ልጥፎች

ከኖቬምበር 7, 2023 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ዋናውን ሚስጥር ነገሩኝ!#spiritual #rural #areassacred #songs #spiritualgrowth ...

ምስል

ዬነገረ ዶር ለገሠ ቱሉ መንገድ ሌሎቻችሁ ትማሩበት ዘንድ ነውና አትበሳጩ። #ፋኖ ለአማራ ህዝብ ቀይ የደም ሴላችን ነው። ይህ ዛሬ የተፃፈ አይደለም የታገልኩበት መሥመሬ ነው። ዛሬ ጄኒራሉ በርከትከት ሲል ከፍሬ መልስ በጎደለ ላይ ማተኮር የስንዱዋ ሥርጉትሻ አነባቢ መንገዷ ነው።

ምስል
ዬነገረ ዶር ለገሠ ቱሉ መንገድ ሌሎቻችሁ ትማሩበት ዘንድ ነውና አትበሳጩ። #ፋኖ ለአማራ ህዝብ ቀይ የደም ሴላችን ነው። ይህ ዛሬ የተፃፈ አይደለም የታገልኩበት መሥመሬ ነው። ዛሬ ጄኒራሉ በርከትከት ሲል ከፍሬ መልስ በጎደለ ላይ ማተኮር የስንዱዋ ሥርጉትሻ አነባቢ መንገዷ ነው።      "አቤቱ ታድነኝ ዘንድ ፍቀድ፤ አቤቱ እኔን ለመርዳት ፍጠን።" (መዝሙር ፴፱ ቁ ፲፫)     #ዕፍታ ። ዬሰሞንን የዶር ለገሰ ቱሉን ንግግር አደብ ገዝቼ አዳመጥኩት። የመልስ መልስ ለመስጠት አይደለም ቁም ነገሩ። ተያያዥ ጉዳዮች ወፍ ካወጣቸው ላነሳቸው እችላለሁኝ።   በኽረ ጉዳዬ የ፬ ኪሎ መንበር የምታልሙ፤ ይህም ባይሆን በተለያዬ ምክንያታዊ ገጠመኝ ህዝብ እናነቃለን፤ ባለፈም ህዝብ እንመራለን፤ እንዲያም ሲል ኮኦርድኔተር ነን፤ እንዲሁም አቅጣጫ ነዳፊ ነን የምትሉ ሁሉ ምን ተማራችሁበት ከዚህ መሰል ወጣ ገባ፤ ጠራጠሮ ሰብዕና፤ ከዚህ መሰል የኃላፊነት ቦታ ካለ የኢትዮጵያን አንደበት ከወከለ ሰው????   በመሪነት ላጫችሁ ይሁን ለታጫችሁ ሁሉ በዶር ለገሰ ቱሉ ቦታ እራሳችሁን አስቀምጡ እና እኔ ብሆን ብላችሁ እራሳችሁን እስኪ መዝኑት። እኔን አይመለከትም። ከዬትኛውም ተቋም ይሁን ተጽዕኖ ፈጣሪ ጋር ግንኙነት ዬለለኝ፦ በመቆጠብ እና እራስን በመግዛት ለራሴ ጥሪ፤ ለተፈጠርኩበት መልዕክት የምታትር ባተሌ ነኝ እና። ዕውቅናው #አይገጠግጠኝም ። #ውዳሴውም #አያሻቅለኝም ። ለዬትኛው የኃላፊነት ቦታም እራሴን አጭቼም አስቀምጬም አላውቅምና። #ሂደት እና ግጥምጥሞሹ። ዶር ለገሰ ቱሉን እያዳመጥኩኝ አሁን መድረክ ላይ፤ ሚዲያ ላይ ያሉትን ወገኖቼን ሁሉ በዕዝለ ህሊናዬ ሳስስ ነበር። ምክንያቱም የዚህ መከረኛ ባለቤት አልቦሽ ትውልድ ሮል ሞዴል ምንጩ፤ አቅጣጫው ውሉ ስለሚጠፋኝ።  

ሰማዕታት!!! የምስራቅ ፋኖ! 07.11.2022

ምስል
  ሰማዕታት!!! የምስራቅ ፋኖ! ይህ ሁሉ መገበር እና ትርፋን? የጀግኖች ውሎ እና ቀሪ የቤተሰብ ተስፋ???? ምን እና ምን፣ እንዴት እና እዴት ይሆን፣ ይኳኋን ይሆን?????? ፦፦፦፦፦ ይህ በጀግና መሬ ወዳጆ የሚመራው ብቻ ነው ሊስቱ። ከነሃሴ 18/2014 አስቸጋሪ ቦታወችን ጥሰው በመግባት በሦስት ቀን ብቻ 45 ባለፋት ሁለት ወራት ብቻ ከ75 አባላት በላይ ሰማዕትነትን ሲቀበሉ፣ የቆሰሉ፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውም አሉ። ይህ የምስራቅ ፋኖ ብቻ እንጂ በጠቅላላ በዬጎበዝ አለቃው፣ በከፍተኛ መሪወች የሚመራውን አይጨምርም። የሆነ ሆኖ ሁለት ዓመት ሙሉ ሁለመናውን፣ መኖሩን የገበረ ቀጣይ ተስፋስ?????  

Die schreckliche Dunkelheit in der Stadt Nekmet in der Wolga Ormiay Region. 07.11.2022

ምስል
  • Die schreckliche Dunkelheit in der Stadt Nekmet in der Wolga Ormiay Region. #Mein Vorwort ist mit tiefer Traurigkeit...   Keine ausländische Regierung konnte den Sorgen der Amhara-Mütter Tränen standhalten. aber wieso? Manchmal fehlen einem die Worte, um seine Trauer auszudrücken. Ich habe heute Nacht nicht geschlafen. Ich habe die Fähigkeit verloren, meine Trauer zu schreiben. • Amahar Genozide ist weiter … und weiter …. Die ununterbrochenen Genozide der Amhara geht in Oromiay weiter. Eine Amhara-Mutter wurde in ihrem Haus mit ihren sechs Kindern in der Arsi-Zone in Jegue (Menbere - Hiyote Keblia oder Gemeinde) getötet. Weitere 9 Amhara-Eingeborene wurden brutal getötet. Vor einigen Tagen wurden 5 Amaras Stamm in einem benachbarten Ort in Addis Hiwet Gemeinde getötet. Inzwischen wurden in der Region Welga Tole Gemeint erneut Tausende Menschen getötet und weiter wieder 300 Amara-Leute vertrieben. (Der Bericht stammt von Heber Radio.) • Die schreckliche Dunkelheit in der

ዬአማራ እናት ከስድስት ልጆቿ ጋር ተገደለች። 07/11/2022

ምስል
  ዬአማራ እናት ከስድስት ልጆቿ ጋር ተገደለች።     ዬአሪሲዋ ሁሩርታም አዬሯ በስጋት እዬተናጠች ነው። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" እያዘንኩ ነው እምጽፈው። በጢቾ ሮቤ መስመር ሌሊቱን ሁሉ ስትሄዱ ብታድሩ ምንም ንክች የሚያደርጋችሁ የደረቅ ወንጀል ፈፃሚ እንኳን አልነበረም። አይደለም የአማፂ ድርጅት አባላት። አሁን ግን የበዛ ስጋት ሙሉ አርሲ አንዣቧል። ከተሞች ለጊዜው ሰላም ቢመስሉም የገጠር ቀበሌወች ግን ኦነጋውያን በዛው በመከረኛው አማራ ላይ ጥቃታቸውን ቀጥለዋል። አንዲት እናት ከስድስት ልጆች ጋር፣ 9 አማራውያን ከሦስት ቀን በፊት ተመሳሳይ 5 ዬአማራውያን የንፁኃን ግድያ በገበሬ መንደሮች እዬተከወነ ነው። በአርሲ ጀጁ ……በመንበረ ሕይወት፣ በአዲስ ህይወት መንደሮች። ከገጠር ጀምረው ነው የዘር ማጽዳት ዘመቻው የተወጠነው። የዘመኑ የፖለቲካ ባህሬ ተረኝነት ሲባል አይደለም ይህ እጭ ላይ ያለ የፖለቲካ ዕሳቤ ነው። አሉታዊ ዴሞግራፊ ላይ ተቀምጦ ይህ መሰል የፖለቲካ ትንታኔ አዘናጊ፣ ትጥቅ አስፈቺ፣ አልዛዢ ነው። ዘመኑ የገዳ ወረራ፣ የገዳ፣ መስፋፋት፣ የገዳ አስምሌሽን፣ የገዳ ዲስክርምኔሽን ነው በማለት አዲስ አበባን ናሙና አድርጌ አራት ዓመት ሙሉ፣ ጽፌያለሁ ተናግሬያለሁ። የችግር መፍቻ አቅም የምታመነጨው፣ የችግሩን ዕውነተኛ ፍላጎት ስታውቀው ነው። በደራሽ እና በጭፍጫፊ አጀንዳ አቅም ሲባክን ባጁ። አሁን ነገረ አማራ ተራግፎ ሙት መሬት ላይ ይገኛል። አይነ ስውራን፣ አቅመ ደካሞች፣ አረጋውያን፣ ሴቶች፣ ህፃናት ካለምንም ሃግ ባይ ሰፊ ጥቃት እዬተፈፀመባቸው ይገኛል። ለዚህም ነበር አበክሬ በተከታታይ 1) ዓለም ዓቀፍ ጠበቃ ቀጥረን መጤም፣ ሰፋሪም ከተሆነ ህግ ይበይንብን። ሪፈረንስ የኔታ ፕ/ ዶር ሃብታሙ ተገኜ፣ ዬኔታ አቻምዬለህ ታምሩ የሠሩት ጥናታዊ

#የአብሽ ቡና።

  ዕለተ ሰንበት እናትነት በቅንነት ለውስጥነት። #የአብሽ ቡና። ስለአብሽ የጀምርኩት ነበር። ዛሬ ይከወናል። ግን እንደምን አደራችሁ? ደህና ናችሁን? #አብሽ እና ቡና። አብሽን ጭልጋ ገበሬ መንደር እንደቡና ሲጠቀሙበት አይቻለሁኝ። መንደሩን አልጠቅሰውም። ቡናው እዬተቆላ አብሹ ተጨመረ። ልኩን አይተው አወረዱት። ጠረኑ ስርንቅ ነበር። ተወገጠ። ተፈላ። እኔም ታደምኩበት። በጣም ይመራል። ብልኃት ይኖረዋል። የጤና ትሩፋት። እዚህ መጥቼ የተለያዩ አገር ቡናወች ጋር እዬቀላቀልኩ ጣዕሙን ለማምጣት ሞክሬያለሁኝ። ከአንድ ኮንብኔሽን ጋር ተመሳሳይ ሆኖ አግኝቼዋለሁኝ። ያው እንደነገርኳችሁ። ቤቴ ውስጥ በዚህ መሰል ጉዳይም አተኩራለሁ። እራሴን እንደ አንድ ኦብጀክት ወስጄ ማለት ነው። ገበሬው ቡናን በጥሬጨው፣ በጣዝማ፣ በማር ወይ በባዶ ይጠጣል። ጣዝማ ከማር ይገረምማል። ይከብዳል። ለጤናም ልዩ ነው። ጥሬጨው ማህል አገር ጨው እምትሉት ነው። ከእኛ ጨው አይባልም ጥሬጨው ነው። ትክክለኛ አማርኛ ትርጉሙም ይህ ነው። ሌላ የጨው ዓይነትም አለ። አሞሌ ጨው የሚባል። ለከብት የሚሰጥ። የሆነ ሆኖ የአብሽ ቡና ጠቀሜታውን ጠይቄ ባልረዳም ገበሬወች እንደሚጠቀሙበት አይቻለሁ። በስኳርም ሆኖ እጅግ በጣም ይመራል። ቤት ስመለስ ሞከርኩት ይመራል። በዚህ ይከወን። ደህና ሁኑ። መልካም ሰንበት። ቸር ወሬ ያሰማን አሜን። #ፎቶው ከአቶ ሰንጋ ተራ ፔጅ ያገኜሁት ነው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 07/11/2021 ኑሩልኝ። አሜን።

07.11.2021#የአማራ ማዕልቱ አልተፀነሰም።

  #የአማራ ማዕልቱ አልተፀነሰም። ማዕልት ቀንና ሌሊት ማለት ነው። #ወጥ አማራ የተፎካካሪ ፓርቲ የቦርድ ሰብሳቢ፣ የድርጅት ማናጀር፣ ሚኒስተር፣ የበጎ ሰው ተሸላሚ ዓይናችሁ አይቷልን? ስለዘኔወማስሬ መልካም ዜና ከሐበሻ ዩኒቲ አዳምጫለሁ፣ አጭር መልዕክት ነው። አብይን ያመነ ጉም የዘገነ ነው። በዛ ስፈላሰፍ ነበር ያደርኩት። ተስማምተዋል ይላል ዘገባው። ከሆነ ጥሩ ነው። "በሬ ሆይ" እንዳይመጣ። አንድ እግር ዱር ቤቴ አንድ እግር ከተማ ይሁን አማራን መሪ አልባ ማስቀረት የግንቦትወአብይዝም ታላቁ የዘመኑ ፕሮጀክት ነው። የኢህአዲግ የግንባሩም ተፎካካሪ የሚባለውም ሊሂቁ የተነካ የለም ሲሾም ሲሸለም፣ የበጎ ሰው ሽልማት ሲሰጠው፣ የቦርድ አባል ሲሆን፣ ሚኒስተር ሲሆን ድርጅቱ ዕውቅና ሲሰጠው፣ በዶላር ሲደጎም፣ የዲፕሎማሲው ማህበረሰብ እንዲያውቀው መድረክ ሲመቻችለት አይተናል። አስተውለናል። ይህን ዕድል በርቁቅ መንገድ ያገኙትን አይተናል። የአማራ ሊሂቃን ሲሳደድ፣ ሲታሰር፣ ሲታገት ይህ ነው እንቅልፍ ነስቶኝ ያደረ። ለምን? አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣ አቶ ኃይለማርያም ደሴ ይንጎራደዳሉ? የቀደሙት የብአዴን ሹመኞች ከሥልጣን ገሸሽ ተደርገው አሉ እነ ገዳ ንጉሱ ጥላሁን እነ አቶ አዲሱ ወዘተ …… ዶር አንባቸው መኮነን የምስጥ ሲሳይ ሆኗል እስከ ቲሙ። ሁለት አባል ያለው የዶር አረጋይ በርሄ ፓርቲ በዕውቅና የአባይን ፕሮጀክት ይመራል። አቶ እስክንድር ነጋ ለ12 ጊዜ ከቲሙ ጋር ታስሮ ካልገደልነው ብለው በተራ ወንበዴ እዬተገለገሉ ነው ዶር አብይ አህመድ። 20 ዓመት ተደራጅቶ አዲስ ኃሳብ በማፍለቅ የማይታክተው፣ ግን በጠራራ ጠሐይ የሚዘረፈው የኢትዮጵያ ዕድል ፈር ቀያሽ የሆነው ኢዴፓ ዲስማንትል ሆኖ የዶር በዬነ ጴጥሮስ ፓርቲ ተሹሞ ድርጅቱ ቀጥሏል። ጫካ የነበረው

Nob 07.2020

  የህሊና ሥልጣኔ ምን ያጎናፅፈኛል ብለህ ስታስብ። አዲስ ዘመን። አዲስ የኃይል አሰላለፍ። አዲስ ተስፋ። አዲስ ቀን። አዲስ ቀለም። አዲስ አስተሳሰብ። አዲስ ራዕይ። የብሥራት ዜና። አዲስ መንገድ ይህ የሰለጠነው ዓለም ያገኘው ፀጋ ነው። ስክነቱ - ከፍታ። የታቆረው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወንበርን ካጨህ ዕለት ጀምሮ አዲስ ግድያ። አዲስ ቀውስ። አዲስ ሴራ። አዲስ ሸፍጥ። አዲስ አድማ። አዲስ ድቀት። አዲስ ድርመሳ። አዲስ በቀል። አዲስ ፍርሰት። አዲስ ቅጥፈት። አዲስ ዘረፋ። አዲስ ነቀላ። አዲስ የቅናት እብጠት። አዲስ መታበይ። ስክነቱ - ቁልቁለት። ኢትዮጵያ በአዲሱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ተስፋዋ በተለይ በአባይ ፖለቲካ የተሻለ ይሆናል ተብሎ ይታሰባል። ትውልደ ኢትዮ አሜሪካውያን ከቁንጮ ኮኦርድኔተር ጀምሮ ደክመዋል። ድካማቸውን ፈጣሪ ሰምቷል። ተመስገን። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie የናፈቅከኝ ዴሞክራሲ መቼ ትመጣ ይሆን?!

Nob 07.2020 ብዙ ከስረህም ቢሆን ትንሽ ለማትረፍ ተንቀሳቀስ።

ምስል
  ብዙ ከስረህም ቢሆን ትንሽ ለማትረፍ ተንቀሳቀስ።   ዘላቂ እርስትህ ቢመለስ አማራ ትልቅ ትሆናለህ። ይህን ደግሞ ዬአብይዝም ፕሮጀክት ያስፈነጥረዋል። አማራ የሚባል ኃይለ ቃል ያውከዋል። ዋጥ አድሮጎ ይዞት እንጂ ያስጎራዋል። አማራ ሲባል ጆሮውን ቅርቅር አጅሬ የዋዛ። ቢያንስ። አዎን ቢያንስ ግን በባዶ 6 በህወሃት ጭካኔ ከምድር በታች የተቀበሩትን አስለቅቅ ፌስታህ የሳሙና አረፋ ሆኖ ተኩረፍርፎ ሳያልቅ። በአፍላው እኔ ተናግሬያለሁ። እመነኝ አልልህም። … ነገ ብዙ ቁምነገር ጭብጦችን ይዞ ስለሚጠብቅህ። ገዳ መርሁ ክህደት ነው። በአማራ ተጋድሎ፣ በብአዴን ሙሉ ድምፅ፣ እጩ ጠቅላይነትን አሳልፎ ሰጥቶ "ትምክህተኛውን በሰበሩን ቦታ ሰብረን የአገሪቱን ዋና ከተማ ተቆጣጥረናል" ያለህን ጠብደል ካህዲ ኦህዴድን እሰበው። ሰቲት የገዳ ዲታወች መዋኛ ትሆናለች። መተማም እንዲሁ። ቋራም ማጠቢያ እንዲሁ። የጎርጎራ እጮኛነት በሚመለከት ከወረራው ሰርግና መልስ ትራፊ፣ ቅንጥብጣቢ ካገኜህ ዕድለኛ ነህ። ሌላው ተረኛውን አድብተው በእጥፍ አማራን ገቢ እስኪያደርጉ ድረስ ለደመህ ዋጋው እነዛን ምንዱባን ባይሆን አስፈታ። እግረ መንገዴን የምነግርህ ትጥቅህን ይዘህ ስለቀረብክ ትጥቅ በጀምላ እንደሚያስፈቱህም እሰበው። ያው እግረ መንገዴን ልንገርህ ብዬ ነው። ወደ ቀደመው ስመለስ ምን አልባት ከ40 ዓመት በላይ የታሰሩ ከዛው ከምድር በታች ጉድጓድ ውስጥ የተቀበሩ ወገኖችህ ጋር ትገናኝ ይሆናል። ማን ያውቃል? በነገራችን ላይ በኢትዮጵያዊነታቸው የፀኑ ተጋሮዎችም የፅዋው ተጋሪዎች ናቸውና ለእነሱም ብርኃን ብልጭ ትላላቸው ይሆን እያልኩ አስባለሁ። ህወሃትን ተገላግለው ለገዳ ማደር ግን የማይቀር ዕጣ ነው። በግራኝ ዘመንም፣ በ16 መቶ ክ/ ዘመንም ድቀት ያልደረሰባት እቴጌ ትግራይ

Nomb 07.2020 ኦ! አትፍረድ።

ምስል
  ኦ! አትፍረድ። ኦ! ፈጣሪ ሆይ እነኛን ቀንበጦች ጠብቅልን። ህይወታቸው ከጨካኞች ታደግልን። አሜን። አንድ ፎቶ አዬሁ። ፎቶ ሾፕ ይሁን፣ ምኞት ይሁን አላውቅም። ከሆነም ምንም የሚያስወቅስ የለውም። በሰው እጅ የወደቀ ከመታዘዝ ውጪ ሌላ ምርጫ የለውም። የተወካዮች ምክር ቤት በማን ሥር ነው? ስለምን አንደመርም ያሉ የአማራ ሊቃናት ለኮሮና ሞት ተሰጡ? አሁን ቁንጮ ላይ ነው ነገ ወደ ታች ወርዶ አልደመርም ያለሁሉ ካቴና፣ ባሩድ ይበላዋል። ገዳ ውሎው ይኽው ነውና። አትፍረድ ይፈረድብኃል። ነውም አይደለም ሙግት አያስፈልገውም። ወቀሳም ነቀሳም አያስፈልገውም። ፈጣሪ የፈቀደውን እንደሚያደርግ ማሰብም ይገባል። እንደ ታሪክ ተመራማሪዎች እኮ ዛሬ ኦሮምያ የተባለው ክልል በገዳ ወረራ የተያዘ ነው። ኗሪውን አስገብረው ቋንቋውን ብቻ ሳይሆን ማንነቱን ገልብጠው ከሰው በታች አድርገው እንደሚገዙት ይታወቃል። ብዙ ነገር አልገባን አለ እንጂ የባህርዳሩ ሰማዕትነት ይህን ነው የሚነግረን። ባህርዳር ለገዳ ገብራለች። የቀረችው ተገዳዳሪ እቴጌ ትግራይ ነበረች ኦፕሬሽኑ እንደተጠናቀቀ ይሰማኛል። ህገ መንግሥት የማክበር የማስከበር አይደለም። በህግ የተሠራ ነገር ስላላዬሁ። ህጋዊ መዋቅሩን እራሱ ገዳ አይፈልገውም። ለዲፕሎማሲው ማህበረሰብ አሳቻነት ብቻ ነው ተልዕኮው። ህግ ማስከበር ሳይሆን ለገዳ ማስገበር እንጂ። ደቡብም የገበረው ሲዳማ ክልል የሆነ ዕለት ነበር። አፋር መሪ ይኑረው አይኑረው አይታወቅም። ጋንቤላ ፈንጅ እንደዋጠ ነው። ቤንሻንጉል ህብረት የፈጠረ ነው ብቸኛ ፕሬዚዳንቱ ያልተቀዬሩበት ክልል ነው። አመራሩም በዬጊዜው ተጨፍጭፏል። ሱማሌ ከሦስት ተሸንሽና ሙሽርነቷ ያከትማል።    የአዲስ አበባ ወረራም ይህው ነው። የጌዲኦ ታሪክም ይኽው ነው። ቀስ እያለ በመንግሥት ይፋዊ ንቅናቄ የሚሟላ

ወጣት አቶ ፋሲል ጌትነት ታረቀኝ ያያችሁ የሰማችሁ? Nomber 16.2020

ወጣት አቶ ፋሲል ጌትነት ታረቀኝ ያያችሁ የሰማችሁ? ይህ ወጣት ፋሲል ጌትነት ታረቀኝ ይባላል፣ ይህ የሚያሳሳ ቀንበጥ ወሮ ቀለቤ ሥዩም ስትታሰር ታፍኖ የተሰወረ ነው። ለቀለቤ ዋርሳ ነው። ዋርሳ ማለት የባለቤት ወንድም ማለት ነው። እናት አለው። እኒህ እናት ትክን ብለው፣ ኩርምት ብለው ደጅ ደጁን ያያሉ። ይመጣልኛል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ። ያ ባዕት ተፈጥሮው ለአማፅያን ምቹ ስለሆነ የመጣ የሄደው ሁሉ የሥልጣኑ ማርጊያ በዚህ ባዕት የደም ፍሳሽ ነው። አሁንም መቀጠሉ ማህፀንን እንደ ዱባ ይቀረድዳል። የሁላችን ወላጆች ወለዱን ማድረግ ቀርቶ ድምፃችን እንደራቃቸው፣ ዓይን ላይን ሳንተያይ መለያዬት ነው። የልጅ እና የእናት ፍቅር እንዲህ ሳይገናኝ ዘመን ይሸኛል በባዕተ ጎንደርዬ። የሚገርመው ጠቅላዩ በጥርሱ የያዙትም ይህን ባዕት ነው። ከዚህ ባዕት ልጅ ብቅ ብሎ እንዲታይ አይፈለገም። አጨዱት። ሰው መስለውኝ እንዲህ እንደ ባሎን ቅትት ሳይሉ፣ ሞድ ቤት ሳይከፍቱ የኦህዴድ የፅህፈት ኃላፊ ሳሉ ዘርዝሬ ፅፌላቸው ነበር የጎንደር እናትን የመከራ የውኃ ልክ። ትርፋ ቅጣት ሆነ እንጂ። የሆነ ሆኑ ይህን ወጣት ያለበትን ሁኔታ የምታውቁ እባካችሁ እናቱን በቃሽ እንባ በሏቸው። የከፋም ነገር ካለ ንገሯቸው። ሽዋ ውስጥ የተሰወሩ የአንድ ቤተሰብ አራት ወጣቶች ድብዛቸው አልተገኜም። አጀንዳው የሆነ አካል የለም። ተረስተዋል። ትውልድ የማይተካው ሊቅ አቶ በዓሉ ግርማም እንዲሁ። እጅግ የሚያሳዝነው የወጣት ፋሲል ጌትነት ታረቀኝ ወንድም የትዳር አጋር የሰላም አንባሳደር ወሮ ቀለቤ ስዩም አራሷ አሁንም እስር ቤት ናት። አማቷ ስለልጃቸውም ስለምራታቸው አሁንም ጭንቅ ላይ ናቸው። የጎንደር የአማራ እናት ሁልጊዜ የልጅ ሊኳንዳ ቤት እንደተከፈተባት ነው። አሁንም የሚሞተው እሱው ነው። ለዛውም እሱን ለሚ

oct 31.2020

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ። አሜን። "የሰው ልብ መንገድ ያዘጋጃል፣ እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" ምሳሌ 16/9 የነግህ ፀሎት። 1) የተመድ ሰላም አስከባሪ ኃይል ኢትዮጵያ እንዲገባ መሻት። 2) የአማራ ክልል የከፍተኛ ተቋም ተማሪዎች ከክልላቸው ውጪ ወደ ሌላ ክልል እንዳይመደቡ መሻት። 3) በኦህዴድ ኦነግ የበቀል መሥመር እንደ ወጡ የቀሩት የአማራ እጩ ሊቃናት የደንቢደሎ ዩንቨርስቲ ተማሪዎችን መጨረሻ ለማወቅ መሻት። 4) ሰው አጥፊው የህወሃትወኦነግ ህገ መንግሥት ሙሉለሙሉ እንዲቀዬር መሻት። 5) መርዛማው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከኢትዮጵያ ይጠፋ ዘንድ መፀለይ። 6) የሥርዓት ለውጥን መሻት። ወሥብኃት ለእግዚአብሔር። ወስብኃት ለእግዚአብሔር።