ልጥፎች

ከጁን 4, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ፍቅር ቁጥር አይደለም።

ምስል
           የፍቅር ተፈጥሯዊ መርህ                 ቁጥር አይደለም።                                          ከሥርጉተ ሥላሴ 03.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።)                        „የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሄርን መፍራት ነው። ሰነፎች ግን ጥበብን ተግሳጽን ይንቃሉ።“                                         (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፯) ፍቅር ቁጥር አይደለም፤ አንድ ሁለት ሦስት እዬተባለ በጥቁር ሰሌዳ ላይ በጠመኔ የሚጻፍ። ፍቅር መስፈሪያ የለውም። ፍቅር ዳርቻ ዲካ የለውም። ፍቅር ስፋት እና ቁመት የለውም። ፍቅር ቅርጽም ፎርምም ሊወጣለት አይችልም። ፍቅር አልፋ እና ኦሜጋ ነው። ፍቅር ነፍስ ነው። ፍቅር ደም ነው አብሮ የተፈጠረ። አብሮ የሚኖር። ልባም ከሆንክ ለትውልድ የምታወርሰው ቋሚ ቅርስ ነው። ትውልድንም የምታስቀጥልጥበት የህሊና ርስት ነው። ፍቅር ደም ነው። ቀዝቃዛም ለብ ያለም ሳይሆን ሙቀቱንም ቅዝቃዜውንም ለመለካት መሳሪያ ያልተሰራለት አንተም እራስህ የማታውቀው፤ ደረጃውን መመዘን መስፈር መመትር የማትችለው። ነገር ግን ፍቅር ተቀብሮ የኖረ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን ሳንጠቀምበት በመቅርታችን፤   እራሳችን ስናጠፋበት የኖርንበት የረቂቅ ሚስጢራት ቅምር ውጤት ሆኖ በተቃራኒው፤ ባልሆነ መንገድ ነው እትጌ ዓለም መጪ ስትል  የኖረችው። ወደ ሰው ሰብዕና ስንመጣ አንድ ሰው በልቡ ያለውን፤ ከደሙ ውስጥ ያለውን የፍቅር ተፈጥሮ የማያውቅ ፍጡር ከሆነ፤ አውጥቶ ለመጠቀም የማይተጋ ሰው ከሆነ የነቃው ህሊና ድፍን የሆነበት ሰው ነው። ይ