ልጥፎች

ከኦገስት 25, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የመቀሌ የፖለቲካ ትኩሳት ደግሞ ወደዬት?

ምስል
በዕለ አሸንዳ በትግራይ።   „ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን አይጠቅምም። ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም። “   የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕከት ወደ ቆረንቶስ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ© ሥላሴ 25.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። መቀሌ እንደለመደባት ሞቅ ደመቅ ብላለች። በሁለተኛው ስታዲዮዋ ላይ ደግሞ ሁለተኛውን ባዕሏን እያከበረች ነው። የትግራይ ባልሥልጣናት በሙሉ በተገኙበት በዚሐው ባዕል ላይ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው በባህላዊ ቀሚሱ ተውበው ተገኝተዋል።  በዚህ ባዕል ላይ ከትግራይ ደም ያላቸው ተዋናዮችን እና ታዋቂ ሰዎችም አንደተገኙ መረጃው ይጠቁማል። ዶር ደብረጽዮን ገ/ ሚኬኤልም አብያዊ ለመሆን በተሸለ አቀራረብ በሚመሯቸው ወገኖች ማህል ሰላምታ በመለዋወጥ እና በማከበር ቀረቤት እንዳላቸው አንድ ያልተለመደ ነገር ሲሳዩ ተመልክቻለሁኝ። ይህም መልካም የሆነው ያልተለመደው ነገር በወያኔ ሃርነት ትግራይ ሥር የወደቁ ነፍሶችን ከእሥር በባዶ 6 ያሉትን ግፉዕና በማስለቀለቅ እና የወረሩትን መሬት በክብር በመመለስ አብነቱን ወደ ስልጣኔ ቢያሻግሩት ምንኛ ይህ ድርጊታቸው ከልባችን በገባ በነበረ። በዚህ የአሽነድዬ ባዕል ባህላዊ ውዝዋዜውንም ሲያኬዱት ተመልከተናል። ከውስጣቸው ይሁን አይሁን አይታወቅም ብቻ ደስ ብሏቸው ሲወዛወዙ አይቻለሁኝ። በዚህ ዓመት በነበረው የትግራይ ህዝባዊ ኮንፈረንስም ላይ እንዲሁ ልባቸው ጥፍት እሲክል ድርስ ሲጨፍሩ አይቻለሁኝ። ይህ መቼም ሰውኛ ነው። እንደ ሰውኛ ጭፈራው ደግሞ ሌሎችን የሸር ገመዶችን እና የሴራ ድሮችን ተወት ቢያደርጉት መልካም ነው። ከሴራ፤ ከሸር፤

ትግራይ ሳትለግም።

ምስል
ልዕልተይ ትግራይ ከፈለገች  ፍቅራዊነት አይሳናትም።  ለግማ ነው እንጂ። „ሕይወት ከእግዚአብሄር የሚገኝ ሲሆን  ድርጎውን ከንጉሥ ይቀበላል።“ መጽሐፈ ሲራክ ምዕራፍ ፴፰ ቁጥር ፩   ከሥርጉተ© ሥላሴ 25.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። እኛ የምናውቃት ትግራይ እንዲህ በሰንደቅዓላማዋ፤ በሃይማኖቷ የማትደራደረውን  ዕንቁዋን ነው! የህዝቡን የኑሮ ደረጃም የህፃናቱ የለበሱትን አልባሳትንም እንዲሁ ማስተዋል ይቻላል።  ዛሬ ስለልዕት ትግራይ ትንሽ ልበል። ትግራይ የታሪክ ማህደራዊ ባዕት ናት። ትግራይ በቀደመው ጊዜ በነፃነት ዙሪያ የተምሳሌት ባዕት ናት። ትግራይ በቀደመው ዘመን የሰው አደራ የሚገኝበት ባድማ ናት። ትግራይ በቀደመው ዘመን የሃይማኖት ጽናት ጽላታዊ ተምሳሌት መንደር ናት። ዛሬስ ያ ዕሴታዊ ትሩፋት እና ትውፊት ሃዲዱ? ስለምትሉት እኔ ሳይሆን ራሳችሁን ትጠይቁ ዘንድ በትህትና አሳስባለሁኝ። ያው የእኔ ሞቶ ለድምጽ አልባዎቹ የኢትዮጵያ እናቶች ስለሆነ ትግራይም በዚህ ትታደማለች። ስለሆነም ስለነገ የትግራይ ህፃናት ስላልተወለዱት እጅግ ይጨንቀኛል። ሴቶቹ የነገም እናቶች፤ ሚስቶች እናሱው ናቸው እና። በተወሰነ ደረጃ የረገበ ነገር ያለ ቢመስልም ትግራውያን ግን አሁንም እንዳደቡ እንደሆነ ይደመጣል።  የሚዋጣቸውን የሚያውቁት እነሱ ስለሆኑ ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው ስለሆነ ይታለፍ አመክንዮው። በሌላ በኩል ግን "ለተራበው ትቼ ለጠገበው የማዘን ግዴታ" ስሌለብኝ ሹመኞችን መሳፍንታትን ግን እስኪባቀቸው በሰላ ብዕሬ ሰወቃቸው ባጅቻለሁኝ። የሆነ ሆነ በ27 ዓመቱ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ሥርዕዎ መንግሥት በደረሰው ህዝባዊ በደል ትግራይ በፀጥታ በዝምት ላይ ነበረች። የወገኖቿን የእ

የነገ መረጃ!

ምስል
ፍልስፍናዊ አመራር።    „የሰው ልብ መንገድ ያዘጋጃል  እግዚአብሄር  ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ምሳሌ ምዕራፍ  ፲፮ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ© ሥላሴ  25.08.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                                 ለዚህ ፎቶ እኔ ትልቅ አክብሮት አለኝ። ኢትዮጵያ ዕድለኛ የሆነችበት ዘመን ብዬ እማስባው ይህን ዘመን ነው። ለዚህም ነው ከጣና ኬኛ ጀምሮ በትጋት በግል የሚጣሉብኝ ሳንኮችን ሁሉ ተቋቁሜ፤ ጫናዎችን ሁሉ ተጋፍቼ፤ ማስጠንቃቄያዎችን ሁሉ ቸል ብዬ ለዚህ ንጹህ መንፈስ ስሞግት የባጀሁት። ትንፋሼ እሳከለች ድረስም ጉዳዬ የድምጽ አልባዎቹ ኢትዮጵያ እናቶች ዕናባ መግቻም መድህን ነው ብዬ በጽኑ አምናለሁኝ።  ወይ ዛሬ ወይ ነገ ጋዜጣዊ መግለጫ ይኖራል ተብሏል። በዛም ብዙ የዘበጡ፤ የተስረከረኩ ዘንባለ ዕሳቤዎች ደግሞ መልክ ይይዛሉ ብዬ አስባለሁኝ። እርግጥ ነው ከሰኞ ጀምሮ ደግሞ አቤሽን አካባቢ ጸጥ ረጭ እንደሚልም አንድ መርዶ አለ። ችግሮችን ከሥር ለማድመጥ የፈቀዱት መሪ ጠ/ ሚር አብይ አህመድ መፍትሄ ያገኙለታል ብዬም አስባለሁኝ። የሆነ ለእኔ መሪ ማለት ችግር ላይ ጥናት ያደረገ፤ ያን ችግር መፍትሄ ለመስጠት መንገዶችን የተለመ፤ የተለመውን ለመተርጎም ደግሞ ጥበብ ያለው ነው መሪ ማለት ለእኔ። ሌላው እኔ መሪ የምለው በቀደሙ ችግሮች ብቻ ሳይሆነ በገጠመኞች በሚፈጠሩ የገዘፉ አዳዲስ ችግሮችም ሳይደናገጥ፤ ሳይርበተበት፤ በስክነት እና በእርጋት የችግሩን የመነሻ ፌርማታ አጥንቶ ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት ጥበቡን ከህሊናው የማፍለቅ አቅም ያለው፤ በዚህም ተከታዮቹን አሳምኖ ወደ ድርጊት ለመቀዬር የቆረጠ ማለት ነው። ይህንም በጂጅጋ በሰው ሰራሽ ችግር የማምረቻ ማከፋፈያ አካባቢ የሆነው

በለው! ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ እግዚአብሄር የግንባሩም የጽ/ቤት ሃላፊ ናቸውን? ዳጥ!

ምስል
ጫን ተደል ሸክም። „እንሆ አፌን ከፍቻለሁ አንደቤተም በትናጋዬ ተናግሯል።“  መጽሐፈ ኢዮብ ምዕራፍ ፴፫ ቁጥር ፪ ከሥርጉተ© ሥላሴ ከጭምቷ ሲወዘርላንድ በ/ሮዋ ዙሪያ ...  ·               መጀመሪያ ያመለክትኩበት ቀን  01.06.2018 -  እርአስ አብይ ሆይ! ·            ሁለተኛ ያሳስብኩበት ቀን 08.08.2018  -  እርእስ - ቁልፍ ·           ለሦስተኛ ጊዜ ማሳሰቢያ ያቀርብኩበት 25.08.2018 እርአስ -  ጫን ተደል ሸከም። ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። ሰሞናቱ ትንሽ ዕንባ ተገስ ስላለ ይመስለኛል ደህንነቴ። እትዬዋ ግን ዛሬ ክፍት ብሏት ጭጭ ብላለች። እጽዋት ግን ባልሳቸውን ያስነኩታል በዝግታ እና በተደሞ።    v       የቅድሚያ። ኢትዮ ሱማኤልን በዘለቄታ መስመር ለማስያዝ የተወሰደው እርምጃ እና ሲከወን የሰነበተው ብሄራዊ ተግባር እጅግ አስደስቶኛል። አብሶ የመሪ ለውጡ እና በሰባዕዊ መብት ዙሪያ ሲተጉ የነበሩት ቅን የአካባቢው ተወላጆች አገር ቤት መግባት ለአዲሱ አማራር ማገር ሊሆኑት እንደሚችሉ ሳስብ ውስጤ ይረጋጋል ይጽናናልም። በሰብዕዊነት ጉዳይ ላይ ትጉኽ የነበሩት የ አቶ ሙስጠፋ ኡመር ወደ አማራር መምጣት፤ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ጀማል ዲሬይ ኸሊፍ አገር መግባት   ከአያያዝ ይፈረዳል ከአነጋገር ይቀደዳል እንዲሉ …. ተስፋን አሰንቆኛል።  በተያያዘ ዜናም በርካት ኢትዮ ሱማሌ ተወላጆች ከጠ/ ሚር አብይ አህመድ ጋር በአዲስ አበባ የተደረገው ውይይትም ተስፋን አበረታቶታል። ያው የሚያስፍልገው የአዕምሮ ዕጥባን በትጋት መከወኑ ነው፤ ለዚህ ደግሞ አቶ ጀማል ዲሬይ ይሸንፋሉ ብዬ አላስብም፤ ሃ