ልጥፎች

ከፌብሩወሪ 16, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የማረተው የደራጎን ዝልቦ አይዋ ጎርምድ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የማረተው የ ደራጎን ዝልቦ። “ … ስለዚህ ክፉዎች፤ በፍርድ፤ ኃጢያተኞችም በፃድቃን ማህበር አይቆሙም፤ እግዚአብሄር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና። የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች። መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፩ ቁጥር ከ፭ እስከ ፮ ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie 16.02.2019                                   ይህ የሆነው ለላንቲካ አይደለም! ·        መነ ሻ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/94071#comments “ ጎንደር የራሱን ክልል መመስረት አለበት ” – የጎንደር ሕብረት ፕሬዚዳንት ዶ / ር ሙሉጌታ ካሳሁን እም! እማይሰማ የለም? እነ የሙት መሬት ባልደረባዎች እነ አያልቅበት ሌላ የሰላ ባለሦስት ጥንዙል የጨለማ ማቃዊ - ድቅድቅ - ሙርቅርቅ ዜማ ደግሞ ይዘው ከች ብለዋል። እነ የጎንደር ህብረት። ለጎንደር ህብረት ዛሬ ሥም ላወጣለት ፈለግሁኝ። ጎርምጥ ብዬ።  ውዶቼ ደህና ዋላችሁልኝ። ደህና ናችሁ ወይ? ናፍቆት በናፍቆት በብራና ፍቅርም ይላክላችሁ የእውነት ንፍቅ ብላችሁኝ ነበር የሰነበታችሁት። እኔ ግልጽ እና ቀጥተኛ ሴት ነኝ። የምላችሁ የሆንኩትን ነው። የጎንደር ህብረት መርዝ አላባራ አለሳ?                                           ዕውነት ይህን ያውጃል! ዛሬ ነው ከሳተናው ስቀጥል ዘሃበሻ ላይ አንድ ገዳይ መንፈስ ደግሞ ያገኘሁት። ከሲኦሎች ማህበር የተቀመመ አዲስ ቅይጥ ትርትር፤ በትን የተባለለት፤ ሸንሽን የተባለለት የመንፈስ መርዝ ነው። ጎንደር ብቻውን ለማሰቀረት ያተሰበ የተለመ መሰሪ ደ

ከታሪክ ማህደር፤ ኮርያ /ከጸሐፊ መስፍን ማሞ።/

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ከታሪክ ማህደር፤ ኮርያ “እግዚአብሄር አለኝ፣ --- አንተ ልጄ ነህ። እኔ ዛሬ ወለድሁህ። መዝመረ ዳዊት ፪ ምዕራፍ ፯ ጸሐፊ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! መቼም የኢትዮጵያ ታሪክ እንደ ሳይንስ የሚያመራምር እንደ ድንቅና ውስብስብ ልቦለድ ታሪክ ውሉን ለማግኘት ታሪኩ የሚመስጥ በዚህች ምድር ላይ ሌላ መሰል ታሪክ ያለው ሀገር ይኖር ይሆን? በ1950ዎቹ (እአአ) ኢትዮጵያ የምትደዳደረው በዘውዳዊው (ሞናርኪ) ሥርዐት ኢኮኖሚያዊ መሰረቷም ፊውዳላዊ። ያም ሆኖ ከራሷ ጂኦግራፊያዊ ክልል አልፋ አህጉራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ተቀባይነትና ግዝፈት ያላት ሀገር - ገራሚ ነው!!  ለማንኛውም ኮርያ እንዝመት፤  ዘመኑ ከ1950 እስከ 1953 (እአአ) ነው። የኮርያ ጦርነት። በኪም ኢል ሱንግ የምትመራዋ ሰሜን ኮርያ በሲንግማን ሪህ የምትመራዋን ደቡብ ኮርያ ወረረች። ሰሜኖች ኮሙኒስት ደቡቦች ካፒታሊስት ሥርዐት ተከታዮች። ከሰሜን ኮርያ ጎን ቻይና እና ሶቪየት ህብረት በግንባር ቀደምትነት ሲሰለፉ ከደቡብ ኮርያ ጎን ደግሞ አሜሪካና የምዕራብ ዲሞክራሲ ሀገራት ተሰለፉ። በዘውዳዊው የግርማዊነታቸው መንግሥት በፊውዳላዊ ኢኮኖሚ የምትደዳደረው ኢትዮጵያችን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ነበረች። እነሆ ከተመድ መሥራች ሀገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ኮሙኒዝምን ልትዋጋ ከዲሞክራሲያዊ ሀገራት ጎን ተሰለፈች። በ1951 (እአአ) ቃኘው ሻለቃ ጦር ወደ ኮርያ ዘመተ። እነሆም በሩቅ ምሥራቁ ጉደኛ ጦርነት ተዓምረኛ ተዋጊዎች የተባሉት የቃኘው ሻለቃ ጦር የኢትዮጵያን የጀግኖች ማማነት በደማቅ የደም ቀለም በዓለም ዐውደ ውጊያ አስፃፈ። ቃኘው ሻለቃ ጦር በዚያ የጦር ዐውድ በተለያዩ የጦር ግንባሮች

ዘመን ያላዳነው ቅምባ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  „በክፉዎች ምክር ያልሄደ በዋዘኞች ወንበር ያልተቀመጠ፤ እሱ የተመሰገነ ነው።“ መዝሙር ፩ ቁጥር ፩ ዘመን ያላዳነው ቅምባ። ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie 16.02.2019 ውዶቼ እንዴት አላችሁልኝ። ደህና ባጃችሁ? እንዴት ናችሁልኝ አዱኛዎቼ። እኔ ልዑሌ ፈጣሪዬ ክብሩ ይስፋ በሙሉ ጤንነት ላይ እገኛለሁኝ። ደህንነተኔ የጠያቃችሁ ክብሮቼ ደህና ነኝ። ግን ድንብልብሏ ከቶ እንዴት ሰነበተች? አላዛሯ ኢትዮጵያስ? መቼም ብዙ ነገር በዚህ 15 ቀን እንደ ተከወነ እና አንደገጠመ አስባለሁኝ። መንፈሴ ከአገሬም ሆነ ከግራጫዋ ፕላኔታችን ጋር ቢሆንም ጥሞና ጊዜ ላይ ስለነበርኩኝ በተዘጋ ገሃዳዊ ዓለም ግን ቧ እና ፏ ባለ መንፈሳዊ የፀጋ ትፍስህት አብሮነት አድርጌ ቆዬሁኝ። ተመሰገን። ዛሬ እጅግ ማልጄ ነበር የተነሳሁት። እትዬ ንግሥትም ፍንትው ብላለች። ብቻ እህታችሁ ትንሽ ዞር ዞር እንያልኩኝ ትንሽ ነገር ለማዬት ለማድመጥም ሞከርኩኝ። ያው የሳተናው ነገር ነፍሴ ነው።  ከቶ እናት እንዴት ሰንብቶ ይሆን ብዬ መጀመሪያ በፍጥነት ከፍቼ ያዬሁት የጥንት የጥዋቱን ቤቴን የሳተናውን ነበር። ደህና ነው። ያለፈኝ እንዳለፈኝ ሆኖ አዳዲስ ጹሑፎችን አነበብኩኝ። እሱን ሳተናውን ደህና በማግኘቴ በውነቱ ደስ ብሎኛል። አማካይ ስለሆነ። ትንፋሽም። ይኑርልን። ልፋቱን የሚመዝን አምላክም ልጆች ካሉት ይበርክለት ይቀደስለት፤ ትዳርም ከኖረው በረከቱን ሁሉ በስፋት ይለግስለት። እማከብረው ድህረ ገጽ ነው። እውነት ምን ብትምር ይሆን ዘመን ከዘመን እንዲህ ሊያልፍላት ያልቻለ የሚል ፈታኝ ነገር ግን በውነቱ ገጥሞኛል። እናላችሁ ዕውነት ምን አለ ተምር ብትሆን አልኩኝ። ተምር በልጅነቴ