ልጥፎች

ከሴፕቴምበር 28, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ተፈጥሮን ያዘመነው የማሰብ ፍልስፍና ልቀት ነው።

ምስል
መሆንን በማሰብ፤ መሆንን በመቻል፤ መሆንን በመሆን። „ይህ ህዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤“  የማቲዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 28.09.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።   v   መ ቅድም። መሆን በመሆን ቢጣፋ? መሆን በመሆን ቢባዛ፤ መሆን በመሆን ቢቀመር በመሆን ውስጥ መኖርን ያጠይቃል። መሆንን ማሰብ፤ መሆን በመቻል ማቻቻል፤ መሆንን በመሆን ማትጋት ሁሎችም የተፈጥሮ መብቶች ናቸው። ልዑል እግዚአብሄር የሰጠን። እርግጥ ነው መሆንን ማሰብ ገደብ የለውም።  መሆንን መቻል ግን የሚከብዱ ነገሮች ይኖራሉ። መሆንን በመሆን ዕውን ለማድረግም እንዲሁ።አንደኛው ለምሳሌ ሊሆኑ የፈለጉትን አለማግኘት ነው።   v   መ ሆንን ማሰብ። መሆንን ማሰብ የሚነሳው ከራስ ብቻ አይደለም ከቤተብም ከአካባቢም ሊሆን ይችላል። ብቻ መሆን ማሰብ እስከ ዕድሜ ልክ አብሮ አድጎ እስከ ገሃዱ ዓለም ሥጋዊ ስንብት ድረስ አኗኗሪ ነው። በዚህ ውስጥ ማሰብ ራሱን የቻለ መክሊትም አለው። ከአካባቢ ወጣ ያለ ምናባዊ፤ ፍልስፍናዊ እሳቤም ይኖራል። ማሰብ ድንበር የለውም እንደ ተፈጥሮ ጸጋ ለሚያዩ አካላት። መኖር የተፈጠረው በማሰብ ሃሳብ ውስጥ ነው። ማናቸውም የመኖር ሁለመና መሰረቱ በማሰብ ልቅና የተገኘ ነው። ከማስብ ልቅና፤ ከማሰብ ብልጽግና ውጪ የሚፈጠሩ የፈጣሪ ፍጡራን እና ተፈጥሮ ብቻ ነው። ተፈጥሮን አሰልጥኖ፤ ተፈጥሮን ዘመናይ ያደረገው የማሰብ ፍልስፍና ልቀት ነው።   v መ ሆንን በመቻል ማቻቻል። ሊሆኑ የፈለጉትን ቢያገኙትም በመሆን ውስጥ ካልተከተበ ብላሽ ነው መሆንን ማሰቡም ሆነ መሆንን በመቻል ለማግኘት። መሆን በማቻል ማቻቻል የማድረግ አቅሙ ተመጣጣኝ ምቹ ሁኔታ እና

እንባ ያቆረዘዘው የ2011መስቀል።

ምስል
ሹግ እና ብርሃኑ አለቀሱ። እጃችሁን ለእግዚአብሄር ስጡ፤ ለዘላላሙ ወደ ተቀደሰው ወደ መቅደሱም ግቡ፤ ጽኑ ቁጣውም ከእናንተ እንዲመለስ አምላካችሁን እግዚአብሄርን አምልኩ። (መጸሐፈ ዜና መዋዕል ምዕራፍ ፴ ቁጥር ፰) ከሥርጉተ©ሥላሴ 28.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። የዕባማውም ሹግ ግማድ ጉሽ! ከቀደሙት ዓመታት መስቀል ሳይመስለኝ ያለፈው የዘንድሮው የ2011 ነው። ፈጽሞ ጠረኑ ድብርት እና ደመመን ተጭኖኝ ነው ያለፈው። ቤተሰቦቻቸውን ለማዬት በተጓዙ ኢትዮጵውያን የደረሰው የመኪና አደጋ ማግስት ነው ባዕሉ የተከበረው። እንደ ብሂሉ ባሳብው  „እንዳያም ጥራው እንዳይበላም ግፋው“ ዓይነት ሆኖ ውጥረት ተፈቅዶለት ተከብሯል። ሁሉም አምጦ እንዳከበረው አስባለሁኝ። የመርዶ ያህል መጪውን ጊዜ እያሰበ …  በ ዕንባም ሰምጦ። እኔ የ2011 የደመራ ባዕል ያለቀሰው የመስቀል ባዕል ብለው ይሻላል። ከሁሉም ዘመን እጅግ ጫና እና ውጥረት በብሄራዊ ደረጃ በበዛበት ሁኔታ የታሰበበት በዓል ቢኖር ዘንድሮ ነው። እርግጥ  ነው የአማራ የማንነት የህልውና ተጋድሎ በተካሄደበት ወቅት በዕሉ በጎንደር ተሰተጓጉሏል፤ ጫናውም በብሄራዊ ደረጃ እንደ ነበር ባስታውሰውም፤ ያን ጊዜ የነፃነት ፈላጊው ጉልህ መንፈስ ጎልቶ ሲሆን አሁን ግን ማተቡንም የሚያፈታተን የልታወቀ መንገድ እዬናጣው ነው አዬሩን ነው የታሰበው... ወዮልሽ ቤተሳይዳ!  ለነገሩ የ2011 የሬቻ ባዕልስ የሚለውን ለሚዛን ግብረ መልስ ነገ የሚሰጠን ይሆናል?  ያን ጊዜ በዘመነ አማራ ተጋድሎ ባህርዳር አንድ ብጹዑ አባት እዮር ልኮ ልጆቻቸውን በመንፈሳቸው አቅፈው እና ደግፈው አጽናንተው እና አበረታተው፤ ችግሩን አብረው ተጋረተው ከጎኑም ተሰለፈው ነበር፤ የብፁዑን አባታችን የአ