ልጥፎች

ከጃንዩወሪ 22, 2020 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዲስክርምኔሽን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት።

ምስል
እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ። የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዲስክርምኔሽን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት። „ኃጢያት ብተሰሠራ ምን ትጎዳዋለህ? መተላለፍህስ ቢበዛ ምን ታደርገዋለህ?“ (መጽሐፈ እዮብ ምዕራፍ 35 ቁጥር 6) ሥርጉተ©ሥላሴ Seregute©Selassie 21.01.2020 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ይድረስ ለኢትዮጵያዊው ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ፤ አዲስ አበባ። ግልባጭ ለ ዶ / ር ዳንኤል በቀለ  - የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን - ኮሚሽነር፤ አዲስ አበባ። ·         ልዑል እግዚአብሄር ለጥያቄዬ ተደማጭነትን ይሰጠው ዘንድ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ይህን ጥቅስ ላጠይቅለት። „ከግፍ ብዛት የተነሳ ሰዎች ይጮኃሉ፣ ከኃያላን ክንድ የተነሳ ለእርዳታ ይጠራሉ።“ (መጽሐፈ እዮብ ምዕራፍ 35 ቁጥር 9) እንሆ በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ውሳኔ የቅድሰት ድንግል ማርያም ፍቅር በጭነት ዚታ መኪና በድፍጠጣ በበላዩ ላይ ተሄደበት። እግዚኦ! ማህከነ! ተሳህለነ! ·         በ ር። እንዴት ናችሁ የአገሬ ቅኖች - ቅኔዎች? ደህና ናችሁ ወይ? ትንሽ የንፋስ ሽውታ በቀዝቃዛ ርጥበታማ አዬር፤ ጭሮሮ ሆነው መለመላቸውን የቆሙቱን እጽዋት ባልስ መሰል ዳንስ ያሠለጥኑታል። ግራጫማ ጭስ መሰል የሰማይ ትንፋሽ የአዬሩን ውቅያኖስ በስሱ ይቀዝፈዋል። ልዕልት ጠሐይም በልግመት ብቅ ብላለች - እንደ ነገሩ። ለ ብ ታን እንኳን ነስታ። በዚህ ማህል ጉርብጥብጥ ብሎኝ ስለሰነባበተው እስካንዳንብያ አገር ያለ የሚመስለው የኢትዮጵያዊ ብሄራዊ   የምርጫ ቦርድ ንጹህ ዲስክርምኔሽን በቁስልት የመገለውን ዕንባዬ ጋር መክረን ልንልክለት እንሆ ወሰን። የቁስለት መግል በብልቂያጥ