ የሰው ልጅ #አስከሬን ለፖለቲካ መደራደሪያ #የሚሰቃይበት ዘመን ያሳዝናል። አቤቱ አምላኬ ሆይ!    "በቸርነትህ ምራኝ።" አሜን።        ፕላኔታችን ትሁን፤ ስለ ሰው ልጅ መብት መረገጥ ግድ የሚላቸው ደጎች ሁሉ፤ ቁመን ለምንሄደው ቢቀር በሥጋ የተለዩት አካላቸው ለየትኛውም ዓለም የፖለቲካ ቅድመ መደራደሪያ #መያዣ የማይሆንበት ዘመን እኔ ይናፍቀኛል። ሰቅጣጭ እና አሰቃቂ አቋም ነውና።   እኔ ከዚህ በተረፈም የሰውን ልጅ የሚጎዳ ማናቸውም #የመዳህኒት #ቅመማ ሁኔታም የዓለም መወያያ አጀንዳ ይሆን ዘንድ እመኛለሁኝ። ጎጂ እንሰሳት፤ ጎጂ አረሞችን የሚቋቋም መዳህኒት መፈልሰም ለሰው ልጅ መኖር #ጥበቃ ያደርጋል። መሰሉን ለሰው ልጅ መጠቀመም ግን #ሰውኛም ፤ #ተፈጥሮኛም አይደለም። አቅሙ ምን ያህል እንደ ሆን ባላውቅም #ተመድ በዚህ ላይ አትኩሮት ቢሰጥ የሚል ህልም አለኝ።   አስቦበት የሚያውቅ ግን አይመስለኝም። ምንጊዜም ለሰው ልጅ ደህንነት እና የውስጥ ሰላም ማግኜትን ጥበቃ የምታደርግ ፕላኔትን አዘውትሬ እመኛለሁኝ።   አሁን ቢቢሲ አማርኛውን ስጎበኝ መልካም ዜና፤ #ቸር ዘገባ አገኜሁኝ። ለፍፃሜ ከበቃ ያን ሁሉ የሰቆቃ ገጠመኝ ያስተናገደው የፍልስጤም እና የእስራኤል ጦርነት በመልክ በመልኩ መቋጫ ያገኛል። ብዙ እጅግ ብዙ ጉዳትን ያስተናገደ ጊዜ ነበር። አሁንም ጦርነቱ አልቆመም። ይህ ዘገባ እንደሚያመለክተው ከሆነ በግራ ቀኙ በኩል #ይሁንታ አለ።    ይሁንታው ታትሞ ዕንባ ሲቆም፤ መጨካከን ቀጥ ሲል፥ ትውልድ ተስፋን የማየት #ፍንጣቂ ብርሃን ሲወጣለት ከደስታ በላይ ሐሴት ይሆናል። ጥ...

#የማይከብደው #ባይከብድ #ስለትውልድ።

ምስል
  #የማይከብደው #ባይከብድ # ስ ለትውልድ ።   "በቸርነትህ ምራኝ።"     #ምዕራፍ ፲፯   #ጠብታ   * ሰላም ለምን ይፈራል? ** ስለሰላም መትጋት ስለምን ይሸሻል? *** ስለሰላም መሆን እንደምን ያቅታል? ሰላም በኽረ አጀንዳችን ስለምን አልሆነም? ****በተለይ በትረ ሥልጣኑን ለያዘ አካል ሰላምን ማስፈን ለምን ይቸግረዋል?   #አይዋ ጦርነት አተረፍኩ ካለ፦ የሚያተርፈው የተቃጠለ ጠቀራማ አመድ እና በቀል ብቻ ነው ።   በሰላም ጉዳይ ሙሉ ኃላፊነቱን ሊወስድ የሚገባው ሥልጣን ላይ የሚገኝ የማንኛውም አገር መንግሥት ሊሆን ይገባል? ጦርነት ታቅዶም ይሁን ሳይታቀድ አትራፊ ክስተት አይደለምና። ጦርነት የሰቆቃ እና የዋይታ፤ እንዲሁም የውድመት #አንበል ነው። ይህ አሰቃቂ ክስተት እንደአይከሰት ጉዳዩን ወደ አገራችን ስወስደው ሰፊ ኃላፊነት ያለበት #የብልጽግና መንግሥት ነው። ወደ ጦርነት የሚወስዱ አቅጣጫወችን በሰላም ገርቶ ትውልድን #የማበርከት ኃላፊነት አለበት የብልጽግና መንግስት።    የብልጽግና መንግሥት #ኮበሌያዊ የእልህ ጉዞውን አቆሞ (ትዕዛዝ አይደለም ትሁታዊ ዕይታ ነው።) ምራቁን የዋጠ፥ የጉልምስና ባለፈም የአዛውንት ተግባራትን ሊፈጽም ይገባል። ዘወትር - ጦርነት፤ ሰርክ የሞት ዜና፤ ሁልጊዜ የስጋት ዓውድ እሰከ መቼ? እኔ #የምክክር ኮሚሽኑ ተግባሩ የሰርክ ሊሆን የሚገባው ብየ የማስበው በሰላም ዙሪያ አቀራራቢ ሃሳቦችን በማመንጨት ከፋኝ ብለው #ዱር ቤቴ ካሉት ወገኖቻችን ጋር ከጫካው ኦነግም ይሁን ከፋኖ ጋር #ቅን የሆኑ ውይይቶች የሚደረጉበትን ዓውደምህረት መፍጠር ይገባው ነበር ባይ ነኝ። ከሰላም በላይ የላቀ የህይወት፤ የመኖር፤ የሥልጣኔ በኽረ አጀንዳ የለ...