ልጥፎች

ከሜይ 4, 2019 ልጥፎች በማሳየት ላይ

መከሰስ ካለበት እውነት ይከሰስ? ወይንም ኢትዮጵያዊ አመክንዮ አልተፈጠርክም ይባልና የ4ኪሎ ጉባኤ ካቴና ይዘዝለት።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  መከሰስ ካለበት እውነት ይከሰስ? ወይንም ኢትዮጵያዊ አመክንዮ አልተፈጠርክም ይባልና  የ4ኪሎ ጉባኤ ካቴና ይዘዝለት። „የሞቱ ዝንቦች የተቀመመውን የዘይት ሽቱ ያገሙታል፤ እንዲሁም ትንሽ ስንፍና ጥበብንና ክብርን ያጠፋል።“   መጽሐፈ መክብብ ፲ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 04.05.2019 ከመነኩሴዋ ዚዊዘርላንድ                                                                    ይህ ተጋድሎ ዛሬ ለኦነግ ተሸልሟል። ይህ ፎቶ የ2.05.2019 ከሳተናው የተወሰደ ነው። ውዶቼ የማከብራችሁ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ ወይ? ዛሬ ቪንቲ ከፍቷታል። እኔም ውስጤ ክፍት ብሎኛል። መከፋት የለመድብን ቢሆንም እንደ አገር ቀረ በ ስንል ተስፋ እንዲህ እያራቀ እያደረቀ ሲሄድ መከፋት ግድ ነው። ተስፋ መድረቁ በመጋጋጥ ሆነ። ሁነኛ አልባ አገር? ሁነኛ አልባ ተስፋ? ሁነኛ አልባ ራዕይ? ሁነኛ አልባ ትውልድ? እም ነው ምጥ። ፍጥነቱ ከብርሃን ቀድሞ መላ አካላታችን እያዳረሰ ሐሤትን በገፍ ሲናኝ የነበረው የመጋቢት 24.2010 ኢትዮጵያዊ አዬር አዳምኗል ። ሥር የለሹ የተስፋም መቅኖው ቁርጠት ላይ ነው። ወገቤን ፈለጠኝ፤ እራሴን ሰነጠቀኝ፤ ትክሻዬን ተጫነኝ፤ ጆሮዬን ሸነጎረኝን፤ አጥለቀለቀኝ፣ አቅለሸለሸኝ፣ ቃር ቃር አለኝም እያለን ነው። አቤቶ ግርባው ብአዴን በሰልፉ ዋዜማ የሰጠውን መግለጫ፤ በመሪዎቹ የሚተላለፉ እላፊ ንግግሮችን አቶ ደመቀ መኮነን አይክልም ለጊዜው እሳቸው ደግሞ ቁርጣችሁን እውቁ ብለው እስከሚያሰናብቱን ድረስ ያው ቅኔው እያስነኩት ስለሆነ … በሌላ በኩል የሃይል አሰላለፋቸውም ከዬትኛው