ልጥፎች

ከጃንዩወሪ 28, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

30የተኛ ሸክም ዘመን። በለሽታ ልምሻ አሻራ፤ በአልቦሽ ሌጋሲ ለለሽታም አሸኛኜት ……… ተቀለደ። ነገ ደግሞ ገራገሩ አማራ ያልተዘመረለት ትለን ይሆናል፤ ልታጀግን ስትፎክር ትገኝ ይሆናል፤ መጥኔ ብለናል።

ምስል
  30የተኛ ሸክም ዘመን። በለሽታ ልምሻ አሻራ፤ በአልቦሽ ሌጋሲ ለለሽታም አሸኛኜት ……… ተቀለደ። ነገ ደግሞ ገራገሩ አማራ ያልተዘመረለት ትለን ይሆናል፤ ልታጀግን ስትፎክር ትገኝ ይሆናል፤ መጥኔ ብለናል። ሲነሪቲ መነቀል ለስሜናዊ ፖለቲከኞች እንጅ ማህበረኦነግን አይመለከትም።     አዛውንት የኦነግ ፖለቲከኞች አሁንም ሥልጣን ላይ ናቸው። ስለዚህ መተካካት የሚለው የኮኔፊውዝድ ዕሳቤ የድቡሽት ቤት ይሆናል። የሆኖ ሆኖ ዘመናቸው በልዝ እንጨት የምመስለው የአቶ ደመቀ መኮነን ሽኝት ወይ አይነድ ወይ አያነድሆኖ የባከነ ዘመን ነው። ለትውልድም አብነት የማይሆን ያልሆነም።    የምዕራፍ ፲፩ ማጠናቀቂያ ወጋወግ። እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም እንዴት ነን? አቶ ደመቀ መኮነን ሙሉ 30 ዓመት በቅኑ ዬአማራ ህዝብ ውክልና፦ በተደላደለ ኑሮ እና ምቾት ቤተሰባዊ ኃላፊነታቸውን በሚገባ ተወጥተው፤ ለዛ ክብር እና ልዕልና ላበቃቸው ፍፁም ደግ፤ ፍፁም ሰው አማኝ፤ ፍፁም አክባሪ የአማራ ህዝብ ከቀዩ በዬዘመኑ መነቀሉ አልበቃ ብሎ፤ በድሮን ጭፍጨፋ እንዲያልቅ፤ ገዳማውያን በገፍ ሲገደሉ፤ ልጆች በወጡበት ሲቀሩ፤ ህዝብ በስጋት ረመጥ ሲቀቀል፤ በጠኔ ሲርገበገብ፤ እሳቸው ከገበርዲናቸው ጋር ይቆለማመጣሉ።   የአማርን ህዝብ በግዞት ይኖር ዘንድ፤ ተተኪ እንዳያፈራ ቀንበጥቹ ለሁለገብ አሳር ሲዳረጉ፤ በድህነት ለመኖር ሰላሙ ሲነጠቅ እዬኖሩ ያልኖሩም ያላኖሩም ሰው ናቸው አቶ ደመቀ መኮነን። ተንሳፋፊም ነው የነበሩት። በእንድም ዬኮሚቴ ሰብሳቢነታቸው ውጤታማ አልነበሩም። የሚገርመው ዛሬ ከአለምንም ኃላፊነት እና ተጠያቂነት በሽልማት ተንሳፋፊነታቸው ባለማህተም ሆኗል። #ሲነሪቲ የሚባል ደመኛ ያላቸው ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊም ስልችት ያላቸውን የአቶ ደመቀ

እዮባዊቷ ቅድስታችን።

ምስል
  እዮባዊቷ ቅድስታችን።   በማዕከላዊ መንግሥት ሁነኛ ልጅ የሌላት እናታችን። አባቶቻችን ቅድስና አላነሳቸውም። አቨው ልቅና አልጎደለባቸውም። ብፁዓን መንፈሳዊ ፀጋ አልሳሳባቸውም። ደናግላን ገሃዳዊ የቀለም ትምህርትም አልነጠፈባቸውም። ሁሉም አላቸው። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" አንዳንድ ነገር አዳመጥኩኝ። ቀረ፣ ጎደለ ስለሚባለው አመክንዮ። ግፍ ነው። በጣም። እርግማን እንዳይሆንም ፈጣሪ ይርዳን። አሜን። ብፁዑ አቡነ ኤርምያስ የሠሩት ገድል በቂ ነው፣ የማስተዳደር፣ የመምራት፣ የማደራጀት፣ የርህራሄ ክህሎታቸውን አይተንበታል። ይህ ሁሉ ሰርክ በግብረ ሰላም ዬሚሽሞነሞነው ዘመነኛ ባለስልጣን ሁሉ የሳቸውን ሲሶ ያክል አቅም ቢኖር የሚሊዮን ደም እና ዕንባ በቅድስት አገር ኢትዮጵያ ምድር ባላጎረፈ ነበር። በብዙ እኮ ተዋርደናል። አንገታችንም ተደፍቷል። ዬእኛ አባቶች ተረጋግተው ጥሪያቸውን እንዳይከውኑ ዘጠኝ አብያተ ቤተ ክርስትያናት በጅጅጋ በማቃጠል፣ በማንደድ ነበር የአብይዝም ዘመን አህዱ ያለው። ብፁዑዓኑ አበው አንድም ወር፣ አንድም ወቅት፣ አንድም ሳምንት፣ አንድም ዓመት፣ አንድም ጊዜ ከወከባ እርፍ ብለው ተረጋግተው የአደባባይ በዓላትን ያከበሩበት ጊዜ አልነበረም። አስተዳደራቸውን ሰክነው ለመምራት አልታደሉም። እነሱን የሚዋጋ የሰለጠነ ሾተላይ ዘመን ላይ ነውና የባጁት። በርካታ ቤተ መቅደሶች ሹግ ሆነዋል። ማህበረ ምዕመኑ፣ ማህበረ ካህናት እስከ ቤተሰቦቻቸው ሰማዕትነት በተለያዬ ጊዜ ተቀብለዋል። ሰብሳቢም የላቸውም። አጥቢያ አድባራት ዬፈረሱት ፈርሰው፣ የቀሩት ተዘግተዋል። ማህበረ ምዕመኑ ሚሊዮኖች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል። በሃዘን፣ በዕንባ፣ በዋይታ ዬከተመ ዘመነ ምፅዓት። እንደዚህ ዘመንም በርከት ባለ ሁኔታ ብፁዑ ቅዱሳን ጳጳሳት በሥጋ ዬተለዩን ዘመን የለም።

Warum hat die Welt immer Angst?

ምስል
  • Warum hat die Welt immer Angst?   Weil sie ihre Ruhe verloren hat. Wer hat ihr den Frieden genommen? Durch ihren eigenen Fehler • Warum? Wie ist es passiert? Die Welt hat ihren Kindern nie das Wesen der Liebe beigebracht, die Grundlage des Friedens. Also stören einige ihrer Kinder ihren Frieden. • Warum? Weil sie böse denken. Und die Welt macht sich Sorgen um sie. Unsere Welt hat Angst davon. Infolgedessen produziert die Welt mehr Waffen. Sie bildet viele Soldaten aus. Aber ich denke, es wäre besser, wenn sich die Welt für so viele romantische Naturschulen öffnen würde. Wenn sie viele Liebesprediger hervorbringe, würden gute Dinge in der Schule passieren. Unsere Welt wurde vor Angst bewahrt. Frieden auf Erden kommt von innen. Und das kommt durch Lernen. Auf Wiedersehen, bis wir uns in meinem nächsten Beitrag treffen. Ich wünsche Ihnen eine schöne Zeit. Gott das Heilige Land Schweiz; Heiliges Land Äthiopien; Schütze die Welt. Amen. Danke. Sergute©Selassie Serugute©Selassie 24.01.202

#አሳቻ ሳኦል!

ምስል
  #አሳቻ ሳኦል!   #ቅቤ ጠባሹ እንጦርጦስ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ አቶ ስብኃት ነጋ እና ቲማቸውን ባንፈታ #የአፍሪካ #አንድነት #ድርጅት #ከኢትዮጵያ $ይለቅ ነበር። የ30 አገሮች ኖ ሞራችሁን ብላሽ አደረጉት፣ ኖቬላቸውንም በዜሮ አጣፍተው በዝልኛቸው ወክ እንዲህ ……ለዚህ ዲያስፖራው አውካካካ በማንኪያ /// ዝልቦ /// ጨብ ጨብ ጨብ ጨብ ጨብ ጨብ ጨብ መንበጫበጭ …………//// በህወኃት መንበር ቲፍ አወች ጢነኝነት ዘገባው የማንዶልደያቸው የአቶ አቤል ብርኃኑ የወይኗ ልጅ ነው። ……… መኝታቸውን አንድ ቢያደርጉ ሲኦል + ሲኦል = ሲኦል። መቃብር + መቃብር። መቃብር። ሁሉም ፎቶወች የዕድምታውን ሂደት እያዋዙ ይከሽኑታል። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 24/01/2022 በቃን ዝልኝ አሳቻ ሳኦል!

#ሰንበተ ለአይዟችሁ!

ምስል
  #ሰንበተ ለአይዟችሁ!   ከቀያችሁ የተነቀላችሁ፣ መጠጊያ ያጣችሁ፣ በግፍ የተደፈራችሁ፣ በበሽታ ላይ ለካቴና የተዳረጋችሁ፣ በዬጫካው፣ በዬስደት ድንኳኑ አራሽ አልባ ዕንባማዎች ሰቀቀን አይታችሁ መኖርን የሸሻችሁ ምንዱባን፣ በግፍ የታገታችሁ፣ የተሰወራችሁ አሳረኞች፣ መሽቶ እስኪነጋ በጠላት ወታደር የበቀል ፍጥጫ መተንፈሻ ያጣችሁ መከረኞች፣ ቤተሰብ የተበተነባችሁ፣ የእንግልቱ ቤተኞች፣ በማያባራ የእርስበርስ ጦርነት ለተጎዳችሁ፣ በሜዳ ላይ የተበተናችሁ ህፃናት፣ ታዳጊዎች፣ ወጣቶች፣ በኢትዮጵያኒዝም ምክንያት ግማድ ተሸካሚዎች፣ ለዕለት ኑሮ፣ ለእራፊ ጨርቅ ያልበቃችሁ የጠኔ ቤተኞች፣ አይዟችሁ! ኢትዮጵያን የፈጠረ አምላክ መልስ አለው። መልሱ ካሳ ዋጋ አይጠይቅም። ፀሎት እና ምስጋና ብቻ። በዓለም የጭካኔ ዓይነት ተሞክረው የከሸፋ ጃርታዊ ተግባር ሁሉ እንደ ጥንቸል በምትሞከረው ኢትዮጵያ ተከውኗል። ኢትዮጵያ #የህሊናዋ #ቤተ - #መቅደስ ልጅ ትሻለች። ይህን ይሰጣት ዘንድ እንፀልይ። ሰው ነን እና እኛም እንደክማለን። ትተነውም እናልፋለን። ፈጣሪ ግን አይተዋትም። እናታችን አሁንም የምትኖረውም በኪነ - ጥበቡ ነው። ቅን ደግ ሩህሩህ አዛኝ መሆን ብቻ የመዳን መስመር ነው። የፊቱን የጀርባውን አትዩ። በተሰጣችሁ ልክ ብቻ ሁኑ። ትዕዛዝ አይደለም አስተያዬት እንጂ። እራስን ከማጣት በላይ አደጋ የለም። እራሳቸውን ያጡ ዓይንም፣ ህሊናም ቢኖራቸውም ግርድ ነው። እነሱን ማዬት አይገባም። ከእነሱ ጋር መፎካከርም አይገባም። ጠቃሚው በመክሊት ውስጥ እራስን ሳይሸሹ መኖር ነው። ለፍቅር ፍቅር ለመስጠት ስስታም ቆጥቋጣ አትሁኑ። ለግሱ በተሰጣችሁ ልክ። አይከፈልበት። ቢያንስ መኖርን በጨካኞች ለተቀሙ እንዘን። ተፈጥሯችን አናሰድደው። ፈጣሪ አምላክ በቃችሁ ይበለን። አሜን። ሥርጉተ©ሥላሴ

24.01.2020 ርህራሄ የመከነበት ዘመን።

ምስል
  ርህራሄ የመከነበት ዘመን።   የአማራ ህዝብ እያዬው ይመስለኛል አብይዝምን። የአማራ ሊሂቃን የተገደሉበትም አመክንዮ ፈጧል። የኢታ ማጆር ሹሙ ምክንያታዊ ግድያ እዬታዬ ነው። በዚህ ሁሉ ሰቆቃ ውስጥ ገዳይን መንፈስ የኢትዮጵያ አዳኝ አድርገህ ትፅፋለህ ትሞግታለህ። ማይክ ላይ ወጥተህ ትፈላሰፋለህ።   ይህን ስሰማ እነዚህ ሰዎች መጠቁ ይሆን እላለሁኝ? ሌላው ሊሂቅ ይመጣና እከሌን እመን አታውቀውም፣ እከሌን እመናት አታውቃትም ይልሃል። ሌላው ደግሞ ከአውጊ አደራ ጋር ፎቶ ተነስቶ ጀገንኩ ይልኃል። እነዛ በበላህሰብ ፍዳቸውን እዬከፈሉ ያሉ ነፍሶች አይመለከታቸውም ለኦነግ ካድሬነት ለተሰለፋ ዘመን ሰጥ ተደማሪ አንደበቶች እና ብዕሮች። ማፈሪያዎች። የገዳይ መንፈስ አቅም እኮ ጠሚር አብይ አህመድ ናቸው። ትናንት የዴያስፖራ አንበሳ ነኝ ብሎ ሜዳ አይባቃኝ ሲል የነበረው ዛሬ ድርጭት ሆኗል አገር ገብቶ። አገር ቤት ድርጭት ሆኖ ዘመኑን የሸኜው አገር አይባቃኝ ብሎ እንደጎረምሳ ይዘላል ይፈርጣል። በዚህ ማህል አገር በጨካኞች ታግታ ፍዳዋን ታያለች። ዥንጉርጉር። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ቸር ወሬ ያሰማን አሜን።