ልጥፎች

ከጁላይ 27, 2022 ልጥፎች በማሳየት ላይ

27.0.2022vኢትዮጵያ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ከብዳናለች ትለለች ሥርጉትሻ።

እንኳን ወደ ከበቡሽ ብሎግ በሰላም መጡልኝ።  ከሰሞኑ ፌስቡክ ላይ የሰራኋቸው ስብስብ። 27.07.2022   ኢትዮጵያ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ከብዳናለች ትለለች ሥርጉትሻ። የኢትዮጵያ ቅዱስ መንፈስ በገብያ ህግ አይተዳደርም። መስቀል እልል አለ። የኔታዊት በትፍህስት ራዕይ። መስቀላዊት በድል ጎዳና። አራት ዕርዕሰ ጉዳይ አዋህጄ ላቅርብ። " የቤትህ ቅናት በላኝ። " አባ እንዴት አደሩልን ? ደህና አደሩልኝ ? ይፍቱኝ አባት ዓለም። አሜን። ህሊና ይሞገት። በዬቦታው በጓዳ የተከዘነውን። በጦርነቱ ወቅት አባ ለአንድ ሠራዊት ሲያሳልሙ ፖስት አደረኩኝ። እሳት ለብሳ እሳት ጎርሳ አንዲት አንስት ተነሳች። ምኑን ለጠፍሽ ብላ ? ቀደም ባለው ጊዜ ላስረዳ እደክም ነበር። ዛሬ እንደዛ የለም። ቅንነት ከተነነበት ጋር አቅም ማባከን ደግ አይደለም። መራራ ስንብት ይፈታዋል። ደጅ ላይ ቁመው የሚጠብቁኝ ቅኖች አሉ። እነሱ ቤተኛ ይሆናሉ። እራሱን ቆልፎ ለሚመጣም ቤቴ ህግ አለው። የሆነ ሆኖ ያቺ ያልታደለች እህቴ ተዋህዶ እዮራዊ መሆኗን ስታ የብፁዑ ወቅዱስ አባቴን በረከት ከፔጅሽ አልይ ስትል በአክብሮት አሰነባትኳት። ብዙ እንዲህ ዓይነት ሰብዕናወች አሉ። የመሸጉ የልዩነት አታሞወች ሌላም አዋሳ በግፍ የታረደችው እጩ ሊቅ ትግሬ አማራ በማለት ሃዘን ላይ የወደቁ ቤተሰቦችን ሲያቆስሉ ነበር። ያችን የመሰለች አበባ ወጣት አፈርነት አልነበረም ጉዳዩ። የሚገርመው ሌላውን የሚያዝኑትን ሁሉ ረስተው የነበሩ ነበሩ። ታዝቤ