ልጥፎች

ከዲሴምበር 11, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ኢትዮጵያዊነት የደሜ ዕምነት ሥነ- ሕይወት! 31.12.2014ትን በምልሰት።

ምስል
ኢትዮጵያዊነት የደሜ ዕምነት ሥነ- ሕይወት! „ለፍጥረቱ ሁሉ ትራራለህ ይቅርም ትላለህ።“  መጽሐፈ ጥብብ ፲፩ ቁጥር ፳፯ ኢትዮጵያዊነት የፍጥረት ዓይነ - ህሊና ነው! እውነተኛ ሐሴትን የመፍጠር አቅሙ ሙሉዑ! ኪናዊ! ከሥርጉተ© ሥላሴ (Seregut© Selassie) ከጭምቷ፡ሲዊዘርላንድ። 31.12.2014 ለመነሻ። የኔዎቹ የፈተና ጥጉ ከ እሰከ የማይበልልት ኢትዮጵያዊነት በ2013 አዲስ ያገረሸ መከራ ነበረበት። እነ አቶ ጃዋር መሃመድ ወደ መድረክ ብቅ ያሉበት ጊዜ ነበር። የዛን ጊዜ ወጣት ጃዋርውያን በሁሉት ዙር ኢትዮጵያዊነትን ወጥረው የያዙበት ወቅት ነበር። በዓይነት ነበር ፓልቶኩ። ለመስማት ቀርቶ ሰምቶ ለመኖር ፈታኝ ጊዜ ነበር። እናም ይህን ጻፍኩኝ። ዘሀበሻም ፖስት አድርጎት ነበር። ዛሬ በምልሰት ሳስበው የዛን ጊዜው ጉግስ በተለያዬ ሁኔታ እዬታዬ ነው። ኢትዮጵያዊነት ጎላ ብሎ ሲወጣ ኦነግውያን እና ወያኔውያን ደማቸው ይፋላል፤ እሱን እንደ አንጡራ ባላንጣቸው ነው የሚዩት። ልብ ለልብ ሳይገናኙ እነሆ ዘመናት ነጎዱአ እነሱም አፈጁ። ትውልዱም አዲስ ዓራት ዓይናማ አብቅሎ ቀስ እያደረገ እያለበው ነው ጉድፋ ጉድፉን ጉንፋን ዕሳቤ። ተመስገን ነው። በታህሳስ 31 ቀን 2014 የተጠፈው በዛሬው ታህሳስ 11 ቀን 2018 ቤት ለእንግዳ ትለዋላች እትጌ ቀንበጥ። እትጌዋ አብራችሁ ትሆኑም ዘንድ በሞንሟናው ኢትዮጵያዊ አክብሮት ታከብራችሁለች። ማክብረን አትሰስትበትም እና። ·        ይህ ነበር መንፈሱ …  ዛሬ ላይ እትጌ ትግራይን ሳስባት እንደ እኔም እሰቧት በዚህ ውስጥ … የእነ ማህበረ የወያኔ ሃርነት ትግራይ መሳፍንታት የትጥቅ እና ስንቅ ጉዞ … መለከት መቼትን ይጠራል? ስለዚህም ደግሞ ማቅረብ ግድ አለ።

ገበር።

ምስል
ገበር። ይቺ ጥበብ ብቻዋን አስቀድሞ የተፈጠረ  አዳምን ጠበቀቸው። ከተፈጠረም በኋላ  እንደ አደራ ዕቃ ጠበቀቸው ከራሱ ኃጢያትም አዳነችው።“  መጽሐፈ ጥብብ ፲ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ© ሥላሴ (Sergute© Selassie) ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ 07.07.2010 እንዴት ናችሁ የእኔዎቹ ባለለዛዎቹ፤ ባለአደቦቹ የቀንበጥሻ ታዳሚዎቼ። ይህን ጹሑፍ በሌላ አውደ ግንባር ሆኜ የኮልሙኩት ነበር። ተቀምጦ የኖረ ወግ ቢጤ ነው። ያው አእምሮ ያፍታታል። ቃል እና ቃሉን ስታሟግቱት፤ ተጠዬቅም ስትሉት። እና አደግድጌ ዛሬ እስኪ ቀንበጥዬ ቤት ለእንግዳ በይው ስላት „መሰናዶዋ ሙሉ ነው አምጪው“ አለችኝ ቀልጠፍ ብላ። ለዛውም ለአደብ የተፈጠረች እኮ ናት ቀንበጥሻ፤ ካለ ዕድሜዋ ምርቋን ዋጥ ያደረገች ናት። „ሁኖልኝ! ነውንም“ አከለችበት። ቀጠለችው  በረጅሙ … ትንፋሿን አስከንድታ …  „ይኸው አረቲው ቡክቡካው፤ ነጭ ራያኑ ጠጅ እሳሩን ቅይጡን … አለችና በልዩ አውድ አሰተናገደችልኝ። ስለምን እንደጻፍኩት እኔ እና ህሊናዬ ብቻ ነው የምናውቀው። ብቻ ለፍንጭ ታህል ያልታለመ እንግዳ ነገር ድንገት ከች ብሎ ስለነበረ … ·        የወግ ገበታ። እነዛ ደማም ፍኩ ርትዑ ቀናት ይዳስሱኛል። እነዛ ዓይነ ግቡ፤ ባለ ውሽክታ ሰዓታት ያጫውቱኛል። እነዛ የንጋት ኮከብ ሰከንዶች ያነጋግሩኛል። ሁሎችም ሰማያዊ ሥጦታዎቼ ናቸውና … እንደ ሰማይ ፕላኔቶች የራቁ መጥምቆች …. መጠመጡኝ በትዝታና ናፍቆት ….   ሽሽ ሽሽ ሽሽት አሰኘኝ ወዴት? አላውቀውም  …. ሽውታ … ግን እንዴት አለህ? … አነተ ሳትሆን እኔ ታስሬያለሁ። አንተ ሳትሆን እኔ ምርኮኛ ሆኛለሁ። አንተ ሳትሆን እኔ ተዘግቶብኛል። አንተ ሳትሆን እኔ እርቆብኛል። አንተ ሳትሆን እ