ልጥፎች

ከጁን 27, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የሰኔ 16ቱ 2010 የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ክሽፈት።

ምስል
የሰኔ 16ቱ የ2010 መፈንቅለ  መንግሥት ሙከራ ክሽፈት  እና ቀጣይ ዕጣ። ከሥርጉተ © ሥላሴ 27.06.2018  (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።) „እኔ በእድሜ ታናሽ ነኝ፤ እናንተ ግን ሽማግሌዎች ናችሁ፤  ስለዚህም ሰጋሁ እውቀቴን እገልጥላችሁ ዘንድ ፈራሁኝ።“  (መጽሐፈ ኢዮብ ምዕራፍ ፴፪ በቁጥር ፮) ·        እፍታ። ብዙ ሰው በጠ/ሚር አሜኑ አብይ አህመድ ላይ ብቻ የተቃጣ ጥቃት አድርጎ ነው የሚገምተው። አብረዋቸው የነበሩትን የካቢኔ አባላትን ሳይ እኔ በጣም የሚቀርቧቸው ከሳቸው ጋር ለመስራት ሙሉ ፈቃደኛ የሆኑትንም በአንድ ላይ ለመፍጀት እንደ ታሰበ ነው የሚገባኝ። መቼም ከጠ/ ሚር አሜኑ  አብይ አህምድ ጋር ለመሥራት ትልቁ መሥፈርት ሌት እና ቀን እንደብረት መትጋት የግድ ይላል። ይህን በቀደመው ጊዜ በሚገባ አብራርቼ ጽፌዋለሁኝ። ሰውዬው ሰርተው የሚደክሙ አይደሉም። የጸሐይ ጉልበት ያላቸው ጉደኛ ፍጥረት ናቸው። ይህን ፈቅደው በሚተጉት ላይም ወያኔ ሃርነት ትግራይ ከአቅሙ እና ከቁጥጥሩ ውጪ በላይ መሆኑ እረፍት አይሰጠውም። የትኞችንም አይፈልጋቸውም።  ·        ጥ ራት ፍጥነት ብቃት በሙሉዑነት። ገራሚው ነገር የሥራቸው ጥራት እና ብቃት ፍጥነት ስኬት በድምሩ ሲታይ ደግሞ Quality የሚባል ዓይነት ነው። የረገጡት ሁሉ ለምለም ነው። የነኩት ሁሉም የተሳካ ነው። የአሮን በትር እንደሚባለው። ይህ ደግሞ የዛሬ አይደለም። በተገኙባቸው ቦታዎች ሁሉ የተሰካ ውጤትን የሚያስመዘግቡ ናቸው። እንዲህ ዓይነት ሰዎች አሉ፤ ተራራን ንደው ለጥ ያለ ምቹ አስፓልት ለማድረግ የተሰጣቸው። ሰዉ ሳይገባው የከረመው ይሄው ልዩ የጸጋ ሚስጢር ነው። በኤርትራውያን ዘንድ ይጎዘጎዛሉ ብዬ ጽፌ ሁሉ ነበር። ያደረጉት ንግ

ሲዊዝ የእኔ ልዕልት ለቀጣይም አዶናይ ይርዳሽ! ይቅናሽ!

ምስል
ዛሬም ደጓ ሲዊዝ ለቀጣዩ ጨዋታ አልፋለች። ተመስገን! ከሥርጉተ © ሥላሴ 27.06.2018 (ከድንግሏ ሲዊዝ) „ሁሉን የሚችል አምላክ እስትንፋስ ማስተዋልን ይሰጣል“        (መጸሐፈ ኢዮብ ምዕራፍ ፴፪ ቁጥር ፰ ቁጥር) ዛሬ የሲዊዝሻ ቀን መልካም ቢሆንም መጨረሻው ላይ ድራማ ነበረው። ሲዊዝ ለሰውኛ ደግንቷ ወደር እና አቻ የላትም። ሲዊዝ ቢኖራትም ባይኖራትም፤ ቢከፋትም ደስ ቢላትም ሁሉንም በልክ የማያዝ አቅም ያላት አገር ናት። ቻይ እና ሲበዛ ቁጥብ ናት። ሲዊዝ የመልካምነቷ ደረጃ ልታይ ልታይ በማለት ሳይሆን መልካምነቷ፤ ቸርነቷ፤ ርህርህናዋ ተከድኖ ነው። ሲዊዝ ያሉ የሃይማኖት ድርጅቶች ሰው መርዳት ብቻ ነው መርኽቸው። ሃይማኖት፤ ቀለም፤ የዕወቀት ደረጃ አገር ቦታ የላቸውም። አሁን የካቶሊክ እና የፕሮቴስታት ሃይማኖታዊ ድርጅቶች ቡድሃንም እስልምናንም ኦርቶዶክስንም ፕሮቴስታንትንም ካቶሊክንም አማኝ የሆነ ሰው ሲረዱ ምንም ሳይዛነፍ ለሁሉም በእኩልነት ነው። ይሄ እጅግ የሚደንቀኝ ተፈጠሯቸው ነው። ፈርሃ እግዚአብሄር ደረጃው በላቀ ሁኔታ ያለባት አገር ናት። ሲዊዝ ውስጥ ተንጠራርቶ የሚሄድ ዲታ የለም። ዝቅ ነው። ሲዊዝ ውስጥ ለሚኖር ማንኛውም ስደተኛ በዬዕለቱ መደበኛ የሰብዕና ትምህርት ቤት ተከፍቶለታል ሳይከፍል። ደስታን በልክ መያዝን። ኑሮን ብልክ ማድረግ። ሲዊዝ ኑሮው እጅግ በጣም ከባድም ቢሆን እንደ አመላችን ከእናትም በላይ በሆነ ሁኔታ እኩል የምትይዝ አገር ናት። ከሰው ደጅ የሚያደርስ ምንም ነገር የለም። ሌላው የሚገርመኝ ሰብዕና የፈለገ ቢሆን መንገድ ላይ ጠብ ተፈጥሮ ቢዩ የሚያሳዩት የእርጋታ ሁኔታ ይደንቀኛል። ጥልቅ የለም። ያላዩ ነው የሚመስሉት። የገለልተኝነት መርኽቸው ደማቸው ይመስለኛል። ስለ በ

ወይ የኢሳት እጬጌ ለአሜኑ ለአብይ መንፈስ ደረት ደቂ ሆነ!

ምስል
ነገረ ጥበብ። ከሥርጉተ© ሥላሴ 27.06.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) „አንጀቴ ፈላች አላረፈችም።“ (መጽሐፈ እዮብ ምእራፍ  ፴ ቁጥር ፳፯) ·        እፍታ። የሲዊዝዬ የኔታወች ያውቁታል „እፍታ - ጠብታ - የወግ ገበታ - ቃና - ማዕዶት ተስፋ - እድምታ - የሎሬት ተስፋ“ የሥርጉትሻ የሚዲያዎቿ መክለፍት እንደሆኑ። ስለዚህ አንቺም በሌብነት ተጠዬቂ አለመባሌ ልብ ልክ ነው። ባይሆን ዘራፊዎቹ ይጠዬቁ። መቼም ዘራፊ እና ዝርፊ ቀን ጨልሞባቸዋል በጠ/ ሚር አሜኑ አብዩ ዘመን። መቼስ ደግፍን ስንጽፍ መከፋት እንደሌለው ሁሉ ተቃውመን ስንጽፍም ዘራፍ እንደማይባል ነው። ሳይደግፉ ቅሬታ ማቅረብ ቀፋፊ ሰብዕና ነው። በመልካሙ ነገር ደግፎ ሲጓዳል ደግሞ ለዛውም ድንበር ተጥሶ ሲመጣ ሃይ ማለት የግድ ይላል። ዛሬም መገረም እንደ ትናንቱ ሁሉ። ዲሲ በባለቅኔው ጠ/ ሚር የድጋፍ ሰልፍ ላይ ዕንባ በወረድ ወረድ ተደመመ አሉ። ወይ መድህኒተ ዓለም አባቴ? ስንት ጉድ ነው የሚሰማው ተዛሬ ላይ። የዛሬ የምልከታዬ ጭብጡ ይሄው ነው። ጥበብን ተጠዬቂ ልል።  ስለመሆኑ ጥበብ ቀን ከሰጠው አምክንዮ ጋር ወይንስ ቀንም ሰጠው አልሰጠውም  ከእውነት ጋር ነው ቤተሰብነቷ? ጥበብ ደግሞ ዘነብል ቀና? ኧረ አላመረብሽም በሏት። እንዴት ተቀለደ አሉ አይዋ እንቶኔ …   ·        እንዴታ ! ለነገሩ ተዚህ ላይስ ለጥበብ መንፈስ ቅዱስ እንዲህ ከሞቀው መጣድ ያምርብሻል ወይ ልል ነው በዛሬው ዕለት። .. ግን ያምርበታልን? ስንት ዕውነትን ስተረጋገጥ የከራረመችው የኢሳት የጥበብ አንባ አንበል … እሷ ትፈታተሽ፤ ትበርብርም … „ሚዛን ለራስ“ ነው ይላሉ ጎንደሬዎች። እንዴታ!መቼስ ጉደኛው ኦህዴድ ስንቱን ሰው ነው የፈተነው፤ የፈተለው