ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 4, 2025 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የእኛ መከራ ማለቂያ የለውም። ሞት ስንቃችን ሆኑ። "በጉጂ ዞን ወርቅ በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች መሬት ተንዶባቸው ሕይወታቸው አለፈ" BBC

    "በጉጂ ዞን ወርቅ በማውጣት ላይ የነበሩ 8 ሰዎች መሬት ተንዶባቸው ሕይወታቸው አለፈ" https://www.bbc.com/amharic/articles/c70kn2y5pn8o   ከ 3 ሰአት በፊት "በጉጂ ዞን ሰባ ቦሩ በተባለ አካባቢ ወርቅ በማውጣት ላይ የነበሩ ሰዎች መሬት ተደርምሶባቸው መሞታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን ውስጥ አደጋው በደረሰበት አካባቢው ነዋሪ የሆኑት ኢዮብ ጂሎ እንዳሉት ለአደጋ መንስዔ የሆነው በማሽን የተቆፈረ መሬት ነው። "መሬቱ በሁለቱ ቦታ በማሽን ተቆፍሮ ነበር። ሰዎች በተቆፈረው መሬቶች መካከል ገብተው ነበር ወርቅ ሲፈልጉ የነበረው። በዚህም ምክንያት መሬቱ ተደርምሶ ሕይወታቸው ሊያልፍ ችሏል" ሲሉ ተናግረዋል። አደጋው ሰኞ ጥር 26/2017 ዓ.ም. ጠዋት 3 ሰዓት አካባቢ መድረሱን የዓይን እማኙ ተናግረው ሁሉም ሟቾች ወንዶች መሆናቸውን አስረድተዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች በማሽን እና በባሕላዊ መሣሪያ ታግዘው በአደጋው ከመሬት በታች የተቀበሩትን ሰዎች ለማዳን ለአምስት ሰዓታት ያህል ቁፈሮ ካደረጉ በኋላ ግለሰቦቹ ሕይወታቸው አልፎ አስከሬናቸውን ማውጣታቸውን ተናግረዋል። ከአደጋው የተረፉ ሰዎች እንደሌሉ እና መሬቱ ተንዶባቸው ተቀብረው የነበሩት የሁሉም ሰዎች አስከሬኖች መውጣታቸውን አክለው አስረድተዋል። የጉጂ ዞን የኮሚዩኔክሽን ኃላፊ አሸናፊ ዳንቁ በአካባቢው በባሕላዊ መንገድ ማዕድን የሚቆፍሩ ሰዎች ላይ መሰል አደጋዎች እንደሚከሰቱ ገልፀዋል። "በባሕላዊ መንገድ ማዕድን የሚያወጡ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ለአደጋ የተጋለጡ ናቸው። አንድ ጉድጓድ ውስጥ በርከት ብለው ነው የሚቆፍሩት። ይህ ደግሞ አደገኛ ነው" ብለዋል። አክለውም በባሕላዊ መልኩ ወርቅ የሚያወ...

"ስዊትዘርላንድ ስደተኞችን ለመቀበል ፈቃደኛ ላልሆነችው ኤርትራ የምትሰጠውን እርዳታ ለማቆም ወሰነች" BBC

ምስል
    "ስዊትዘርላንድ ስደተኞችን ለመቀበል ፈቃደኛ ላልሆነችው ኤርትራ የምትሰጠውን እርዳታ ለማቆም ወሰነች"  https://www.bbc.com/amharic/articles/cm23120denvo   የፎቶው ባለመብት, Getty Images   ከ 2 ሰአት በፊት "ስዊትዘርላንድ፤ የኤርትራ መንግሥት ተመላሽ ስደተኞችን ለመቀበል ባለመስማማቱ ምክንያት ለሀገሪቱ ስታደርግ የነበረውን እርዳታ ለማቋረጥ ወሰነች። የስዊትዘርላንድ መንግሥት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ኤርትራ ስደተኛ የሆኑ ዜጎቿን እንድትቀበል ለማበረታታት ሲሰጥ የነበረው እርዳታ የታለመለትን ግብ ለማሳካት እንዳልቻለ በሀገሪቱ መንግሥት የተደረገ ግምገማ ካረጋገጠ በኋላ ነው። የስዊዝ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ዘገባ እንደሚያመለክተው ስዊትዘርላንድ ውስጥ ሰባት ሺህ ገደማ ጊዜያዊ ተቀባይነት ያገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች ይገኛሉ። ከሁለት መቶ በላይ በሀገሪቱ የሚገኙ ኤርትራውያንም ሀገሪቱን ለቅቀው እንዲወጡ ይጠበቃል። የስዊትዘርላንድ መንግሥት ኤርትራ ተመላሽ ስደተኞችን እንድትቀበል ለማበረታታት የቀረጸውን "የልማት እርዳታ ፕሮግራም" መተግበር የጀመረው እ.አ.አ በ2017 ነበር። ፕሮግራሙ ኤርትራ ውስጥ ለወጣቶች የሚሰጠውን የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና በማሻሻል የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እና የሥራ እድል ለማሳደግ ያለመ ነበር። ይህ ፕሮግራም በሀገሪቱ ያለውን የቴክኒክ እና ሙያ ስልጠና ለማጠናከር እንደቻለ የስዊትዘርላንድ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማይክል ስታይነር ለስዊዝ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ይሁንና ኤርትራ ውስጥ ያሉት የግል ኩባንያዎች እና የሥራ አማራጮች ውስን በመሆናቸው በሀገሪቱ የሥራ እድል የተፈጠረው ተፅእኖ የተገደበ መሆኑን ቃል አቀባዩ ገልፀዋል። የእርዳታ ፕሮግ...

"በዩኤስ ኤይድ የሚደገፉ የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሀብት እና ገንዘብ እንዳያስተላልፉ ተከለከሉ" BBC

  በዩኤስ ኤይድ የሚደገፉ የኢትዮጵያ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሀብት እና ገንዘብ እንዳያስተላልፉ ተከለከሉ https://www.bbc.com/amharic/articles/cx2pwngd20lo እንዳያስተላልፉ ተከለከሉ ከ 47 ደቂቃዎች በፊት «የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ እና ከአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት (USAID) የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ያለ ባለስልጣኑ " ግልፅ ፈቃድ " ሀብት እና ገንዘብ እንዳያስተላልፉ እንዲሁም እንዳይሸጡ አሳሰበ። ይህንን ማሳሰቢያ በሚተላለፉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ እርምጃ እንደሚወስድም ባለስልጣኑ አስጠንቅቋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን የመከታተል እና የመቆጣጠር ስልጣን ያለው ተቆጣጣሪ መሥሪያ ቤቱ ይህንን ማሳሰቢያ የሰጠው ማክሰኞ ጥር 27/2017 ዓ . ም . ባወጣው " አስቸኳይ መግለጫ " ነው። የባለስልጣኑ መግለጫ፤ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅትን የእርዳታ የማቆም ውሳኔ የተመለከተ ነው። ባለፈው ወር ሥልጣን የያዙት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያሳለፉትን ትዕዛዝ ተከትሎ የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት በዓለም ዙሪያ የሚሰጠውን እርዳታ እና ድጋፍ አቁሟል። የትራምፕ አስተዳደር ተቋሙን በሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ሥር ለማድረግ ማቀዱም ተገልጿል። አሜሪካ በአውሮፓውያኑ 2023 በጀት ዓመት ብቻ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለተለያዩ ሀገራት የ 72 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ አድ...

"ኬንያ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች" BBC

ምስል
  ኬንያ በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች  https://www.bbc.com/amharic/articles/c5yvrn3jrero   የኬንያ ፖሊስ ምክትል ዋና አዛዥ ጊልበርት ማንጊሲ ከሌሎች የጸጥታ ኃይሎች ጋር ከ 6 ሰአት በፊት "ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር በምትዋሰንበት የድንበር ግዛቶቿ ላይ ባሉ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ታጣቂዎች ላይ ያነጣጠረ ወታደራዊ ዘመቻ መጀመሯን አስታወቀች። የኬንያ መንግሥት የጦሩ አባላት ተደብቀውባቸዋል ባላቸው የማርሳቤት እና ኢሲዮሎ ግዛቶች ላይ "ወንጀለኞችን ማስወገድ" የተሰኘ ከፍተኛ የፀጥታ ዘመቻ ባለፈው ወር፣ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም. መጀመሩን ገልጿል። እነዚህ የሰሜን ኬንያ ግዛቶችን ታጣቂ ቡድኑ "ድንበር ዘለል የወንጀል ድርጊቶችን ለማሳለጥ የሚጠቀምባቸው ናቸው" ሲል የኬንያ መንግሥት ብሔራዊ የፖሊስ አገልግሎት ሰኞ፣ ጥር 26/2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ወንጅሎታል። የኢትዮጵያ መንግሥት በሽብር ቡድንነት የፈረጀው እና "ሸኔ" እያለ የሚጠራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በኬንያ ግዛቶች ውስጥም ሕገወጥ የማዕድን ማውጣትን ጨምሮ ሌሎች ሕገወጥ ድርጊቶችን እየፈጸመ ነው ስትል ኬንያ ወንጅላለች። የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ ቡድኑን "በተለያዩ ሕገወጥ የጦር መሳሪያ፣ አደንዛዥ ዕጾች ዝውውር፣ ሕገወጥ የማዕድን ማውጣት፣ የሰዎች ዝውውር ንግድ ተሰማርቶ ይገኛል" ብሎታል በመግለጫው። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት "ለገንዘብ ሲል እገታዎችን በመፈጸም እንዲሁም ድንበር ዘለል ወረራዎችን በማካሄድ እና በጎሳዎች መካከል ግጭቶች እንዲቀሰቀሱ በማድረግ ለኬንያ የብሔራዊ ደኅንነት ከፍተኛ ስጋት" ሆኗል ሲል ፖሊስ ጠቅሷል። የኦሮሞ ነጻነ...