የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሊመራ የሚገባው #ሰብዓዊነት እና #ተፈጥሯዊነት ሊሆን ይገባል።
የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሊመራ የሚገባው #ሰብዓዊነት እና #ተፈጥሯዊነት ሊሆን ይገባል። "ልቤ ጽኑ ነው፥ አቤቱ ልቤ ጽኑ ነው፤ እቀኛለሁ፤ በክብሬም እዘምራለሁኝ።" (መዝሙር ፻፯ ቁጥር ፩።) ትናንት የአማራ ፖለቲከኞች እስር እና የፍትህ ውሳኔ ሃሳቡን ሙሉውን፤ የእኔ ሃሳብ ሳይታከልበት ከBBC ያገኜሁትን መረጃ ሼር አድርጌ ነበር። #ሳስበው ነው ያደርኩት። የተጠየቀውን ቅድመ ሁኔታ ያልተቀበሉ ፖለቲከኞችን ሊስቱን ትናንት አላገኜሁም ነበር። አሁን ከአቶ ዳንኤል በቀለ ፔጅ የተገኜ። አመሰግናቸዋለሁኝ። #ምዕራፍ ፲፱። ጉዳዩን ከህግ አንፃር የመፍትሄ አቅጣጫው ከድንጋጌወች ጋር አዛምደው ቁልፋን የሚፈቱት የህግ #ባለሙያወች ናቸው። ለዚህም ነው ከአስተያዬት የተቆጠብኩት። በሌላ በኩል ውሳኔው የእኛ ዕይታ ሳይሆን #እንግልት ላይ የሚገኙት የፖለቲካ እስረኞችን ውሳኔ ብቻ ነው ሊጠብቅ የሚገባው። እስረኞች ከጠበቆቻቸው ጋር፤ ከቤተሰቦቻቸው ጋር መክረው፤ ጉዳዩን አስበውበት የሚፈጽሙት ቢሆን የተሻለ ነው። ሃሳባቸውን የሚያባትል ዕይታ ከማንኛውም ወገን መቅረቡ ጥሩ አይደለም። ከእኛ ምንም ተጨማሪ #ጫና አያስፈልጋቸውም። ጠቃሚውን እና ጎጁን መስመር የመወሰን አቅም የባለ ጉዳዮቹ ጉዳይ ነው። እንደ እኔ ያለ ፍትህ ፍለጋ በቋሚነት #መባተል ነው። እስረኞች #እንዳይዘነጉ #አዌርነስ መፍጠር ነው። በመሪው በብልፄው ላይ #ጫና መፍጠር ነው በብዕር እና በብራና አጋዥነት። የእኔ ንጹህ ፍላጎት የሃሳብ አፍላቂ ሞጋቾችን መመከት እንጂ ህሊናን ማሰር አያስፈልግም ባይ ነኝ። በኢትዮጵያ #አንድም የፖለቲካ #እስረኛ እንዳይኖር ነው እምተጋው። ሙሉ ዕድሜዬ ...