ልጥፎች

ከጁላይ 13, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የበቀል ሞት!

ምስል
· ፎሪን ጠ/ ሚር አብይ አህመድን ሰብዕና አላወቀውም ወይንም አላጠናውም። „ ከአፌ ቃል ፈቀቅ አትበል።“ (ምሳሌ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፭) ከሥርጉተ ሥላሴ 14.07.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላድን።)       መነሻ። ስለፎሪ https://www.youtube.com/watch?v=Qrd5D12Z8hw awaze news ን ካነሳሁኝ ፎሪን ለአማራ ተጋድሎ የሰጠው ዕውቅና እና ክብር እጅግ አስደስቶኛል። በቃ „የነፃነት ሃይሉ“ የፉከራ እና የቀረርቶ ሞገድ ተንሳፎ የብል ራት ሆኖ ቀረልኝ። ተመስገን! ወደ ቀደመው ምልሰት ሲሆን … ዛሬ ጥዋት አዋዜን አዳመጥኩት፤ እናም ይህን መልስ ከስሩ ለጠፍኩኝ። ምን አልባት ታዳሚዎቼ ካለነበባችሁት፤ ካላገኛችሁት ብዬ በድጋሜ ብሎጌ ላይ መለጠፍ ግድ  አለኝ።  በዚህ የዓለም አቀፉ አንጋፋ ጋዜጠኛ ትንተና ላይ ከግላዊ ስሜት በፍጹም ሁኔታ የራቁ ግን የነጠሩ እና የበለጡ እጅግ ብልህ የሆኖ የኢትዮጵያን ፖለቲካው መንፈስ በውል የመረመሩ ጉዳዮች ተነስተዋል። ጋዜጠኛ እንደዚህ ነው መሆን ያለበት። ከስሜት ርቆ ግን ፋክቶችን ፈልፍሎ አቅጣጫ ማመላከት፤ ቅን ጉዳዮች የበለጠ እንዲበረታቱ መሠረት ያለው ተግባር መከወን። እንጂ የራስን ስሜት በሚገፋ ስጋውን እንደተነሳ ውሻ የህዝብን መንፈስ ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ የሚመሩ ጫሪ ፤ ቆስቋሽ መንፈሶችን እያነካኩ ማቆሳሰል አይደለም። ከሁሉ በላይ አሁን ያለንበት ዘመን መሪ ያለበት ዘመን ነው።  መሪ ነኝ ለሚለውም ተፎካካሪ ፓርቲ ሁሉ መሪ አልባ ሆኖ የኖረበት ረግረጋማ ጨቀጨቆች ተወግደው ጥርት ያለ ብሩህ የስውኛ መስመር የተዘረጋበት ነው … በተለመደው ዙረህ እቀፈኝ የመገዳዳል የመበቃቃል የቁርሾ ጠጅ መልስ እና ቅልቅል ያከተመበት አዲ

የአማራ ተጋድሎ አንበሶች ድላቸው ያለው በብአዴን ውስጥ ነው።

ምስል
ገዱ ገድ ወይንስ መንገድ? „አንተ ታካች ወደ ገብረ ጉንዳን ሂድ  መንገዳዋን ተለምክተህ ጠቢብ ሁን።“ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፮ ቁጥር፮) ከሥርጉተ ©ሥላሴ 13.07.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) ቁም ነገር  ይሄ የለውጥ አብዮት ቢቀለበስ የመጀመሪያ ተጠቂዎች የቄሮ እንበሶች እና የአማራ የማንነት የህልውና ታግድሎ  አንበሶች ናቸው። ይህን ከልብ ማድመጥ ያሰፈልጋል። ለዚህ አብዮት ቄሮ እና የአማራ ታገድሎ ወታደሩ፤ የደህንነት ሰራተኛው መሆን ይኖርባቸው። ገዱና እና ለማ ኢህአዴግን አፍርሱ የነበረው ዘመቻ እኮ ታጋድሎዎቹ ተቀብረው፤ ታሪኩም ድሉም ለሌላ ሥጦታነት እንዲቀርብ የታሰበ ነበር። ስለዚህ እንደ ጎንደሮች "ልብ  ያለው ሸብ ነው!"  ·        ውሃ ቀጠነ። በሰሞኑ በብአዴን ጉባኤ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በተናገሩት ላይ ትርምስ ተፈጥሯል። የተደገፈውን መንገድ ውሃ በቀጣነ ቁጥር እዬቀጣህ እና እዬቀጠቀጥክ አይሆንም። አሁን እኮ የእነ ገዱ መንፈስ ተጋድሎ ላይ ነው። መከራ ውስጥ ነው። እያንዳንዷ ደቂቃ ውጪ ግቢ ነብስ ነው።  ወያኔ ሃርነት ትግራይ አይደለም በፊትም ዛሬም እያመሰ ያለው የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ ሎሌ ለመሆን የፈቀደው አማራ፤ አፋር፤  ሲዳማ፤ ሆዳሙ ፤  ከምባታ፤ ሆ ኢትዮ ሱማሊያ ሃድያ፤ ጉምዝ ነው ወዘተ ወዘተ ጠላትማ ጠላት ነው ይታወቃል ውሎውም አድርሻውም። በወዳጅ ሥም የተጠጋው ነው ለጥቃት ለሽንፍት የሚዳርገው። ብአዴን እኮ አሁንም እነ ሳጅን አለምነህ መኮነን ተሸክሞ ነው ያለው። ይቻለዋል ቦታውን ማስለቀቅ፤ ምክንያቱም ህዝብ ለሰከንድ እሳቸውን ማዬት እንደማይፈቀድ አሳምሮ ያውቀዋል። ስለዚህ እነኝህን የተሸከመ ብአዴን ችግሮቹ አልቃዋል ማለት አይቻል

አብን ለፕ/ መስፍን ወልደማርያም መንፈስ ይሰግድ ይሆን?

ምስል
የአብን እጮኝነቱ ለማን ስለማን? ከሥርጉተ© ሥላሴ 13.07.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ) „ልጄ ሆይ ተግሳጽን አትናቅ፤“ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፩) የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አመራር አካሉን መሪ በጊዜያዊነት መርጧል ዶር ደሳለኝ ጫኔ ነገ ግን አይቀጥልም። "የባዶነት፤ ዬየለመነትን" የፕ/ መስፍን ወልደማርያምን የጡት ልጅ ሰማያዊ ፓርቲን ካስጠጋ ... ለነገሩ ጥርጊው ...  ሰማያዊውም ጊዜያዊ ሊቀመ ነበር አቶ የሺዋስ አሰፋ አሉ አሁን በሊቀመንበርነት ነገ ግን አይቀጥሉም። መንገዱ የዱራኛ ነውና! ቀደም ብዬ በዚህ ጉዳይ ላይ ጽፌያለሁ። ዛሬም እደግማዋለሁኝ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ የራስ ተሰማ ናደውን ሚና ለመጫወት ዘብርሃነ ኢትዮጵያን የእቴጌ ጣይቱን የግዞት ዘመን በምልሰት ዳግም ነፍሷን ለጥቃት እጅ ሊያሰጥ ወይንስ ለአማራ ሊቆም? ይህ ከሆነ ከሰማዬዊ ፓርቲ ትራፊ ስለምን አሰኘው? ለዛውም ቁልፍ ቦታው የተሰጠው የድርጅት ጉዳዩን ለሰማያዊ ፓርቲ መንፈስ ነው። አቶ ጋሻው ምርሻ የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ(የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበረ) እንዲይዙ የተደረገው ከሰማያዊ ፓርቲ መጡ ለሚባሉት ሰው ነው። ህምም እምም ነው። ይህን ጊዜ ብዙ ንቃቃት ተፈጥሯል ልክ እንደ ደረቀ የዋልካ ጭቃ። ይህ መንገድ አንድነትን ፍርስርሱን አውጥቶ ታሪክ አልባ ያደረገው አሰቃቂ ድራማ ነበር። አንድነት ዶር. ነጋሶ ጊዳዳን፤ አቶ ሰዬ አብርሃምን፤ አቶ አስራት አብራሃምን በመጨረሻ አቶ ሃብታሙ አያሌውን ሳይቸግር ጤፍ ብድር የድርጀትን መርህ እዬጣሰ በበር በሰበር መርህ አሰገባ፤ ቀዩን ምንጣፍ አንጥፎ እልል ኩልልል እያለ መንበሩን አስረከበ። ራሱን ቀብሮ እንደ እናት ድርጀቱ እንደ ቅንጅት መራራ ስንብቱን ተጎነጨ።