ልጥፎች

ከፌብሩዋሪ 17, 2026 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ሕይወት #የሚቀለው የሰው ልጅ ለመኖር #ፍላጎት ሲኖረው ነው።

ምስል
  ሕይወት #የሚቀለው የሰው ልጅ ለመኖር #ፍላጎት ሲኖረው ነው።    የመኖር #ፍላጎቱ ምኽዋር ደግሞ ሰላም።   ለእኔ ሰላም ፲፫ኛው ፕላኔት ነው።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።       ለመኖር ፍላጎት ማመንጨት የሚቻለው #በስኬት ብቻ አይመስለኝም። የተሳካላቸው ፈቅደው መራራውን ስንብት ሲወስኑ ስለምናይም /// ስለማድመጥም። ለመኖር ፍላጎት መኖር #መማርም ብቻውን፤ የመኖር ፍላጎትን ያበረታታል ብዬ አላምንም - እኔው። ለመኖር ፍላጎት አስቻይ ሁኔታ የሽልማት ብዛትም አይመስለኝም። ሽልማቱ ሲቀር ወይንም ሲቀንስ መኖር #በቁዘማ ውስጥ ሊታክት ይችል ይሆናል። የመኖር ፍላጎት እንዲቀጥል ቤተሰብ መመስረት፤ ልጆች መኖር፤ ጥሩ ቢላ ሠርቶ ምቾትን ማስተናገድ ብቻውን ለመኖር ፍላጎት መጨመር ሚና ሊኖረው ይችላል ብዬም አላስብም።   መኖርን የሚያኖረው #የውስጥ #ሰላም ፤ የከባቢ ሰላማዊ አየር፤ ከጭንቀት ጋር የማይነካካ ገጠመኝ ሲኖር የሰው ልጅ መኖርን ሊፈልገው፤ በመኖሩ ተስፋ ሊያደርግ፤ መኖሩን እንደ አንድ #በኽረ መሪ ኃይል አድርጎ ሊወስደው ይችላል ብዬ አስባለሁኝ።   #ሰላም ።   ቁልፍ ግን የሰው ልጅ ለሰላም ያለው አትኩሮቱ ቀጫጫ። የመፍትሄ ጎዳና ግን የሰው ልጅ ለሰላም ያለው አክብሮቱ ስስ። የውስጥ ሐሤት አመንጭ ሆኖ ግን የሰው ልጅ ውስጡን ያሸፈተበት። ሰላም የማሰብ አቅምን አፋፍቶ የህሊና #ብቃትን የሚያጎለብት ግን የሰው ልጅ የሚሰጠው ትዕግስት ኮሳሳ። የፍልስፍና ልቅና ገላጭነት ባለቤት ሆኖ ግን የሰው ልጅ በመቻል አቅም ጥብቆነት እንዲሰቃይ የሚደረገው።   የሰላም ጎዳና፤ ሰላሚዊ - እርምጃ፤ ሰላማዊ - ሩጫም፤ ልቅናም ይሁን ልዕልና፤...

ከአቶ ታደሰ ሞገስ ፔጅ ያገኜሁት ነው። አመሰግናለሁኝ። የእቴጌን ብልህ አመራር ያዘከረ ነው።

ምስል
        ከአቶ ታደሰ ሞገስ ፔጅ ያገኜሁት ነው። አመሰግናለሁኝ። የእቴጌን ብልህ አመራር ያዘከረ ነው።   "የጥሙ ዘበኛ" ኦገስት ዋይልድ ክፍል ስድስ" (ታዴሞ)   "​አሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን ሊያበቃ ጥቂት ዓመታት ሲቀሩት፣ በለንደን ጎዳናዎች ላይ የሚታየው ጭጋግ በፖለቲካው ዓለምም ተጋርዶ ነበር። በወቅቱ የታወቀው እንግሊዛዊ ጋዜጠኛና ዲፕሎማት ኦገስት ዋይልድ (Augustus B. Wylde)፣ ከለንደን ወደ ቀይ ባሕር ዳርቻ የሚወስደውን መርከብ ሲሳፈር፣ ወደፊት የሚጠብቀው ታሪክ የዓለምን ካርታ እንደሚቀይር አልተገነዘበም ነበር።   ​ዋይልድ ተራ መንገደኛ አልነበረም። ቀደም ሲል በምሥራቅ አፍሪካና በሱዳን በኩል በነበረው የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ ውስጥ እጁ የነበረበት፣ የቀይ ባሕርን ፖለቲካና የአቢሲኒያን ምድር እንደ እጁ መዳፍ የሚያውቅ አርቆ አሳቢ ነበር። የብሪታንያ መንግሥት "በጣሊያንና በኢትዮጵያ መካከል የሚነሳው እሳት ወዴት ያመራል?" የሚለውን ምስጢር እንዲሰልልና ዘገባ እንዲያቀርብ በስውር ዓይኑን ወደ እርሱ ጥሎ ነበር።   ​ከለንደን ተነስቶ በሱዌዝ ካናል በኩል በማለፍ፣ ቀይ ባሕርን አቋርጦ ምጽዋ ደረሰ። በወቅቱ ምጽዋ በጣሊያኖች እጅ ብትሆንም፣ ዋይልድ ግን ወደ መረብ ወንዝ ተሻግሮ የንጉሠ ነገሥቱን ግርማ ለማየት ቆርጦ ተነሳ። በአህያና በበቅሎ ጀርባ ተጭኖ፣ አስቸጋሪዎቹን የሰሜን ተራሮች እያቋረጠ፣ በኤርትራ በኩል አድርጎ ወደ ትግራይ ምድር ዘለቀ።   ​ወደ መቀሌ ሲቃረብ፣ በየመንገዱ የሚያያቸው ነገሮች ሁሉ ያስገርሙት ነበር። "እነዚህ ሰዎች እንዴት በጎራዴና በናስ ጠመንጃ ታላቋን አውሮፓዊት ሀገር ይጋፈጣሉ?" የሚለው ጥያቄ በአዕምሮው ይመላለሳል። ነገር ግን መቀሌ ሲደርስ ያየው ...

ህወሃት #ቤርሙዳ ትርያንግል ነው። ቀደምት ከተማዋ ናፍቆቴ ደብረታቦር #ጠቀራ መልበሱ ሐሤቱ ለማን ይሆን?

ምስል
  ቀደምት ከተማዋ ናፍቆቴ ደብረታቦር #ጠቀራ መልበሱ ሐሤቱ ለማን ይሆን?   ህወሃት #ቤርሙዳ ትርያንግል ነው።   "አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"       #ምዕራፍ ፲፰።   እንዴት አረፈዳችሁ ውዶቹ ውቦቹ። የሚናፍቀኝ፤ የምሳሳለት የደብረታቦር ከተማ መንደዱን ሳደምጥ በሃዘን ውስጥ ሆኜ ነው። በብልጽግና እና በህወሃት መካከል የተደረገውን ጦርነት በሠላም ሲቋጭ ተረፋልኝ ብዬ ከደብረብርሃን ጀምሮ ያሉ ከተሞችን ስዘረዝር #ደብረታቦር ከተማ አንዱ ነበር። ሙሉ ለሙሉ በህወሃት ወረራ እና የበቀል እርምጃ ህወሃታውያን ሳያሳኩት ከቀሩ ከተሞች የደቡብ ጎንደር ርዕሰ መዲና የታሪክም #ቀንዲል ደብረታቦር አንዱ ነበር።    ይህ የሰሞኑ መጥፎ አጋጣሚ የታሪክ #ጠቀራን ሳደምጥ ውስጤ አዘነ። ደብረታቦር አልባሌ ከተማ አይደለም። በጣም ነው የማውቀው። ቀበሌ መንደሮችን ሁሉ። ዝክረ ታሪኩ ዘለግ ብሎ ከሚጠቀስባቸው ከተሞች አንዱ ደብረታቦር ነው። የታሪክ ድርሳንነቱ በክብር ጥበቃ ሊደረግለት ሲገባ እንዲህ አመድ ሆኖ ማዬት ውርዴት ብቻ ሳይሆን #ውርዴም ነው። ማን ይፈጽመው ማን አላውቅም። እኔ ከቦታው ስለለሁኝ፤ ማንንም ስለማላገኝ ትክክለኛውን መረጃ ለማግኜት አልችልም፤ ማን ምን ፈጸመ የሚለውን። በስማ በለው ደግሞ ለህሊና ዳኝነት ይቸግራል።   ግን ከአመድ፤ ከጭስ፤ ከውድመት የሚታፈስ ቅርስ እና ውርስ እንደሌለ ጠንቅቄ አውቃለሁኝ። ያሳዘነኝ ይህ ነው። ወረታም መቀጠሉን ሰምቻለሁኝ። ወረታ ወሳኝ ከተማ ነው። ይህ ለህወሃት ለተስፋው ጥሩ መደሊድል የሚፈቅድ ስትራቴጂያዊ የድል ብሥራትም ነው። ወደ አዲስ ዘመን፤ እንፍራንዝ፤ ጸዳ፤ ጎንደር ከተማ ለማቅናት፤ የአዲስ አበባ ጎንደር መንገድን ለመዝጋት፤ የ...

#ሰብአዊነት ከምህረት #ይጀመር። #መሪነት ከሰዋዊነት ነው የሚጀምረው።

  #ሰብአዊነት ከምህረት #ይጀመር ። #መሪነት ከሰዋዊነት ነው የሚጀምረው። #መሪነት ራስን በዲስፕሊን ለማስገዛት ከመፍቀድ ይመነጫል። #ማዳንን ማዳን የማይቻለው ስለምን ይሆን?   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #ምዕራፍ ፲፰   በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ካሉ ነዋሪወች ጋር ብልጽግና ያደረገውን ውይይይት በሙሉ አዳመጥኩት። አንዳንዱ ሙሉ ሳይሆን ከፊሉ ተቆርጦ በዜና መልክ ይቀርብ ስለነበር እሱንም ታግሼ በጥሞና ተከታተልኩት። ግብረ መልሱ #ወጥ ነው። ህዝቡ "መከላከያ፤ ፋኖ፤ ሚሊሻው፤ አድማ በታኙም ልጃችን፤ ወንድሞቻችን፤ የእህት የወንድሞቻችን ልጆች፤ የአክስት አጎቶቻችን ልጆች፤ የኛው የራሳችን ወገኖች ናቸው።" ሲሉ ነው ያደመጥኩት።    ይህ ማለት ሃዘኑም፤ ደስታውም የጋራ እና የወል ነው የሚል ዕድምታ አለው። ስለሆነም ከግብረ መልሱ የተረዳሁት የመፍትሄ አቅጣጫ ብሄራዊ የምህረት ዓዋጅ ቢታወጅ #ወጥ የሆነ የውስጥ መረጋጋትን ይፈጥራል ብዬ አሰብኩኝ። ስለሆነም ይህን ጉዳይ የመጀመሪያ ረድፍ እርምጃ የብልጽግናን መንግሥት ይወስድ ዘንድ ጠየቅኩኝ። አቤቶ ብልጽግና ሊሰማኝ ፈጽሞ አልፈቀደም። የተፃፈው ለብልጽግና ሆኖ #ፋኖ ግን ሰምቶ የምህረት ዓዋጅ ማወጁን አዳመጥኩኝ።   በገዢው ፓርቲ ቁብ ያልተሰጠው ቁምነገር ከፋኝ ብሎ ዱር ቤቴ ባለው ፋኖ መደመጡ ጥሩ ነገር ነው። የእኔ ጉዳዬ መኖሩ ሰላም ላጣው የአማራ ህዝብ እና የክልሉ ነዋሪ የውስጥ #መረጋጋትን በአንፃራዊ ሁኔታ ያመጣ ዘንድ ነበር ብሄራዊ የምህረት ዓዋጅ ያስፈልጋል ያልኩት። እርግጥ ነው ብሄራዊ የምህረት ዓዋጅ፤ ለሚያውጀው አካልም አቅም፤ ኃይል ያሰባስባል። የመረጃ #ፍሰቱንም ያጠናክራል። መተማመንም #በአንፃራዊነት ይፈጥራል።  ...