"#ጥቃቅን ቡድን?" የምክክር ኮሚሽኑ ሥያሜ። #ሰብዕናን #ይጫናል። ሰብዕናዊ ክብርንም ይዳፈራልም።

 

"#ጥቃቅን ቡድን?" የምክክር ኮሚሽኑ ሥያሜ። #ሰብዕናን #ይጫናል። ሰብዕናዊ ክብርንም ይዳፈራልም።
 
"የዋሆች ብጹዓን ናቸው፤
ምድርን ይወርሳሉና።"
(የማቲወስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፭)
 
#ምዕራፍ ፲፱።
 
የምክክር ኮሚሽኑ ለሥራ እንዲያመቸው የጉባኤውን ተሳታፊ በተለያዩ ዘርፎች ማደራጀቱን አዳምጫለሁኝ። "#ጥቃቅን ቡድን" የሚለው አልተመቸኝም። ንዑስ እንዳይሉት #ንዑስ የሚባል አለ። ከንዑስ ዝቅ ያለውን ይመስለኛል "#ጥቃቅን ያሉት። 
 
ቡድኑ የሰወች #ማህበር ነው። ቡድን ለቋሚም ለጊዚያዊም ተግባር ይደራጃል። የምክክር ኮሚሽኑ የጉባዔ አደረጃጀት #ለጊዜያዊ ተልዕኮ ነው።
 
ቡድኑ ለተወሰነ ጊዜ፤ በተሰጠው አጀንዳ፤ በተፈቀደለት #የጊዜ ማዕቀፍ ተለይቶ የተሰጠውን #ተግባሩን ከውኖ የሚያስረክብ። ለሰወች ጊዚያዊ ይሁን ዘላቂ ቡድን "#ጥቃቅን" ማለት ይከብዳል። #ሰብዕናን #ይጫናል
 
ጥቃቅን #ለቁስ ሊሆን ይችላል። #የነገር ሥም። ለሰው ልጅ ማህበር ግን "#ጥቃቅን" ፈጽሞ የማይመጥን ሥያሜ ነው። ከጥቂት ደቂቃወች በፊት መግለጫ ተሰጥቷል። ከዛ ስሰማው ከበደኝ።
 
ከጥቃቅን ይልቅ #መሠረት ቢባል የተሻለ በሆነ ነበር። #መነሻ ቢባልም እንዲሁ ለሰው ልጅ የሰብዕና ልዕልና የሚመጥን ይመስለኛል። አስኳል ይባላል በፖለቲካ አደረጃጀት። ይህንንም ከአዕውፋት ዝርያ ወይንም ከዶሮ፤ ከቆቅ፤ ከዥግራ ጋር የሚያገናኝ መንፈስ ስላለው፤ እንደ "#ጥቃቅን" ባይከብድም ………
 
ቡድን #በሰው ልጅ ነው የሚደራጀው። ስለዚህ ለሰው ልጅ ማህበር የሚሰጠው ሥም #መጣኝ#በክብሩ ልክም ቢሆን ጥሩ ነበር። ፈጣሪ አልቆ፤ አጽድቆም በእኔ ዕሳቤ አጹሞም የፈጠረው የሰው ልጅን "ጥቃቅን" ሰብዕናን ይገስፃል።
ለምክክሩ ኮሚሽን ለታሪክ አዘጋገብ፤ ለአሻራም፤ ለትውፊትም፤ የሰውን ልጅ ማህበር "ጥቃቅን" ለእኔ አልተመቸኝም። በዘመነ - ህወሃት "በጥቃቅን" የተደራጁ የሚለው ነገር ነበረው። የዛ ውርስ መሰለኝ። የምክክር ኮሚሽኑ ቃሉን እንዳለ መውሰዱ የተገባ ነው ብዬ አላምንም። #የንዑስ - #ንዑስ ቡድን ማለት ይቻል ነበር።
እርግጥ ነው የዘርፋ አባላት ተግባራቸውን በማጠናቀቅ ላይ ስለመሆናቸው አድምጫለሁኝ። ተልዕኮው ከመሠረቱ ወደ ላይኛው ክፍል ቢሄድም የቡድኑ #ሥያሜው ግን ቀጣይ ይሆናል።
በአንድ የታሪክ ማዕቀፍ ውስጥ ያለ ማናቸውም ክስተት ተግባሩም፤ ሂደቱም ዝክረ ይሆናል። #በቋሚነት ልል አልችልም። የኢትዮጵያ ፖለቲካ የቀደመን ነገር በአወንታዊ ተቀብሎ የማስቀጠል ባህል የለሽ ስለሆነ። ቢሆን ግን አፍሶ ከመልቀም፤ ለቅሞ ከማፍሰስ አዟሪት ውስጥ ቢወጣ የመዋለ - መንፈስ፤ የመዋለ - ንዋይ፤ የመዋለ - ጊዜ፤ የመዋለ - ተግባር #ጥሪት ቅርስም መሆን ይችል ነበር።
ማህበረ ቅንነት እንደምን አድራችሁ፤ አረፈዳችሁ፤ ዋላችሁልኝም።
ቸር አስበን ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ።
Sergute©Selassie.
28 / 07/026.
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው አሜን።
See less

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።