የማረተው የደራጎን ዝልቦ አይዋ ጎርምድ።

እንኳን ደህና መጡልኝ።

የማረተው የደራጎን ዝልቦ።

“ … ስለዚህ ክፉዎች፤ በፍርድ፤ ኃጢያተኞችም
በፃድቃን ማህበር አይቆሙም፤ እግዚአብሄር
የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና።
የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።
መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ቁጥር ከ፭ እስከ

ከሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
16.02.2019

                                 ይህ የሆነው ለላንቲካ አይደለም!
·       መነ
ጎንደር የራሱን ክልል መመስረት አለበት የጎንደር ሕብረት ፕሬዚዳንት / ሙሉጌታ ካሳሁን

እም! እማይሰማ የለም? እነ የሙት መሬት ባልደረባዎች እነ አያልቅበት ሌላ የሰላ ባለሦስት ጥንዙል የጨለማ ማቃዊ - ድቅድቅ - ሙርቅርቅ ዜማ ደግሞ ይዘው ከች ብለዋል። እነ የጎንደር ህብረት። ለጎንደር ህብረት ዛሬ ሥም ላወጣለት ፈለግሁኝ። ጎርምጥ ብዬ። 

ውዶቼ ደህና ዋላችሁልኝ። ደህና ናችሁ ወይ? ናፍቆት በናፍቆት በብራና ፍቅርም ይላክላችሁ የእውነት ንፍቅ ብላችሁኝ ነበር የሰነበታችሁት። እኔ ግልጽ እና ቀጥተኛ ሴት ነኝ። የምላችሁ የሆንኩትን ነው። የጎንደር ህብረት መርዝ አላባራ አለሳ?
                                          ዕውነት ይህን ያውጃል!
ዛሬ ነው ከሳተናው ስቀጥል ዘሃበሻ ላይ አንድ ገዳይ መንፈስ ደግሞ ያገኘሁት። ከሲኦሎች ማህበር የተቀመመ አዲስ ቅይጥ ትርትር፤ በትን የተባለለት፤ ሸንሽን የተባለለት የመንፈስ መርዝ ነው። ጎንደር ብቻውን ለማሰቀረት ያተሰበ የተለመ መሰሪ ደባም ነው። 

ይህ መርዛማ ጉዳይ በዛን ሰሞናት በነፃነት ክብረ ልዕልና በዬሚዲያው ይለፍ እዬተሰጠው ሲቃበጥ የነበረው የአቶ እነቶኔ ጹሑፍ በስተመጨረሻው ላይ “የጎጃም ክልል” ይኑርልን ብሎ አረፈ እና እንክህ እንክህ ሲሉት ከባጁት ደንበኞቹ ድህረ ገጽ ከሁሉም በፎርፌ ተሰናበተ። አሁን ደግሞ የጎንደር ማህበር የጎንደር ክልል ብሎ ዘጭ ብሏል። ለነገሩ ጠረኑ ሎሌነት ጥራኝ የተፈጠረበት ነው ... 

 ጋቤጣ አሮጌ ካሬታ መንፈስ ነው ድሮውም ቢሆን ተሸክሞ የኖረው። አይድንም። እርር ድብን የሚልበት ጉዳይ የአማራ አይበገሬነት ከቀን ወደ ቀን እዬጎበተ በመጣ ቁጥር ያባትተዋል። ያደቆነ ሰይጣን እንዲሉ …

                       ይህ የ66ቱ የፖለቲካ አክተሮች ለማንገስ አልነበረም።

ሸንክ አሰተሳሰብ አያልቅበትም ለጎንደር ህብረት። ጊንጥ ነው አሰተሳቡ ሆነ መነሻና መድረሻው።  የተደራጀውም ለዚህ ነው። ጎንደርን መለመላዋን አስቀርቶ ለማክሰል። የጎንደር ልጅ እድሜ ይንሳው እና ለዛ ጃርት ሳጅን በረከት ስምኦን ማን አለ ቀድሞ ነገር። ብቅ ሲል ሲነቀል፤ ሲነቀል ዘሩ ከስሏለኝ። አንድ ለምስል ማግኘት አይቻልም። አሁን ፌድራል ክልል በሚበላው ላይ።
                              ይህ ድምጽ ለከረንቡላ ጨዋታ አይደለም።

የጎንደር ህብረት የተፈጠረበትን የሚያውቀው እሱ ራሱ ነው። ጎረይና ቅቤ እና የደለበ ወይፈን በሬ አሰኝቶት ይሆናል። የወልቃይት፤ የጠገዴ፤ የራያ፤ የመተከል ጥያቄዎች ባክነው ባለቤት አጥተው እንዲቀሩ ሲያሴር ባጀ፤ ያ ሲከሽፈበት ደግሞ አሁን ደግሞ የሰላ ማጭዱን ይዞ ከች አለ።

                          በዚህ ውስጥ የቆሰሉት ለአማራነት ክብር ነው!

የጎንደር አራጇ፤ የአማራ ሰቃዩ ብዛቱ ቁጥር ስፍር አጣ? እንዴት በአሁን ጊዜ ይህ ጥያቄ ሆኖ ይነሳል? ደመነፍስ እሳቤ ነው። ከመደነፍስም ያለፈ ትቢያ አስተሳሰብ ነው። ከውድቀቱ የማይማር ሰላቢም - ሰልሳይም ድርጅት።

                      ኢትዮጵያዊነት ከዚህ በላይ የሚገልጽ ንዑድነት የለም።

የአማራን አልጋ አንጣፊነት፤ የአማራን ሎሌነት የሚመኘው ይህ የዳራጎን አሰተሳሰብ ማህበርተኛ ጭላጭ ባገኝ ብሎ ደግሞ በአዲስ አንቡላ መንፈስ ዱቅ ብሏል። ጎንደር በታሪኩ አጋር ያውም ደም የገበረ ውስጥ ያገኘው በዘመነ አማራ ብሄርተኝነት ነው። የ አማራ የህኢለውና ተጋድሎ ለጎንደር የሥለት ልጁ ነው። በቅንነቱ ውስጥ አባቶቹ ሰግደው፤ ጹመው፤ ጸልዬው ያሰጡት እዮራዊ ሽልማት። መቼም ዘመን ሰጠኝ ብሎ ጎንደር ደፍሮ ሊናገር የሚችለው የአማራ የህልውና ተጋድሎ የሰጠውን ችሮታ፤ በረከት እና ረድኤት ብቻ እና ብቻ ነው።
                           መኖርን ያሳጣው ማንነቱ በክብር ለማሰመለስ!
ለዚህ ነው በግራ በቀኝ አሰፍስፈው የራሳቸውን ወገኖች በቁጠባ ይዘው ግን በእሱ ደም በእሱ ግብር በአክተርነት ዘመን ተዘመን ተከብክበው እንደ ታቦት የኖሩት ሁሉ ዘረፋን አና ብለው በአደባባይ ተያይዘውት የባጁት። አሁን ደግሞ በአማልጅ ... 

                      የአማራ ተጋድሎ ከዚህ የበታችነት ለመውጣት ነው!

ባለፈው ሁለት ዓመት የነበረው አሸርጋጅነት አይሆኑ ሲሆን፤ መንፈሱም ህልሙም ከሰሞ እንሆ አሁን ደግሞ የጠሉት ይወርሳል እንዲሉት በአዲስ ካፖርተኝነት ዘመን ከሰጣቸው ጋር ደግሞ ባተማረረ ማንነት አዲስ ዘጭ ዘጭ እያስተዋልን ነው። መገለባበጥ ሃፍረትም ነውርም አይደለምና።
            አማራኔትን አትንኩ እንጂ ጎንደርን ከልሉ አልነበረም ተጋድሎው።

የሆነው ሁሉ የሚሆነው ሁሉ ከ አማራ መንፈስ ጥላቻ ጋር የተያያዘ ነው። አማራ መሆን የመከራ ማማረቻ ፋፍሪካን ማቋቋም ማለት ነው።

                                       ጀግነት በካብችኖ አይለካም
                                        ጀግነንት በመሆን ውስጥ
                                        የህልውና ተጋድሎ አውራ!


ዛሬ ምስጋና ይግባው ለሐምሌ 5 የጀግና ቀን ከኮ/ ደመቀ ዘውዱ ተጋድሎ ጎንደር ሁነኛ ልብ፤ ሁነኛ ቅን መንፈስ፤ ሁነኛ ኑዑዳን አይዞህ ባይ በዘመኑ አግኝቶ የማያውቀውን ቅኑንጃም ሰጠውና ያን የጨለማ ቀን በጎጃም ክንድ እና ትክሻ አሳለፈው። 

ጎንደር ሲባል ጸጉሩ የማይቆም የለም። ስለምን? የእድምታ ሚስጢረኞችም የበቀሉት እዛው ባዕት ስለሆነ አዳሉ ካልተባሉ ይፈቱላቸው ነበር። ውጪ አገር ያን ያህል ጊዜ ብጹዕን አባቶቻችን ሲቀመጡ ባሊህ ያላቸው የፖለቲካ ሊሂቅ የለም። ስለምን? እነሱም ያውቁታል እኛም አሳምርን እናውቀዋለን። አሁን በ አስተርዮ አዲስ ትይንት ደግሞ ታዚቤያለሁኝ። መጪው ባለተራውን ጊዜን የሚተነብይ። 
                                        መከረኞቹ የአማራ እናቶች!

እኔ እንደ ሥርጉተ ጎጃም ሃይማኖቴ ነው። ለጎጃም አይደለም አቅሜን ህይወቴን ብሰጥለት ቅጭጭ አይለኝም። ጎጃም የከፈለውን መስዋዕትነት ማንም አልከፈለውም። ጎጃም የገበረውን መንፈስ ያህል ማንም አልከፈለውም። ጎጃም ከሚስጢር በላይ ነው። ጎጃምም ከሃሳብ በላይ ነው። ጎጃም ማተቤ፤ ክብሬ፤ ኩራቴ፤ አለኝታዬ ተስፋዬ ማግስቴ ነው።


                              ህልውናዬን አትዳፈሩት ነው ተጋድሎው!

በአንድም በሌላም አትለያዩት አማራን ጎጃም ጎንደር ሸዋ ወሎ እያላችሁ የሚሉ ቅኖች አሉ። ህመማቸው ይሰማኛል። ግን የእግዚአብሄር መንግሥት ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ ይላል። በዛ የቀን ጨለማ ወቅት የጎንደር አብዮት ያነሳቸውን ሉላዊ ጥያቄዎች አንግቦ ልጆቹን፤ ትዳሩን፤ ኑሮውን፤ ነፍሱን የገበረ ታላቅ የአገር ዋርካ ልዩም ባለውለታ ነው ጎጃም። ስለሆነም ለጎጃም ጎንደር ታቦት ቢቀርጽለት ቢያንሰው እንጂ አይበልጥበትም።
                                በአማራነት ውስጥ ያለው ይኸው ነው!
ለዚህ ቀን ያደረሰ ማገር ህዝብ ነው ጎጃም። ጎጃም ከቅኔ በላይ ነው። ሞት ቢመጣ ከጎጃም አማራ ነፍሱን ጎንደር መለዬት አይኖርበትም። ዛሬ እያደቡ ሽንኮች አዲስ የቤት ሥራ እና አጀንዳ እዬተሰጣቸው እነ ልጅ ፋሲል የኔ ዓለም አና ብለው በረከት ያመጣው የአማራ ብሄርተኝነት ሲሉ፤ አንዱ ደግሞ ጎጃም ብቻውን ይከለል ሲል፤ ሌላውም ያን ተከትሎ ጎንደር ብቻውን ይከለል ይለናል። ለጎንደርም ለጎጃም ታዝኖ አይደለም። 

                                  ተጋድሎው "አማራነት ይከበር" ነው።

አማራ በአቅሙ ልክ ጎልቶ፤ ደምቆ፤ ፈክቶ መውጣቱ ሁሉንም ስለሚያርደው ነው በዚህም በዚያም ሳሃ የበዛበት። አማራነት ተፈሪነትን የወረሰው ከኢትዮጵያዊነቱ ነው።

                   የመንፈስ ቅዱስ ድምጽ የአማራ ተጋድሎ ይቀጥላል።

ኢትዮጵያን ሲዋዳት አማራ ለልዋጭ፤ ወይ ለቀን ማማሻ አይደለም። በፍጹም! እሱን ለነጋዴዎች መተው ነው። በዬዘመኑ ሲተውኑ ዕድሜያቸው እያለፋቸው እዬሄደ ነው። ለነገሩ ዕድሜው ወደ ቁልቁል እዬተቆጠረም እዬታዬ ነው …

                                         ጎጃም ነባቢቴ!

አማራነት ኢትዮጵያን የሚወዳት የነባቢቱ በትረ መሰረት ስለሆነችም ነው። እሱን አሳምራ፤ አብራርታ፤ ስለምትገለጠውም፤ ስለምታነበውም ጭምር ነው። እሱና እሷን መለዬት አያችልም። የሙጥኝ ቢላት እናቱን ሚስጢሩን የማመሳጠር የብቃቱ ልክ ነው ይህን የጸጋ ጃኖ ያጎናጸፈው። ጥበቡም ያለ ከዚህ ላይ ነው።
                                ይህ ገናና ታሪክ መሸቀጫ አይሆንም!

አማራነት ምስባክነት ነው። የሚቆረጥመው ይቆረጣጥመው። እናቱን የሚወድ ልጅ ምስባክ ቢባል የተገባ ሥያሜ ነው። አማራነት እናቱን ተፃሮ የመወጣት ተፈጥሮው አይፈቅድለትም። እሷን እንዴት እንዳበጃት መንፈሱ መጸሐፉን ጽፎለታል እና። ደክሞለታታል። 
                            ዕብድት ነው ይህን ተጋድሎ አሳልፎ መስጠት!
                                               ባንዳነትም!

መንፈስ በትውስት አይጸደይም። መንፈስ በራስ ውስጥ ባለ ክህሎት ውስጥ ነው የሚጸደዬው። መከራ የተገበው እኮ ባልበቀለበት አለሁ ሲል ሲሾልክ፤ ሲሾልክ፤ ሲንዘላለጥ ለኖረው ዕዳና ፍዳ የሆነው ይኸው ጉዳይ ነው። ከረባትም ገበርዲንም በጽናት ውስጥ ሲሆኑ ነው የሚያምርባቸው።  

በዬትኛውም ዘመን የትኛውም ድርጅት ይህን መሰል ህዝባዊ ሰልፍ አሰናድቶ አያውቅም!
በዚህ ውስጥ ነው የአማራ መንፈስ መመዘን ያለበት።
አማራነት ይከበር እንጂ ጎንደሬነት ይከበር አልነበረም።
የተደረጀ፤ የተሰናዳ የቀደመ ልቅና እራሱን አያስቀማም!
በዬበበበበበበበ በበ
የሆነ ሆኖ አማራ አንድ ሆኖም መጪውን መከራ መቋቋም አይችለውም እንኳንስ ተበትኖ። መጪው ለአማራ የከፋ ዘመን ነው። “የህልውና ታገድሎ” ሠው ሰራሽ መስሏችሁዋል። ይህ መንፈስ ቅዱስ የቀረጸው ጉዳይ ነው። ለዚህም ነው የዲያቢሎስ መንፈስ የተጠናወተው ሁሉ የአማራ የህልውና ታገድሎ ለማለት ሲያድጠው፤ ሲያንዘላልጠው፤ ሲፈጠፍጠው፤ ሲያስነጥሰው የምታዩት - ሲያርደው የምታዩት ...

                                  አማራነት ማሟያነት አይሆንም!

አማራ ባለበት ቦታ ሁሉ እሱን መንፈሱን ሥነ - ልቦናውን፤ ትውፊቱን ታሪኩን ማንነቱን፤ አቅሙን ልቅናውን ተስፋውን የሚቃማ ሳጥኤል አለ። አማራነት ቀራንዮነት ነው። አማራነት ጎለጎታነት ነው። አማራነት ፍዳ መሸከም ማለት ነው።

                             ትግሉ ዳር ደንበር የለውም የህልውና ነውና!

ያልገባው የአማራ ልጅ ይህ ሚስጢር ነው። አማራ ያሰገኛቸው ማናቸውም ትሩፋቶች ይፈለጋሉ፤ አማራ ግን በዛ ተፈጥሮ ውስጥ እንዲሰክን አይፈለገም። ለምን ለሚለው ጫፉን ካስያዝኳችሁ መሰረቱን ፈልፍሎ ማግኘት የናንተው ነው። የትም ቦታ በዬትም ሁኔታ ዛሬም የሚገለለው፤ የሚሳደደው አማራ ነው ግን ተመስጥሮ። ቁልጭ ባለ በጠራ አማርኛ  የአማራ ጭቆና በዬትኛውም ሁኔታ አለ።  ለአማራ እውቅና ከመስጠት ጸሀይ ጨረቃ ብትሆን ይሻላታል።
              የአማራ ተጋድሎ ለቅምጥሎች ሆነ ለግልባጦች የሚሆን አይደለም!
                                         
የተንጠፈጠፈ ተስፋ እንኳን አለ ለማለት ለጊዜ ማማሻ ብቻ ነው ስለ አማራ የሚተጋ አንደም አላዬንም አልሰማነም፤ ለድልድይነት ብቻ ትናንትም ዛሬም። እራሱ አማራው በራሱ ውስጥ አለመኖረን ከድቶት ሸሽቶት - ፈርቶት - መኖሩ ኑሮው አላስተምረው ብሎ ስልብነቱን ዘመን እዬነገረን ነው። ሎሌነትን አብዝቶ ይመኛል - ዛሬም።

                                       ጥቃት የማያውቀው አማራ ለራሱም አለለት!

አማራነት እኮ ሌላ ፍች የለውም ኢትዮጵያዊነት ነው። ይህን የሌሉበት አክሮባቲስቶች ሊያስተምሩን ይዳዳቸዋል። አለማፈር! 

ዘመን ሲገለብጣቸው እዬተገላበጡ እንደ ሽንብራ ቂጣ አማራ ትክሻ እና ልቅና ቼ! ማለት የተለመደ ነውና። አቅም ከሌለው ስለምን አማራ አንድነት ላይ ያነጣጥራል? ስለምን ሌላው ላይ አይነጣጠረም? ስለምን ቁጥሩ የበዛው ሲደርጅ አይገረብጥም አያሰፈራም ነበር?
                        ዘሩ እንዲጠፋ ለተበዬነበት አማራ ራሱ ለጉዳዩ አለለት። 

የጎንደር ህብረት ሲኦል፤ የሳጥናኤል ማህበረ መንፈስ እዬደለቀ ዛሬ ጭልጋ ደንቢያ ላይ ያለው እልቂት እሰደስቶት ሌላ በታኝ የሆነ ደግሞ አዲስ እሳቤ ይዞ ብቅ ብሏል። ጥሩ ነው ካልጎሼ አይጠራም። እንኳንም ጎሼ። ተግበስብሶ አብሮ ከመግበስበሰ በጠራ መንገድ መጪ ማለቱን አማራ ያውቅበታል።
                                   በዚህ ቁስለት ውስጥ የሌለ አማራ 
                                            የቁም ሙት ነው
                                                 በድን!

አማራ ዘመኑን የኖረው ያለአሰተማሪ ነው። ዕውቅትን ለፈጠረ የኔታ ማህበረሰብ የሚገደው የለም። ቻይነቱ ስለጎዳው ቻይነቱን ቀነስ አድርጎ በአቅሙ፤ በክህሎቱ ልክ የፖለቲካ ድርሻውን ማጉላት ግድ ይለዋል። አማራ ለግርድና እና ለሎነት አልተፈጠረም እና።
ምን አልባት አማራ ልማር ቢል ቅንነቱን እና ደግነቱን ቀነስ ማድረግን ይሆናል። ያበዛዋል ቅንነቱን ሆነ ሰው አማኝነቱን። የትናንቱ ላይበቃ ዛሬም ያመናቸው ምን ላይ እንዳሉ መስፈሪያ አያስፈለገውም። ወይንም ጠንቆይ ቀላቢ መሄድ የለበትም። 

                                                     ይህ የሚያስተኘው አማራ 
                                   ገና አልተፈጠረም! እጭ ነው!

ከዛ በተረፈ አማራ ፈለግ ፈላጊ ከሆነ የአባቶቹ ልቅና ተርፎም ይናኛል። ይልቅ አማራ ማቄን ጨርቄን ሳይል ግእዝን ሁለተኛ ቋንቋው አድርጎ በራሱ እርምጃ መምህራኖችን በዬቤቱ እዬቀጠረ ይማር። 
ይህን የጥቃት ጥቅርሻ ተንተርሶ የሚተኛ
 አማራ ራሱን የዳጠ ነው!

ከግእዝ ማርና ቅኔ ይዘንባል። የዓለምን ስልጣኔ የገነባ ማንነት ቢገፋም፤ ቸል ቢባልም ዛሬ ናሳን ሄዶ መጎብኘት ነው። አውሮፓንም እንዲሁ። ለዚህ ነው ልባሞቹ ልጆቻቸውን ቀጥ አድርገው ግእዝ እያሰተማሩ የሚገኙት ጀርመኖች። ሚስጢር ናቸው፤ ሚስጢር ደግሞ አክባሪውን ያከብራል፤ ባከበሩት ልክ ዲታዎችም ብልሆችም ናቸው - ጀርመኖች። የሻቱትን ያገኙት ባከበሩት ሚስጢር ውስጥ ነው። “ልብ ያለው ሸብ” ይላሉ የጎንደር አማራዎች።
                                        መሆን በቅኔ  -አማራ!


አማራ ሚስጠርህ እንደ አባይ ፏፏቴ እዬተነፎለፎለ ከደጀህ ውጭ ውጩን አያሳኝህ። በነገራችን ላይ ግዮን ወደ ጉምዝ የተከለለበት ሚስጢር ይገባችሁልን? የዕውቀት ማዕከልነቱ በራሱ ሌላ የዘመን የቤት ሥራ ነው። ዝልቅነትህን እንዳወጣ ከመቸብቸብ በራስ ነገር ላይ ብታተኩር ስንት ላም ጣም አለው ሲሳይ ቤት አና ብሎ በዝቀሽ በገባ በነበረ -  ለአማራ!
                                          ለዚህ መከራ ለመቆም 
                                          በአማራነት መደራጀት!

ዛሬ በሁሉም መስክ እዬተሳደደክ መሆንህን ልብ ገዝተህ፤ ማስተዋልን አስበህ መራመድ ይኖርብሃል። በራስህ ውስጥ ያለው ማንነት በዬሰከነዱ አሳዳጅ ያምርትልሃል። ተኝተህ በለኝ ትለው ዘንድ ነው ዘንዶው ዕሳቤ ደግሞ የጎንደር አዲስ ክልል የተጠዬቀልህ።

                                           የአማራነት ግማድ!

ያ ሁሉ መስዋዕትነት ባክኖ፤ ተኖ እንዲቀር ብቻ አይደለም፤ ከዛም ከዚህም መስዋዕነቱ እንደተለመደው ለነጋዴዎች በጅምላ እና በችርቻሮ ለማቅረብ በተሰጠው ድጎማ ልክ የቀረበ ዝልቦ እሳቤ ነው የጎንደር ጉርምጥ ማህበር ይዞ የመጣው። ዱቅዱቅ!ስለሆነም አማራ ሆይ! ልብ ይስጥህ። ዛሬ ልጆች አሉህ። ቢያስንስ በቃኝ ያሉ።

                                     አዲሱ የአማራ ትውልድ እንደ
                                    ትውፊቱ ራሱን ለሁለገብ የፖለቲካ 
                                                እውቅና ያብቃ!

መንፈስህ ከራስ ነገር ላይ መሳረፍ ብቻ ነው መፍትሄው። ደጅ ደጁን አትይ አማራ ሆይ! ያለህ ይበቃሃል። በአንድ አማራነት መንፈስ ውስጥ መጪውን ትውልድ ለማትረፍ ትጋ። መቼም ዛሬ እንደዜጋ እታያለሁ ብለህ አማራ እንደማትተርብ ነው … ቀን የሚጠበቁ በርካታ ፍንጆች አሉ። ጫፋጫፋቸውንም እያዬህው ነው ... 

አቤቱ አማራ ሆይ! ካለተደራጀህ፤ በቅጡ ካለተሰናዳህ ሱናሜው በሁሉም መስክ አንተን አስምጦ የሚሄድ ስለመሆኑ ልብ በለው። መዘናጋቱ ይብቃ! ቸለልተኘነቱም ይቁም። አንተ በመኖርህ ውስጥ ነው አገርህ መኖር የምትችለው። 

የድርብ ድርሻ ግዴታ አለብህ። ራስህን በማዳን ውስጥ አገርህን ለማዳን ራስህን ችለህ ቁምጥገኞች ምርኩዝ ፍለጋ ይማስኑ … አንተ የአባቶች ሌጋሲ ከበቂ በላይ ነው። ለዛም ሞጥረህ ግዕዝን አጥናው። ከዳዊትም፤ ከሰለሞንም ጥበብ በላይ ግዕዝ ውስጥ በስፋት ይቀዳልሃል ሚስጥር የመኖር በለው የመመራመር። … "ልብ ያለው ሸብ።"

“አህዛብ ለምን ያጉረመርማሉ?
ወገኖችስ ለምን ከንቱ ይናገራሉ?”
መዝሙር ፪ ቁጥር ፩

"አማራነት ይከበር!"
አማራነት ሸቀጥ አይደለም!
አማራነት በገባይ ህግ አይገዛም!


                                           የኔዎቹ ኑሩልኝ።

                                            መሸቢያ ጊዜ። 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።