ልጥፎች

ከሜይ 3, 2024 ልጥፎች በማሳየት ላይ

BBC "በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሱ ያሉ ‘የጅምላ ጭፍጨፋዎች’ ሆን ተብለው እየተፈጸሙ እንደሆነ የአውሮፓ የፍትሕና ሕግ ማዕከል የተባለ ድርጅት አስታወቀ"

ምስል
 https://www.bbc.com/amharic/articles/c4n10p0elr7o   በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሱ ያሉ ‘የጅምላ ጭፍጨፋዎች’ ሆን ተብለው እየተፈጸሙ እንደሆነ የአውሮፓ የፍትሕና ሕግ ማዕከል የተባለ ድርጅት አስታወቀ የፎቶው ባለመብት, Getty Images 2 ግንቦት 2024 የአውሮፓ የፍትሕና ሕግ ማዕከል የተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት “ድምጽ አልባው የአማራ ሕዝብ ስቃይ በኢትዮጵያ” በሚል አርዕስት ባወጣው ሪፖርት በክልሉና ከክልሉ ውጭ ከ2010 ዓ.ም. ጀምሮ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ዘርዝሯል።በአውሮፓ እና በአለም አቀፍ ደረጃ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ላይ የሚሰራው ማዕከሉ የአገሪቱን የረጅም ዘመን ታሪክና የተወሳሰበ የፖለቲካ ስርዓት ቃኝቶ ሪፖርቱን የሚጀምር ሲሆን፤ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያ ጉልህ የሆነ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ጨምሯል ብሏል።በግጭቶች የሚባባሰውና በዋናነት በአማራ፣ ኦሮሚያና ትግራይ ክልሎች የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዓለም አቀፍ ትኩረትን ማግኘታቸውን የሚጠቅሰው ሪፖርቱ፤ በተለይ ግን በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመው በደል የጥልቀቱን ያህል በቂ ሽፋን አያገኝም ብሏል። መቀመጫውን ፈረንሳይ ያደረገው እና ከአውሮፓውያኑ 2007 ጀምሮ በተባበሩት መንግሥታት ልዩ የአማካሪነት ስፍራ እንደተሰጠው የጠቆመው ማዕከሉ ይህን ክፍተት ለመሙላት በአማራ ማሕበረሰብ ላይ እየደረሰ ነው ያለውን በደል በደንብ በመፈተሽ ሪፖርቱን ስለማውጣቱ ጠቅሷል።የሪፖርቱ ግኝት በአማራ ሕዝብ ላይ አሳሳቢ፣ ሰፊና የተያያዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እተፈጸሙ እንደሆነ ጠቁሟል። ለዚህም አሁንም ድረስ እተፈጸሙ ናቸው ያላቸውን ጥሰቶች የሚያነሳ ሲሆን፤ እልቂቶች፣ ያለ ፍርድ ግድያዎች፣ የድሮን ጥቃቶች፣ በኃይል ማፈናቀል እና የጅምላ እስሮችን ዘ

መወላለቃችን አሁንም አልታዬንም።

ምስል
      መወላለቃችን አሁንም አልታዬንም። "የሰው ልብ መንገድ ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱) ገና ከመነሻው ፍላጎታችን #ባለቤት አልነበረውም። እንወጣዋለን ለእኛ ተውት ያሉትም መተንፈሻ ሲያገኙ ካለአቅማቸው ነበር እና ኃላፊነቱ አላቀቀን ብለው የአራጅ አባሪ ገባሪ ሆነው አረፈቱ። ለመሆኑ #አይዋ ትግል የአሁነኛው ሥምህ ማን ይባል ይሆን? ለፍትህ? ለነፃነት? ለርትህ? ለዴሞክራሲ እንዳትለኝ እና ቁጥቧን ሳቄን እንዳታፈነዳት። እራሱ አሁናዊ ትግሉስ ቀለሙ፣ ጣዕሙ፣ ቁመናው ማን ይሰኛል? ለመሆኑስ ብሄራዊ ታጋዩስ አለን? ማነው ባለቤቱስ? ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ እንደ ፍጥርጥርህ ተብሎ የተሰጠው አደራ ነፍሱ አለን? ትንፋሹ ብን ትር ትላለች #የአሻግሬ ማሸጋገር? ምን የተያዘ? ምን የተጨበጠ ነገር ኖረን? ከአንድ እርቦ #የሚርነት ማዕረግ በስተቀር። ለዛስ #ሥልጣኑ ወይንስ #ደሞዙ ይሆን ያለው? እንጠይቃለን። ጥያቄውም አያልቅ እኛም አይደክመን? ለመሆኑ አሁን እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ የቀረን፣ የተረፈን ኢትዮጵያዊ ተቋም? ክብር? ልዕልና? አለን። ደፍረን እንናገራለን? ተስፋ ደረጃው የት ላይ ይሆን? አፈላልጋችሁት ታውቁ ይሆን አባ ወራ የአገር መሪነት እጮኛ የነበራችሁት። ከዘመን እስከ ዘመን የተሰው ሰማዕታት ተነስተው ቢጠይቁን መልስ አለን? በተለይ ሁሉንም ጨፈላልቃችሁ #አውራ ነን፣ እኛ ህይወት እና መንገድ ነን ላላችሁ ሰብዕናወች ተኝታችሁ ማደራችሁ ይገርመኛል። እንቅልፍ ይወስዳችሁ ይሆን? ስንት ቡቃያ አዝላችሁ፣ ነቅላችሁ እንዲህ አገር #አረም ሲበቅልባት። ሙሉ ትውልድ ከተስፋው ሲነቀል፣ ከተስፋው ሲቆራረጥ፣ በተበተነ ሃሳብ ሲታጨድ፣ ጎዳና ላይ ሲወድቅ። #የተረፈን ነገር አለን? #አለን የም

2.05.2020 የት ላይ ነን? ጥያቄው ሁላችንም ይመለከታል።

ምስል
      የት ላይ ነን? ጥያቄው ሁላችንም ይመለከታል። ከእንግሊዝ አገር ከቢቢሲ የአማርኛው ክፍል ያጋራሁት ልብ የሚነካ የነርሷ የመጨረሻ ቃል ልቤን መሰጠው እና እራሴንም ጠዬቅሁት። የሌላው አገር ሁሉም የተደራጀ ሆኖ መንግሥትም እያላቸው ኮሮና ነው አሁን አገር እዬፈታ ያለው። እኛ ሁሉ የሌለንስ? የት ላይ ነን ሞት እንዲህ በሆነ ሁኔታ በዬሰከንዱ እዬፈተነን ለመሆኑ እኛ የት ላይ ነው። ማንስ አለን ለጋህዳዊው ዓለም መኖር? የዶር አብይ መንግሥትስ የት ላይ ነው? ምን እዬሠራ ነው። ያው ይህ እንዲሆን ቀድሞ የሰራው ነገር በሲነሪትም በመደበኛ ዕውቀትም ይበልጠኛል ያለን ዶር አንባቸው መኮነን አስወግጿል። ህልሙ ምዕራብውያኑና አውሮፓውያኑ ተፎካካሪ አሳተፉ እንዲባል ኢዜማን አማራ ክልልን ወክሎ እንዲወጣ ማድረግ ነበር። አልተቻለውም። ምን እዬሆነ ነው? የመስቃ ዱላውስ እስከመቼ ነው? ይህ ሁሉን ሰብዕና አንደርማይን የማድረጉ ሂደት ለዚህ ወቅት እንደ ቢታሚን ቢ ተቆጠረ ይሆን? ለመሆኑ እኛስ እኔን ብቻ አድምጡ የሚለው ብቸኛው አራጊ ፈጣሪ ዱለኛው የአብይዝምን መታበይ፣ ማፌዝ፣ ዱላ፣ መስቃ እንዴት እናዬዋለን? ሥርዓት የለም። የመንግስታዊ ለቦታው የሚሰጥ። ልቅ ሰብዕና። ገራሚው 60 አመት ሙሉ ፖለቲካ ድርጅት ስንፈጥር፣ ስንስረው ስንበትነው ኖረን ዛሬ ይህን ዱለኛ ሥርዓት የመተካት አቅም ከዜሮ በታች ሲሆን ህይወታቸውን የሰጡት ኢትዮጵያዊ ወገኖቼ እና ቤተሰቦቼን አስቤ በውነት አነባሁኝ። በቃ በድፍረት አገር ለመምራት የሚያስችል ቁመና ላይ አይደለንም ይላሉ ተፎካካሪዎች። ትውልዱ አያሳዝንም በዬዘመኑ የከፈለው አሁንም ያላባራው መስዋዕትነትስ ከዬት ይጠጋ? አሁን ትናንት የተፈጠረ ይህ የጨረቃ ቤት ብልፅግና ፓርቲ ሆኖ ይህን ያህል መስቃውን ሲያወርደው እልሁ፣ ቁጭቱ ፖለቲከኛ ነኝ

እናትነት እናታዊነት እና መራራው ዕጣዋ በኢትዮጵያ ፖለቲካ።

ምስል
    እ ናትነት እናታዊነት እና መራራው ዕጣዋ በኢትዮጵያ ፖለቲካ።   ይ ሁዳ እንኳን ጎለጎታን አልነፈገም። በኢትዮጵያ ግን ይህም አይፈቀድም። የዘመኑ ምጽዓታዊነት ከዚህ አንፃር አዬዋለሁ። የርግማን ይመስለኛል። ሙ ሴ የተባለ ሰብዕና ምድር አስተናግዳው የማታውቀውን አረማዊነት ሲፈቅድ ፈጣሪ ይዳኜው ዘንድ ወደ እሱ አቤት ማለትን በጽናት ይጠይቃል። ሌ ሊቱን ይህን ሳስብ ይሁዳ እሺ ባይል የጎለግታ ታምርንስ እናይ ይሆን ነበርን ? ምንስ ይፈጠር ነበር ? ሥነ ሥቅለቱ ላይ እርገት ወይስ ትንሳኤ ? ብፁዑ አቡነ ሉቃስ « ኧረ ልብ ይስጥህ» ብለዋል። እንደአፋቸው ያድርግልን አሜን።   መ ከረኛውን ማህፀን አምላኬ መጽናናቱን ይስጥ ብያለሁኝ። እንዲህ ያለ ዘመንን የምንላቀቅበት የሰከነ ህሊና እና ተግባር የላይኛው ይስጠን አሜን። ይ ህን እያሰብኩ በግልጽም በስውርም በጨካኙ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ባህል እናታችሁን፤ ልጃችሁን፤ ትዳራችሁን ቤተሰባችሁን ያጣችሁ ሁሉ እ ግዚአብሄር ጥናት መቀነቱን ይስጣችሁ፦ ይስጠን። ። ክ ብረቶቼ እንዴት ናችሁ። አይዞን። «ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።» ሥርጉተ © ሥላሴ Sergute©Selassie 3/05/2024 አባት ሆይ ! ፅናትህን ለአደብ እናደርገው ዘንድ እርዳን።