ልጥፎች

ከኖቬምበር 5, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

አቶ ፍጹም አረጋ ከሃላፊነታቸው ተነሱ።

ምስል
አዲስ የፕሬስ ሴክረታሪ ለውጥ በጠ/ሚር ጽ/ቤት። „አቤቱ በልቤ ሁሉ አመሰግንህ አለሁ።   ተአምራትህንም ሁሉ እናገራለሁ።“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ© ሥላሴ  05.11.2018 ከገዳማዊቷ አገር ከሲዊዝ። በአዲሳዊነት ቀመር ፋታ ሳይሰጥ እዬገሰገሰ ያለው የጥጋናዊ ለውጥ ማዕበል ዛሬ ደግሞ አዲስ ነገር እያሰደመጠን ነው። አንዱንም በቅጡ አጣጥመን ሆድ ዕቀውን ዛረጋግፈን ፈትሸን ሳንቃኘው በዬዕለቱ በአዲሳዊነት መርህ ግብር ወደ ፊት የሚገሰግሰው የለማ አብይ ካቢኔ አሁን አዳምጡኝ እያለን ነው። በፎቶ በተደገፈ አጫጭር መረጃዎችን በማዕከልነት ሲያሰተናግዱ የቆዩት አቶ ፍጹም አረጋ በሌላ መተካታቸውን አዲስ ዜና እያደመጥን ነው። "ከአረጋ" ሥያሜ አንድ ቀነሰ እንደ ማለት፤ አቶ ፍጹም "አረጋ" አቶ አዲሱ አረጋ አቶ ዳዊት "አረጋ።" የሆነ ሆኖ እርእሱ እንዲህ ይላል። „Ethiopia:ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ስር የተቋቋመው የፕሬስ ሴክሬታሪ በይፋ ስራ መጀመሩን አስታወቀ“ ማድመጡን ትንታኔውን ለእናንተው የቤት ሥራ ሰጥቼ ሥርጉትሻ ሹልክ … https://www.youtube.com/watch?v=rBfiQz1fH0Q ሰላም ሲሆኑበት ችግርን የመፍተት አቅሙ አንቱ ነው። መሸቢያ ጊዜ። ትሁት አካባሪያችሁ።

ከወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም የአማራ ተጋድሎ ግብ አይጠብቅም!

ምስል
የሴቶች የፖለቲካ ዕውቅና ማግኘትን አንገት ማስደፋት ትልቅ የታሪክ ፍቀት ነው። „አቤቱ ምህረትህን ለዘላለም እዘምራለሁ እውነትህንም በአፌ ለልጅ ልጅ እናገራለሁ።“ መዝሙር ፹፭ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  05.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። የሴቶች የፖለቲካ ዕውቅና ማግኘትን አንገት ማስደፋት ትልቅ የታሪክ ፍቀት ነው። የኢትዮጵያ ሴቶች በማንኛውም መስከ ለዘመናት የአገር አንድነት እና ሉዑላዊነትን ለማስከበር ጉልህ ተጋድሎ ያደረጉ ናቸው። የኢትዮጵያ ሴቶች ያልተሳተፉበት፤ ያልተሰዉበት አንድም የትግል መስክ አልነበረም። በሌላ በኩል በኢትዮጵያ የአገር ግንባታም የኢትዮጵያ ሴቶች ሁለገብ ተሳትፏቸው ቢልቅ እንጂ የሚያንስ አይደለም። የኢትዮጵያ ሴቶች ብልህነታቸውን፤ መክሊታቸውን፤ ጸጋቸውን፤ ስጦታቸውን፤ ጥበባቸውን፤ ብልህነታቸውን፤ ሁለመናቸው ሳይቆጠቡ ሳይሳሱ የሰጡ ድንቅ ፍጥረቶች ናቸው። የኢትዮጵያ ሴቶች በማናቸውም መሰክ የግንባር ቀደሙን ድርሻ በመውሰድ እኩልነታቸውን በዬዘመኑ በዬምዕራፉ አስመስከረዋል። ቀደም ባለው ጊዜም ቢሆን ለሴቶች የፖለቲካ ዕውቅና በመስጠት አጤዎች የአንስት እቴጌዎችን ምክራቸውን በማድመጥ፤ ብልህነታቸውን በመቀበል የብዙ ዕድል ባለቤት መሆን መቻላቸውን ታሪክ ያስረዳል። በ60ዎቹ የማርክስስት ሌኒኒስት ፍልስፍና ተጋድሎ ሂደቶች ውስጥም ሴቶች እኩል ተሳትፎ ቢያደርጉም ከፖለቲካ የተገለሉበት፤ እንዳሉም ያማይቆጠሩበት ለመስዋዕትነት ብቻ የሚፈለጉ የበይ ተመልካቾች ነበሩ። ከዚህም ሌላ የሰው ልጅ አቅርቦት ላይ ብቻ አትኩሮት ከማድረግ ውጪ ሴቶች ዜግነታቸውን በስልት የተነፈጉበት ወቅት ነበር። „እንዳያማ ጥራው እንዳይበላም ግፋው“ ዓይነት ነበር። አሁን ባለው የአማራ እና የኦሮሞ ተጋድሎ በተገኘው የለወ