#ስጋቴ "የስበት ህግ" #ምልክት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ላይ #እንዳይጫን ነው።
#ስጋቴ "የስበት ህግ" #ምልክት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ላይ #እንዳይጫን ነው። "ቤት በጥበብ ይሠራል፤ በማስተዋል ይጸናል፤ በውቀት ከከበረውና ካማረው ሃብት ሁሉ ጓዳወች ይሞላሉ።" አሜን። ይደረግልን። ይሁንልን። (ምሳሌ ምዕራፍ ፳፬ ከቁ ፫- ፬) ማህበረ ቅንነት እንዴት ናችሁ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። #ምዕራፍ ፲፱። የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን ፕሮጀክት #ሎጎ በመደበኛ እከታተላለሁኝ። ለእኔ ሎጓቸው የምር ጉዳዬ ነው። የፖሊሲወቻቸው መሻቶች በሎጓቸው #ካፒትንነት የሚካሄድ በመሆኑ። #የአብይዝም #ብልፄው ፖሊሲ የለሽ ነው የሚሉ ወገኖች እንዳሉ አውቃለሁኝ። በስሱ ብቅ ጥልቅ የሚሉ፤ በሙሉነት ግን በጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ህሊና ተመስጥረው የተያዙ ፖሊሲወች አሉ። የአብይዝም መሪ ሃሳባ የሚሰክነው በሎጎወቻቸው ነው። ስለዚህም በአትኩሮት የየፕሮጆክታቸውን ሞቶ እና ሎጎ እከታተላለሁኝ። እስከዛሬ ባየሁት የሎጎ ምርጫ ከኢትዮጵያ ኦርጋኒክ ተፈጥሮ፤ አሻራ እና ትውፊት #ሽሽት ነው እማይባቸው። እኔ እንደማስበው አብይዝም የዓለም ሎጎ #ጭማቂ የመሆን ህልም እንዳለው አስባለሁኝ። የራስ - ነገር፤ ቀደምት ክብርና - ልዕልና፤ አዛውንት ባህልና - ቅርስ፤ የበቃ የታሪክ - መዘከርነት እና የኛነት ድምቀት ለአብይዝም አጀንዳው የሚሆን ሆኖ አላየሁም። ህዝባዊ ድጋፍን ላለማጣት ደማቅ ጉዳዮችን ተቀብሎ በውዞ፤ ወይንም አሸጋሽጎ ለማስቀጠል ጥረቱን አያለሁኝ። ዓድዋ ወደ ማዕከል መጥቷል። ሥሙ ግን የተለፋለትን ጥረቱን ገዳይ ነው። "ዓድዋ #ዜሮ ዜሮ" አንድ ዜሮነት አልበቃም። ዜሮ ስኮዬር? የታሪክ ሙሁራንም ጭጭ ነው ያሉት...