ልጥፎች

ከኖቬምበር 15, 2018 ልጥፎች በማሳየት ላይ

የአቅም ጥገትን መንገዱን ማንበብ ይቻላል!

ምስል
የሚቀድመውን የመለዬት ጥበብ ለሁሉም መርሁ  ቢሆን ምን አለበት? „የእግዚአብሄር ቤተ መቅደስ እንደሆናችሁ የእግዚአብሄርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁንም?“ ወደ ቆረንቶስ ምዕራፍ ፫ ቁጥር፲፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ 15.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ  የአቅም ጥገትን መንገዱን እንደ መጸሐፍ ማንበብ ይቻላል። ·        እ ፍታ አላዛሯ ኢትዮጵያ የ27 ዓመታት ግዞታዊ ኑሮዬ በቃኝ ብላ ማዕበል ውስጥ ኑሯውን ካደረገች ወደ ስድስት ሰባት ዓመት ሊሆናት ነው። ከድምጻችን ይሰማ ሉላዊ፤ ሰላማዊ ድንቅ አብዮት ጀምሮ ሲሰላ፤ በቃኝን ተከትሎ ያሉ ወጀቦች ሁሉ ተነሱም፤ ተቀመጡም ፍሬዎቿን ሲለቀሙ ኖረዋል። ለቃሚዎች ደግሞ አሁን ተለቃሚዎች ሁነዋል። ወጀቡ እንደ አገር ለአላዛሯ ኢትዮጵያ እኩል ነው። አደጋውም ያን ያህል ሴንሲቲብ ነው። አሁንም አውሎ ላይ ናት እናት ኢትዮጵያ። ቀላል እርምጃ አይደለም የሰሞናቱ ውሳኔ እና ቁርጠኝነት። እጅግ ደፋር እና እጅግም ልብ የተሸለመው ልባም ድርጊት ነው። አፈጻጸሙ እራሱ ተውኔታዊ ነው። ለነገሩ እኔ በመንፈሳዊ ስለማምን የአምላክ ስራ ነው። በቃችሁ ብሎናል አማኑኤል። ድፍን 50 ዓመት ሲባክን ለነበረው ተከታታይ ትውልድ እንደገና የመፈጠር ያህል ነው። ከአነጋገር ይፈረዳል፤  ከአያያዝ ይቀደዳል እንዲሉ። ·        ብ ይን እስቲ ስጡበት። አንድ ሙሉ ቤት በጉንዳን ቢወረር፤ ልብሱ ሁሉም ጉንዳን ቢወረው፤ ምግቡንም ሁሉ ጉንዳን ቢወረው፤ መኝታውንም ሁሉ ጉንዳን ቢወረው የቤቱ ባለቤት መጀመሪያ የቱን ቢያሰቀድም ራሱን አረጋግቶ ከጉንዳን እርግጫ እና ቁንጥጫ ወጥቶ ጉንዳኑ በቁጥጥር ስር ሊያውል ይችላል ብዬ ራሴን ፈተንኩት? ውዴቼ ታዳሚዎቾቼ ግን የቤቱ ባለቤት የቱን

አቶ ያሬድ ዘሪሁን ወደ ኬኒያ ሊሸሹ ሲሉ

ምስል
የአቤል እንባ ወደ እዮር ይጮሃል … „ማንም እራሱን አያታልል ከእናንተ ማንም በዚች ዓለም ጥበበኛ የሆነ ቢመስለው ጥበባኛ ይሆን ዘንድ ሞኝ ነው።“ ወደ ቆረንቶስ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፲፱ እስከ ፳   ከሥርጉተ ሥላሴ 15.11.2018  ከገዳማዊቷ፡ሲዊዘርላንድ። የቀድሞው የመረጃ እና የደህነንት ሃላፊ እና የፌድራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት ጄኒራል አቶ ያሬድ ዘሪሁን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኢቢሲ ዘገበ። የአቤል ዕንባ ባክኖ መቼም አይቀረም። የድምጽ አልባዎቹ የኢትዮጵያ እናቶች የ27 ዕንባም ፈሶ አይቀርም።  እሳቸው ኬኒያ ሌላኛው አቶ ክንፈ ዳኘው ወደ ሱዳን ሌላው ደግሞ ወደ ጁቡቲ ይቀጥላል እንዲህ እያለ ማለት ነው … ቢያንስ  የኢትዮጵያ መንግሥት መረጃውን የጨረሰውን ተጠያቂዎች መቅደም ካልቻለ ሾልከው ይሄዳሉ፤ መሄዳቸው ሳይሆን ክፋቱ እዛም ሆነው ማነኮራቸው አይቀሬ ይሆናል።  ስለዚህ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ዳታ ብዙ ከእንግዲህ አዋጪ አይመስለኝም። እራሱ ግብረ መልሱም የከፋ ሊሆን ይቻላል፤ እንዲህ ዓይነት ሰው ከጭካኔ ስለማይመለስ በዬቦታው የፍንዳታ የቦንብም ሊሆን ይቻላል ሊከሰት ይችል ይሆናል። አጥፍቶ መጥፋት ተስፋ ከቆረጡ ሰብዕናዎች ስለሚመጡ። በሌላ በኩል ብዙ ዜናውን አለማሟቅ እና በተደሞ እና በትእግስት ሁኔታውን መከታተል በእጀጉ ያስፈልጋል። በተለይ ከተሞች አካባቢ በጊዜ መግባትን ጨምሮ ሁሉም ዘብ መቆም ይኖርበታል ለዬአካባቢው ደህንነት።   ዘመን ያሉ ጥያቄዎችንም ተግ አለማድረግ፤ በመንግሥት ላይ ጫና የሚፈጥሩ ሁኔታዎችንም ማስታገስ ያስፈልጋል። ከባድ ሁኔታ ነው አሁን ያለው ሃላፊነት። ሃላፊነት የሁሉም ነውና። በመንፈስም በጸሎትም መንግሥትን መርዳት የዜግነት ግዴታችን ነው።