Nob 07.2020 ብዙ ከስረህም ቢሆን ትንሽ ለማትረፍ ተንቀሳቀስ።

 

ብዙ ከስረህም ቢሆን ትንሽ ለማትረፍ ተንቀሳቀስ።
 No photo description available.
ዘላቂ እርስትህ ቢመለስ አማራ ትልቅ ትሆናለህ። ይህን ደግሞ ዬአብይዝም ፕሮጀክት ያስፈነጥረዋል። አማራ የሚባል ኃይለ ቃል ያውከዋል። ዋጥ አድሮጎ ይዞት እንጂ ያስጎራዋል። አማራ ሲባል ጆሮውን ቅርቅር አጅሬ የዋዛ።
ቢያንስ።
አዎን ቢያንስ ግን በባዶ 6 በህወሃት ጭካኔ ከምድር በታች የተቀበሩትን አስለቅቅ ፌስታህ የሳሙና አረፋ ሆኖ ተኩረፍርፎ ሳያልቅ። በአፍላው እኔ ተናግሬያለሁ።
እመነኝ አልልህም።
… ነገ ብዙ ቁምነገር ጭብጦችን ይዞ ስለሚጠብቅህ። ገዳ መርሁ ክህደት ነው። በአማራ ተጋድሎ፣ በብአዴን ሙሉ ድምፅ፣ እጩ ጠቅላይነትን አሳልፎ ሰጥቶ "ትምክህተኛውን በሰበሩን ቦታ ሰብረን የአገሪቱን ዋና ከተማ ተቆጣጥረናል" ያለህን ጠብደል ካህዲ ኦህዴድን እሰበው።
ሰቲት የገዳ ዲታወች መዋኛ ትሆናለች። መተማም እንዲሁ። ቋራም ማጠቢያ እንዲሁ። የጎርጎራ እጮኛነት በሚመለከት ከወረራው ሰርግና መልስ ትራፊ፣ ቅንጥብጣቢ ካገኜህ ዕድለኛ ነህ።
ሌላው ተረኛውን አድብተው በእጥፍ አማራን ገቢ እስኪያደርጉ ድረስ ለደመህ ዋጋው እነዛን ምንዱባን ባይሆን አስፈታ።
እግረ መንገዴን የምነግርህ ትጥቅህን ይዘህ ስለቀረብክ ትጥቅ በጀምላ እንደሚያስፈቱህም እሰበው። ያው እግረ መንገዴን ልንገርህ ብዬ ነው።
ወደ ቀደመው ስመለስ ምን አልባት ከ40 ዓመት በላይ የታሰሩ ከዛው ከምድር በታች ጉድጓድ ውስጥ የተቀበሩ ወገኖችህ ጋር ትገናኝ ይሆናል። ማን ያውቃል?
በነገራችን ላይ በኢትዮጵያዊነታቸው የፀኑ ተጋሮዎችም የፅዋው ተጋሪዎች ናቸውና ለእነሱም ብርኃን ብልጭ ትላላቸው ይሆን እያልኩ አስባለሁ።
ህወሃትን ተገላግለው ለገዳ ማደር ግን የማይቀር ዕጣ ነው። በግራኝ ዘመንም፣ በ16 መቶ ክ/ ዘመንም ድቀት ያልደረሰባት እቴጌ ትግራይ በዩዲት ግን ደቃለች። ምርጡ ሉባም አሁን አንበርክኮ ያስገብራታል ዕድሜ ለአብርኃምወአረጋይ።
ገዳ በትግራይ ቀጣዩ ተውኔት ነው። ከእናንተ ወዲያ ላሳር ተብለው እንክብካቤን ሲኮመኩሙ የባጁ የህወኃት ጌጦች በተራቸው ደግሞ ወህኒ እንኳን ደህና መጣችሁ ይላቸዋል። አባ ገዳ፣ አባ ዱላ በቀሉን እስኪበቃቸው ይግታቸዋል።
በዚህ ማህል ዜጋ አይደለህም ተብለህ ከዕለተ የኦዳ ንግሥና ጀምሮ የታጨድክ አማራዬ በለስ ከቀናህ ባዶ 6 አስከፍት እና ትንሽ ተንፈስ በል። ነገረ እርስት ማስመለስ? እም።
ያ መርዛማ ድርጅትን ግንቦት 7 ሽተው ሲጓዙ በህወሃት የታፈኑ ሥማቸውም፣ አድራሻቸውም የማይታወቁ የገራገሩ የአማራ ወጣቶችም ሊገኙ ይችላሉ። አማራ ሲረገም ግንቦት 7 የጎን ውጋት ተፈጠረለት።
የሆነ ሆኖ እስረኞችህን ለማስፈታት በዚህ ጉዳይ ላይ ጠንከር ብለህ ትጋ። የዘመቻው ዓላማ ተነግሮኃል ህወሃትን አፍርሶ የገዳን ብልፅግና ትግራይ ላይ መትከል ነው። ዓድዋ ላይ የመለስወአረጋይ ህልም የቀብር ሥርዓቱ ተፈጥሞ የሌንጮ ለታ ህልም ሲሳካ አይታይ ይሆን? ጠብቀው።
እግረ መንገዱን ግን ከህወሃት ጋር የተሰለፈው የኦነግ ክንፍ በእርስበርስ ውጊያው በአባ ገዳ ሉባ እንዳይነሳ ሆኖ ደቋል በተለይ የዲያስፖራው የሚዲያ አውራሪስ።
ለኦነግ ዓላማ ስኬት አብይዝምን ያህል ለድል የበቃ መንፈስ የለም። ነገ እራሱ ጊዜ ቢኖረውም ዋንጫውን ይወስዳል። ሻንፕዮን ነው። የመቃብር ስፍራው አብይዝም በስል ገብቶ ጣጥሶ ለድል በቅቷል። ይህን አትካደው።
የአመራር ድክመት ምንትሶ ቅብጥርሶ አለበት ብትል አልሰማህም። እማዬውን ነው የማምነው። አንተ ልቀህ ይህን የሚመከት ድርጅት ግን የለህም። የተደራጀ ሃሳብ እንኳን።
ሰሞኑን ታዘብኩህ ለሳሙና አረፋ ተስፋ እንደ እንቦይ ካብ ተንደህ፣ ስትፍረከረክ፣ ስትወድቅ ስትነሳ፣ ስትፈርስ ስትሰራ። በቀን ስንት የብራና ማደናገሪዬ ሰራህ? እሰበው።
ዕድሜ ለግንቦት 7፣ ለዳያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ለዶር ዳኛቸው አሳፋ፣ ለደመቀወገዱ። ተራቸው ሲደርስ ኮንቴይነር እንዲያሟሙቁ ይላካሉ እንጂ የቤተ - መንግሥቱን ሉባ አደላድለው ኢትዮጵያን አወረሱ። እሱም የልቡ ደረሰለት። ምኞቱ ተሳካለት። ለጊዜው ነው አደራ እንዳትለኝ። አንተ ምን አለህ እና?
ቀዳማይ ገባሪዎችን መረቃቸው እርገማቸው አልልህም። ኧረ ምን በውጣኝ? እናቴ በአራስ ቤቷ አላበደችም። እኔ ሥራዬ ደንገዝገዝ ያለውን ወለል ማድረግ ነው። ለዛውም አደቡን ከሰጠህ። አቅል የላይኛው ከሸለመህ።
በል ወዳጄ እነኝህን ከፍ አድርገህ ሰንደቅህ አድርገህ ፍቱልኝ በል አሁን ባፍላው። ቸኩል። ተጣደፍ። ፍጠን። ፌስታው የሳሙና አረፋ ስለመሆኑ ግን እጬጌው ሂደት ቁጭ አድርጎ ያኮመኩምኃል። ጠብቀው።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
…ኃራም ሸፍጥ!

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።