ልጥፎች

ከኦገስት 30, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የአዲሱ ለውጥ ትሩፋት።

ምስል
መንትዮሾቹ የተግባር ልዕልቶች በደግነት      ማዕዶት! „የፃድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፤ ሙሉቀን እስኪሆን ድረስ እዬተጨመረ ይበራል።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ 30.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። አዲሱ ለውጡ አደጋ ያመጣል የሚሉት የአባ ቆስቁስ የአቶ በረከትን የኑዛዜ መስቃ እንዲህ መናነቱን ተግባር ቁሞ ይመሰክራል። የአባ ቆስቁስ የአቶ በረከት ስምዖን ሙገት ቁሞቀርም መሆኑ እንዲህ ይታያል። ይህ ተግባር አላዛሯ ኢትዮጵያ የተፈጠረችበትን የደግነትን፤ የቸርነት ትውፊቷን አህዱ ብላ መጀመሯን ያሳያል። ሲጀመር ጀምሮ ለውጡ ሰውኛ እና ተፈጥሮኛ ነው በማለት ነበር ስሞግት የባጀሁት። አዲሱ የኢትዮጵያ መንገድ ይሄውና ዛሬም የበጎ ምግባርን ተግባር ተስፋን ሰንቆልናል ... ይህ ድርጀት መቄዶኒያ በራስ አነሳሽነት ከመንገድ ላይ የወደቁ አቅመ ደካሞችን በራስ ጊዜ፤ ጉልበት እና አቅም የተጀመረ ነው። መስራቹ ቅዱስ ብቻቸውን የጀመሩት ተቋም ዛሬ እንዲህ አፍርቶ ለወግ ለማዕረግ በቅቶ ለዚህ ቀን በቅቷል።  ቤተ መንግሥትም እንዲህ እንሆ ታደመበት። ወይ ጊዜ እንዲህ ትክሳለህ! ሁለት ዳጋጋውያን አንስቶች እራሳቸው ደካሞችን በማስተናገድ የተሰለፉበት ይህ የቸርነት መንገድ አዲሱ የለውጥ መንፈስ እንዲህ ቅንድስና፤ ብጽዕና ያለው መሆኑን ያመላክታል። ይህ የቸርነት ጉዞ ትንሽ ራቅ አድርጌ የዛሬ አምስት ዓመት የት ትደረስ ይሆን ብዬ ስጠይቀው „አይተሽ ፍረጂ ብሎኛል።“ እናንተም አይታችሁ ፍረዱት ልበል በተሰጠኝ መልስ መሰረትነት።  የኔ ውዶች የጹሁፌ ታዳሚዎች ትንሽ ገፋ አድርገሽ ወደ 10 ዓመትስ ስለምን አለወሰድሽውም ትሉኝ ይሆናል። 10 ዓመቱ ረዘመብኝ እና ነው በእኩሌታው

ቢያፍሩ ምን አለ አባ ቆስቁስ?

ምስል
አባ ቆስስቁስ አቤቶ  አቶ በረከት ስምዖን  ሥልጣናዊ ቅርፊት  ፍርክርክ ብትክትክ። „ምናምንቴ ሰው የበደለኛም ልጅ በጠማማ አፍ ይሄዳል፤ በዓይኑ ይጠቅሳል፤ በእግሩ ይናገራል፤ በጣቱ ያስተምራል፤ ጠማማነት ብልቡ አለ፤ ሁልጊዜም ክፋትን ያስባል፤ ጠብንም ይዘራል።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፮ ከቁጥር ፲፪ እስከ ፲፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ  30.08.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። የሳጅን በረከት ሥጦታ - ለአማራ።   ·        ኑ ዛዜ። ቀድመው የተናዘዙት አቦይ ስብሃት ነጋ ነበሩ። የሰሞናቱ  የኑዛዜ ሁለተኛው ነው ። ባለ ኑዛዜው አቶ በረከት ስምዖን እና ማህበረ ኔትወርካቸው ነው። በጣም የሚያስደስተው እና ተስፋ የሚሰጠው ደግሞ አቶ በረከት ስምዖን በብአዴን ላይ ስሞታ አቅራቢ ሆነው መገኘታቸው ነው። ብትክትክ አሉ። አሁን ነው እኔ እርግጥም ብአዴን ራሱን ችሎ መቆም መጀመሩን የተደስትኩበት። ብራቦ! ብአዴን ብለናል ተዚህ ተኮሽ አይሏ ሲዊዚሻ። በሌላ በኩልም አባ ቆስቁስቁስ አቶ በረከት ስምዖን በአቶ ደመቀ መኮነን ያቀረቡት ክስም ቢሆን አቶ ደመቀ መኮነን ጥሩ ሰው መሆናቸውን ማወቅ አስችሎለኛል። ምክንያቱም አቶ በረከት ስምዖን የሚጠሉት ወይንም የሚያገሉት ወይንም የሚያሳድሙበት፤ ወይንም የሚያሳድዱት ሰው ጥሩ እና ቀና ሰውን ብቻ ነው። የሚበልጣቸውን ወይንም ሴራቸውን የሚያጋልጣቸውን።  ስለሆነም በጣም ለድጋፍ ዳታ ያበዛሁበት የአቶ ደመቀ መኮነን ነገር አቋሜን ጥርት ባለ መልኩ ደጋፊያቸው ሆኜ እንድቆም አስችሎኛል የሰሞናቱ የአቶ በረከት ስምዖን ኑዛዜ፤ ወቃሳ እና በዛቸው ላይ እንደለመደባቸው የከፈቱት ዘመቻ። ስለሆነም ከዛሬዋ ዕለት  ከእለተ ሃሙስ የቀን ቅዱስ 30.08.2018 ጀምሮ የአቶ ደመቀ መኮነን ደጋፊ